የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የዓመቱን የስራ ጊዜ መገባደድ አስመልክቶ ለዳኞች የምስጋና መግለጫ ልከዋል፡፡ የመግለጫው ሙሉ ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
የዓመቱን የስራ ጊዜ መገባደድ አስመልክቶ ከጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት
ለዳኞች የተላከ የምስጋና መግለጫ
ሐምሌ 30 ቀን 2011 ዓ.ም
የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ሆኜ ከተሾምኩበት ከጥቅምት 22/2011 ዓ.ም ጀምሮ ዳኞቻችን በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት፣ ትጋት እና የሙያ ፍቅር ሃላፊነታቸውን በመወጣት ላይ መሆናችሁን ተገንዝቤአለሁ፡፡ ለዚህም ጠለቅ ያለ የዓመቱ ምስጋና ይገባችኋል፡፡
እኔና ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ የስራ ሃላፊነት ተቀብለን ወደ ጠ/ፍ/ቤት ከመጣንበት ጊዜ ጀምሮ በምናስበው መንገድ ሃላፊነታችንን እንድንወጣ ያደረጋችሁልን በጎ አቀባበል እና ድጋፍ የሚደነቅ ነው፡፡
እንደምትገነዘቡት የፍ/ቤታችን አዲስ አመራር የተቃኘው አዎንታዊ አመራር ወይንም Positive Leadership በሚባለው የአመራር አቅጣጫ ነው፡፡ ይህ አይነት አመራር በግልጽነት፣ በመተማመን፣ የጋራ ራዕይ በመፍጠር የሚያምን፣ በአዎንታዊ እና በበጎ ጎኖች ላይ የሚገነባ አበረታች የአመራር ዘዴ ነው:: በሌላ በኩል የምንከተለው የአመራር አቅጣጫ ቴክኒካዊ ብቻ ሳይሆን ፈር ቀዳጅ ይሆናል፡፡ ባለፉት ወራት ፍ/ቤቶቻችን ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ውጤታማ እና ቀልጣፋ እንዲሆኑ በርካታ የስልጠና፣ የሕዝብ ግንኙነት፣ የአስተዳደር ወዘተ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡
የጀመርነውን የፍ/ቤቶች ማሻሻያ ስራ የበለጠ ቅርጽ ለማስያዝ የሶስት ዓመት የስራ ዕቅድ ነድፈን ተወያይተን ተስማምተንባቸዋል፡፡ ዕቅዱን ለማስፈጸም መንግስት ከመደበልን በጀት በተጨማሪ የሀብት ማሰባሰብ ተግባር ቀጣዩ ስራችን ነው፡፡
ውድ ዳኞች
ከተጀመሩት የማሻሻያ /Reform/ ስራዎች ጥቂቱን ላስታውሳችሁ፡-
• ፌደራል ፍ/ቤት ራሱን የማስተዳደር አቅም እንዲጠነክር፣ በአባላቱ ጥንቅርም ሆነ በስልጣን ወሰን የተጠናከረ የዳኝነት አስተዳደር ጉባኤ እንዲቋቋም ረቂቅ የሕግ ማሻሻያ ተዘጋጅቷል፤
• ፍ/ቤቶቻችን የሚመለከቷቸው ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደርን ውጤታማ ለማድረግ የፍ/ቤታችንን አደረጃጀት እና ስልጣን የሚወስነውን አዋጅ 25/88 እና ተከታታይ ማሻሻያዎችን በአዲስ መልክ ለማሻሻል የተጠቃለለ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፤
• ‘’FITH” (ፍትህ) በመባል ተሰይሞ በUSAID /አሜሪካን የልማት ድርጅት/ አጋርነት የሚከናወነው ፕሮጀክት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በዳኞች ስነምግባር ደንብ እና በዳኞች የስራ አፈጻጸም ምዘና ላይ ትኩረት በማድረግ በመስራት ላይ እንገኛለን፡፡ የሚዘጋጁት ደንቦች እና መመሪያዎች የሀገራችንን የቆየ የዳኝነት አስተዳደር እና ዓለምአቀፍ መመዘኛዎችን ቀምረው የሚዘጋጁ ሲሆኑ ተጠናቀው ወደ ስራ ሲተረጉሙ ለተቋማችን ጥንካሬ ከፍተኛ አስተዋፆ ያደርጋሉ፡፡
