#Update
የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ ፀደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ።
ረቂቅ አዋጁ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።
ረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ክርክር ሲነሳበት እንደነበር ይታወቃል። በተለይ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማሕበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ረቂቅ አዋጁ ላይ የደመወዝ ገቢ ግብር መነሻ ተብሎ የተቀመጠው 2,000 ብር ወደ 8,324 ብር ከፍ እንዲል ፤ አጠቃላይ አዋጁ የኑሮ ውድነቱንና ጫናውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲታረም ሲወተውት ነበር።
ከ0 ጀምሮ 10% ፣ 15% ፣ 20% ፣ 25% ፣ 30% ፣ 35% ይቀጥል የነበርው የግብር ምጣኔም በረቂቅ አዋጁ 10% ከመሃል ወጥቶ ከ0 ጀምሮ ቀጥታ ባከፍተኛው 15% መጀመሩንም ታቃውሞ ነበር።
ሌላው 14,100 በላይ የሚያገኝ ሰው 35% ግብር ይከፍላል በሚለው ላይም ጥያቄ ተነስቶ ነበር።
በአሁኑ የኑሮ ውድነት ሰራተኛው በእያንዳንዱ ነገር በምግብ ዋጋ፣ በሚገዛው እቃ 15% ይጨምራል ይሄ በ35% ላይ ሲደመር 50% ይመጣል፤ 7% የጡረታ አለ ሲደመር 57% ከደመወዙ ላይ ይሄዳል በቀረችው 43% ልጆች ያስተምራል ፣ ምግብ ይበላል ፣ ልብስ ይገዛል ፣ ቤት ይከራያል ምንድነው የሚያደርገው ? የሚል የሰራተኛውን ጥያቄ በማንሳት ረቂቁ እንዲታረም ጠይቆ ነበር።
ኮንፌዴሬሽኑ ፤ " መኖር ከማይችል እና በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አይሰብሰብም " ብሎም የነበረ ሲሆነ " እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብና ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም ግን መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም " በማለት ረቂቁ እንዲታረም ብርቱ ጥያቄ አቅርቦ ነበር።
ሌሎችም አካላት ሰፊ ክርክር ሲያደርጉበት የነበረው ረቂቅ አዋጅ በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአብላጭ ድምጽ ፀድቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ ፀደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ።
ረቂቅ አዋጁ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።
ረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ክርክር ሲነሳበት እንደነበር ይታወቃል። በተለይ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማሕበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ረቂቅ አዋጁ ላይ የደመወዝ ገቢ ግብር መነሻ ተብሎ የተቀመጠው 2,000 ብር ወደ 8,324 ብር ከፍ እንዲል ፤ አጠቃላይ አዋጁ የኑሮ ውድነቱንና ጫናውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲታረም ሲወተውት ነበር።
ከ0 ጀምሮ 10% ፣ 15% ፣ 20% ፣ 25% ፣ 30% ፣ 35% ይቀጥል የነበርው የግብር ምጣኔም በረቂቅ አዋጁ 10% ከመሃል ወጥቶ ከ0 ጀምሮ ቀጥታ ባከፍተኛው 15% መጀመሩንም ታቃውሞ ነበር።
ሌላው 14,100 በላይ የሚያገኝ ሰው 35% ግብር ይከፍላል በሚለው ላይም ጥያቄ ተነስቶ ነበር።
በአሁኑ የኑሮ ውድነት ሰራተኛው በእያንዳንዱ ነገር በምግብ ዋጋ፣ በሚገዛው እቃ 15% ይጨምራል ይሄ በ35% ላይ ሲደመር 50% ይመጣል፤ 7% የጡረታ አለ ሲደመር 57% ከደመወዙ ላይ ይሄዳል በቀረችው 43% ልጆች ያስተምራል ፣ ምግብ ይበላል ፣ ልብስ ይገዛል ፣ ቤት ይከራያል ምንድነው የሚያደርገው ? የሚል የሰራተኛውን ጥያቄ በማንሳት ረቂቁ እንዲታረም ጠይቆ ነበር።
ኮንፌዴሬሽኑ ፤ " መኖር ከማይችል እና በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አይሰብሰብም " ብሎም የነበረ ሲሆነ " እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብና ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም ግን መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም " በማለት ረቂቁ እንዲታረም ብርቱ ጥያቄ አቅርቦ ነበር።
ሌሎችም አካላት ሰፊ ክርክር ሲያደርጉበት የነበረው ረቂቅ አዋጅ በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአብላጭ ድምጽ ፀድቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
❤27👎8💔1