ውድ ዳኞች
እየተደረጉ ያሉት የሕግ ማሻሻያ ስራዎች በፍ/ቤቱ በተሰየመ የከፍተኛ የህግ ባለሞያዎች ቡድን የሚታገዝ ነው፡፡ ባለሙያዎቹ ከፍተኛ የሞያ ታማኝነት እና የአገልግሎት መንፈስ አሳይተዋል፡፡
ክቡራን ዳኞች
በምሳሌነት የተጠቀሱት እርምጃዎች ላቀድናቸው የፍ/ቤቱ የሪፎርም ስራዎች መሠረት የሚሆኑ ናቸው፡፡ በረቂቅ ህጎች /ደንቦች/ መመሪያዎች ላይ የዳኞችን አስተያየት የማሰባሰቡ ስራ ይቀጥላል፡፡ የተጠቀሱት የህግ ማዕቀፎች ከጸደቁ በኋላ አስፈላጊ ስልጠናዎች ተደርገው የሪፎርም ስራውን በሰፊው እናራምዳለን፡፡
ውድ ዳኞች
የዳኝነት ሃላፊነት ከባድ መሆኑን ሕዝቡ እንዲገነዘበው ማድረጉ አንዱ ሃላፊነታችን ነው፡፡ ሕዝቡ ከፍርድ ቤቶቻችን ሚዛናዊ ብቻ ሳይሆን የተቀላጠፈና መብት አክባሪ የፍትህ አገልግሎት ይጠብቃል፡፡ በአንጻሩ የጉዳዩች ፍሰት ብዛት፣ የአቅርቦት ውስንነት እና ሌሎች እጥረቶች ስራችንን ፈታኝ ያደርጉታል፡፡
የዳኝነት የስራ ጫና ለመቀነስ በቅርቡ ከ150 በላይ የረዳት ዳኞች ቅጥር በማከናወን ላይ እንገኛለን፣ በሂደት ግባችን እያንዳንዱ ዳኛ ማለትም 354ቱም ዳኞች ረዳቶች እንዲኖሯቸው ነው፡፡
በዚህ ዓመት ካከናወናቸው ስራዎች አንዱ 16 ተጨማሪ የጠ/ፍ/ቤት ዳኞች በፓርላማ መሾማቸው ነው፡፡ ከተሾሙት ዳኞች 40 በመቶ የሚጠጉት ሴቶች መሆናቸው እንደ ትልቅ ዜና መታየት አለበት ፡፡
ክቡራን ዳኞች
በተለይ በወንጀል ጉዳይ ከሌሎች የፍትህ አካላት ጋር መነጋገር የሚገቡን ጉዳዮች ስላሉ ²አብይ ኮሚቴ² በተባለው መድረክ ላይ ገንቢ ሚና በመጫወት ላይ ነን፡፡ በወንጀል ጉዳይ የተጠረጠሩ ሰዎች በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ የሚያደርጉ ዋና ጉዳዮች ተለይተው ችግሩን ለመፍታት እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው፡፡ ይሄ ለነገ የሚባል ስራ አይደለም፡፡
ውድ ዳኞች
ሃላፊነታችን የየዕለት የመዝገብ ስራ ሳይስተጓጎል እንዲከናወን ማድረግ ብቻ ሳይሆን የዳኝነት ዘርፍ እንደ ሶስተኛ የመንግስት አካል ሚናው ምን እንደሆነ ለሕዝብ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የመንግስት አካላት በአዲስ መልክ የማስገንዘብ ስራንም ይጨምራል፡፡ በዚህ ዓመት የፍ/ቤቱን በጀት በቀጥታ ለፓርላማ አቅርበን ማስወሰናችን አንደኛው የፍ/ቤቱ ተቋማዊ ነጻነት እርምጃ ማረጋገጫ ሆኖ ይታያል፡፡ በብሄራዊም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፍ/ቤታችን ገጽታ እያደገ ነው፡፡ በመሆኑም እንድናከናውናቸው የሚጠበቁ ዓላማዎች በርካቶች ናቸው፡፡
ውድ ዳኞች
ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ቀልጣፋ እና ውጤታማ ፍ/ቤት በመገንባት ሀገራችን ወደ ዲሞክራሲ እና ልማት ለመሸጋገር አስተዋፆ ለማድረግ የታሪክ አጋጣሚ መፈጠሩ አስደሳች ነው፡፡ ለአንድ የሕግ ባለሞያ ከዚህ የተሻለውን የእርካታ እድል ሊፈጥር የሚችል ምን አጋጣሚ ይገኛል? በተባበረ መንፈስ ጠንክረን በመስራት ይሄንን እድል ለማሳካት እንችላለን፡፡
ውድ ዳኞች
ከዳኝነት የሚጠበቀውን ከፍ ያለ የሙያም ሆነ የጨዋነት/ (integrity) ደረጃ የማያሟሉ ዳኞች በስልጠና ወደ መስመር እንዲገቡ ጥረት ይደረጋል:: ከዚያ የሚሰፉ ችግሮችም በሕጋዊ ስርዓት የሚታዩ ይሆናል፡፡
ወድ ዳኞች
በመደበኛ ቀጠሮዎች ከሚታዩት መዝገቦች ሌላ ከ2009 ዓ.ም በፊት ተከፍተው እንደ ውዝፍ መዝገብ /Backlog/ የፈረጅናቸውን መዝገቦች ለመወሰን ከፍተኛ ትጋት አሳይታችኋል፡፡ በዚህ ረገድ በሶስቱም ፍ/ቤቶቻችን 7,663 መዝገቦች እልባት አግኝተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በእረፍት ጊዜአችሁ ቀሪ የዘገዩ መዝገቦችን ለመወሰን አብዛኞቻችሁ ፍቃደኞች መሆናቸሁ ሌላ የሚያስመሰግን ተግባር ነው፡፡
ወድ ዳኞች በመጨረሻም
በከፊል ስራ ላይ ብትሆኑም ከዛሬ ሐምሌ 30/2011 ዓ.ም ጀምሮ ፍ/ቤቶቻችን ዝግ በመሆናቸው መልካም የእረፍት እና የቤተሰብ ጊዜ እመኛለሁ፡፡ መስከረም ሲጠባ በመጪው የስራ ዘመን አቅጣጫ ላይ ለመወያየት የዓዲስ አመት ጉባኤ ይጠራል፡፡ ይህን የምስጋና መግለጫ በአንድ የወታደር ጥቅስ መዝጋት እፈልጋለሁ፡፡
“በሰላምና እና በነጻነት ጊዜ የምንኖርባትን ሀገር በችግር ጊዜም ልንቆምላት ይገባናል"
መዓዛ አሸናፊ መንግስቱ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት
የዓመቱን የስራ ጊዜ መገባደድ አስመልክቶ ከጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት
ለዳኞች የተላከ የምስጋና መግለጫ
ሐምሌ 30 ቀን 2011 ዓ.ም
የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝደንት ሆኜ ከተሾምኩበት ከጥቅምት 22/2011 ዓ.ም ጀምሮ ዳኞቻችን በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት፣ ትጋት እና የሙያ ፍቅር ሃላፊነታቸውን በመወጣት ላይ መሆናችሁን ተገንዝቤአለሁ፡፡ ለዚህም ጠለቅ ያለ የዓመቱ ምስጋና ይገባችኋል፡፡
እኔና ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ የስራ ሃላፊነት ተቀብለን ወደ ጠ/ፍ/ቤት ከመጣንበት ጊዜ ጀምሮ በምናስበው መንገድ ሃላፊነታችንን እንድንወጣ ያደረጋችሁልን በጎ አቀባበል እና ድጋፍ የሚደነቅ ነው፡፡
እንደምትገነዘቡት የፍ/ቤታችን አዲስ አመራር የተቃኘው አዎንታዊ አመራር ወይንም Positive Leadership በሚባለው የአመራር አቅጣጫ ነው፡፡ ይህ አይነት አመራር በግልጽነት፣ በመተማመን፣ የጋራ ራዕይ በመፍጠር የሚያምን፣ በአዎንታዊ እና በበጎ ጎኖች ላይ የሚገነባ አበረታች የአመራር ዘዴ ነው:: በሌላ በኩል የምንከተለው የአመራር አቅጣጫ ቴክኒካዊ ብቻ ሳይሆን ፈር ቀዳጅ ይሆናል፡፡ ባለፉት ወራት ፍ/ቤቶቻችን ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ውጤታማ እና ቀልጣፋ እንዲሆኑ በርካታ የስልጠና፣ የሕዝብ ግንኙነት፣ የአስተዳደር ወዘተ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡
የጀመርነውን የፍ/ቤቶች ማሻሻያ ስራ የበለጠ ቅርጽ ለማስያዝ የሶስት ዓመት የስራ ዕቅድ ነድፈን ተወያይተን ተስማምተንባቸዋል፡፡ ዕቅዱን ለማስፈጸም መንግስት ከመደበልን በጀት በተጨማሪ የሀብት ማሰባሰብ ተግባር ቀጣዩ ስራችን ነው፡፡
ውድ ዳኞች
ከተጀመሩት የማሻሻያ /Reform/ ስራዎች ጥቂቱን ላስታውሳችሁ፡-
• ፌደራል ፍ/ቤት ራሱን የማስተዳደር አቅም እንዲጠነክር፣ በአባላቱ ጥንቅርም ሆነ በስልጣን ወሰን የተጠናከረ የዳኝነት አስተዳደር ጉባኤ እንዲቋቋም ረቂቅ የሕግ ማሻሻያ ተዘጋጅቷል፤
• ፍ/ቤቶቻችን የሚመለከቷቸው ጉዳዮች ፍሰት አስተዳደርን ውጤታማ ለማድረግ የፍ/ቤታችንን አደረጃጀት እና ስልጣን የሚወስነውን አዋጅ 25/88 እና ተከታታይ ማሻሻያዎችን በአዲስ መልክ ለማሻሻል የተጠቃለለ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፤
• ‘’FITH” (ፍትህ) በመባል ተሰይሞ በUSAID /አሜሪካን የልማት ድርጅት/ አጋርነት የሚከናወነው ፕሮጀክት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በዳኞች ስነምግባር ደንብ እና በዳኞች የስራ አፈጻጸም ምዘና ላይ ትኩረት በማድረግ በመስራት ላይ እንገኛለን፡፡ የሚዘጋጁት ደንቦች እና መመሪያዎች የሀገራችንን የቆየ የዳኝነት አስተዳደር እና ዓለምአቀፍ መመዘኛዎችን ቀምረው የሚዘጋጁ ሲሆኑ ተጠናቀው ወደ ስራ ሲተረጉሙ ለተቋማችን ጥንካሬ ከፍተኛ አስተዋፆ ያደርጋሉ፡፡
ውድ ዳኞች
እየተደረጉ ያሉት የሕግ ማሻሻያ ስራዎች በፍ/ቤቱ በተሰየመ የከፍተኛ የህግ ባለሞያዎች ቡድን የሚታገዝ ነው፡፡ ባለሙያዎቹ ከፍተኛ የሞያ ታማኝነት እና የአገልግሎት መንፈስ አሳይተዋል፡፡
ክቡራን ዳኞች
በምሳሌነት የተጠቀሱት እርምጃዎች ላቀድናቸው የፍ/ቤቱ የሪፎርም ስራዎች መሠረት የሚሆኑ ናቸው፡፡ በረቂቅ ህጎች /ደንቦች/ መመሪያዎች ላይ የዳኞችን አስተያየት የማሰባሰቡ ስራ ይቀጥላል፡፡ የተጠቀሱት የህግ ማዕቀፎች ከጸደቁ በኋላ አስፈላጊ ስልጠናዎች ተደርገው የሪፎርም ስራውን በሰፊው እናራምዳለን፡፡
ውድ ዳኞች
የዳኝነት ሃላፊነት ከባድ መሆኑን ሕዝቡ እንዲገነዘበው ማድረጉ አንዱ ሃላፊነታችን ነው፡፡ ሕዝቡ ከፍርድ ቤቶቻችን ሚዛናዊ ብቻ ሳይሆን የተቀላጠፈና መብት አክባሪ የፍትህ አገልግሎት ይጠብቃል፡፡ በአንጻሩ የጉዳዩች ፍሰት ብዛት፣ የአቅርቦት ውስንነት እና ሌሎች እጥረቶች ስራችንን ፈታኝ ያደርጉታል፡፡
የዳኝነት የስራ ጫና ለመቀነስ በቅርቡ ከ150 በላይ የረዳት ዳኞች ቅጥር በማከናወን ላይ እንገኛለን፣ በሂደት ግባችን እያንዳንዱ ዳኛ ማለትም 354ቱም ዳኞች ረዳቶች እንዲኖሯቸው ነው፡፡
በዚህ ዓመት ካከናወናቸው ስራዎች አንዱ 16 ተጨማሪ የጠ/ፍ/ቤት ዳኞች በፓርላማ መሾማቸው ነው፡፡ ከተሾሙት ዳኞች 40 በመቶ የሚጠጉት ሴቶች መሆናቸው እንደ ትልቅ ዜና መታየት አለበት ፡፡
ክቡራን ዳኞች
በተለይ በወንጀል ጉዳይ ከሌሎች የፍትህ አካላት ጋር መነጋገር የሚገቡን ጉዳዮች ስላሉ ²አብይ ኮሚቴ² በተባለው መድረክ ላይ ገንቢ ሚና በመጫወት ላይ ነን፡፡ በወንጀል ጉዳይ የተጠረጠሩ ሰዎች በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ የሚያደርጉ ዋና ጉዳዮች ተለይተው ችግሩን ለመፍታት እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው፡፡ ይሄ ለነገ የሚባል ስራ አይደለም፡፡
ውድ ዳኞች
ሃላፊነታችን የየዕለት የመዝገብ ስራ ሳይስተጓጎል እንዲከናወን ማድረግ ብቻ ሳይሆን የዳኝነት ዘርፍ እንደ ሶስተኛ የመንግስት አካል ሚናው ምን እንደሆነ ለሕዝብ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የመንግስት አካላት በአዲስ መልክ የማስገንዘብ ስራንም ይጨምራል፡፡ በዚህ ዓመት የፍ/ቤቱን በጀት በቀጥታ ለፓርላማ አቅርበን ማስወሰናችን አንደኛው የፍ/ቤቱ ተቋማዊ ነጻነት እርምጃ ማረጋገጫ ሆኖ ይታያል፡፡ በብሄራዊም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፍ/ቤታችን ገጽታ እያደገ ነው፡፡ በመሆኑም እንድናከናውናቸው የሚጠበቁ ዓላማዎች በርካቶች ናቸው፡፡
ውድ ዳኞች
ነጻ፣ ገለልተኛ፣ ቀልጣፋ እና ውጤታማ ፍ/ቤት በመገንባት ሀገራችን ወደ ዲሞክራሲ እና ልማት ለመሸጋገር አስተዋፆ ለማድረግ የታሪክ አጋጣሚ መፈጠሩ አስደሳች ነው፡፡ ለአንድ የሕግ ባለሞያ ከዚህ የተሻለውን የእርካታ እድል ሊፈጥር የሚችል ምን አጋጣሚ ይገኛል? በተባበረ መንፈስ ጠንክረን በመስራት ይሄንን እድል ለማሳካት እንችላለን፡፡
ውድ ዳኞች
ከዳኝነት የሚጠበቀውን ከፍ ያለ የሙያም ሆነ የጨዋነት/ (integrity) ደረጃ የማያሟሉ ዳኞች በስልጠና ወደ መስመር እንዲገቡ ጥረት ይደረጋል:: ከዚያ የሚሰፉ ችግሮችም በሕጋዊ ስርዓት የሚታዩ ይሆናል፡፡
ወድ ዳኞች
በመደበኛ ቀጠሮዎች ከሚታዩት መዝገቦች ሌላ ከ2009 ዓ.ም በፊት ተከፍተው እንደ ውዝፍ መዝገብ /Backlog/ የፈረጅናቸውን መዝገቦች ለመወሰን ከፍተኛ ትጋት አሳይታችኋል፡፡ በዚህ ረገድ በሶስቱም ፍ/ቤቶቻችን 7,663 መዝገቦች እልባት አግኝተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በእረፍት ጊዜአችሁ ቀሪ የዘገዩ መዝገቦችን ለመወሰን አብዛኞቻችሁ ፍቃደኞች መሆናቸሁ ሌላ የሚያስመሰግን ተግባር ነው፡፡
ወድ ዳኞች በመጨረሻም
በከፊል ስራ ላይ ብትሆኑም ከዛሬ ሐምሌ 30/2011 ዓ.ም ጀምሮ ፍ/ቤቶቻችን ዝግ በመሆናቸው መልካም የእረፍት እና የቤተሰብ ጊዜ እመኛለሁ፡፡ መስከረም ሲጠባ በመጪው የስራ ዘመን አቅጣጫ ላይ ለመወያየት የዓዲስ አመት ጉባኤ ይጠራል፡፡ ይህን የምስጋና መግለጫ በአንድ የወታደር ጥቅስ መዝጋት እፈልጋለሁ፡፡
“በሰላምና እና በነጻነት ጊዜ የምንኖርባትን ሀገር በችግር ጊዜም ልንቆምላት ይገባናል"
መዓዛ አሸናፊ መንግስቱ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት
........Rewrting ........:
ሙስሊም ወንድም እና እህቶች መልካም የአረፋ ዐዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ ተመኘው🙏🙏🙏🙏
ሙስሊም ወንድም እና እህቶች መልካም የአረፋ ዐዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ ተመኘው🙏🙏🙏🙏
ALE Law Society is the independent professional body for all law societies @lawsocieties @lawsocieties @lawsocieties @lawsocieties @lawsocieties @lawsocieties @lawsocieties @lawsocieties
We are the voice of all law societies, drive excellence in the profession and safeguard the rule of law.
We are the voice of all law societies, drive excellence in the profession and safeguard the rule of law.
Ale 🔴Thank you Andy ye Henu: for sending us ....
Second year first semester course
Second year first semester course
Vip Vip:
Please Ale oromia region honew oromigna lemyichilu ye hig temariwoch le training endet memezgeb endemichilu merega yiseten please?
Please Ale oromia region honew oromigna lemyichilu ye hig temariwoch le training endet memezgeb endemichilu merega yiseten please?