አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.83K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#ለቲክቶከሮች እና #የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች #አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ!
ጤና ይስጥልኝ! ሚኪያስ መላክ ነኝ፣ ጠበቃ እና የህግ አማካሪ።
በማህበራዊ ሚዲያ በተለይም በቲክቶክ ላይ ንቁ ተሳትፎ ለምታደርጉ ሁሉ፣ አሁን የምሰጣችሁን ማስጠንቀቂያ በደንብ እንድትገነዘቡት እጠይቃለሁ። የቅርብ ጊዜዎቹ #ቲክቶከሮች #ጃኒ በትክክለኛው ስሟ ስመኝ ገብሩ እና የሌሎችን ቲክቶከር ጉዳዮችን ስንታዘብ ያየነው እና የተመለከትናቸው ዋነኛ ምሳሌዎች ናቸው። ሁሉም በፖሊስ ተይዘው ወደ ጣቢያ መወሰዳቸው፣ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች የሕግ ተጠያቂነትን በሚመለከት ሊገነዘቡት የሚገባ ትልቅ ትምህርት ነው። የእናንተ ተፅዕኖ ፈጣሪነት የራሱ የሆነ ኃላፊነት አለበት።
ጥንቃቄ አይለያችሁ!
አንድ ስኬታማ ሰው በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚኖረው እንቅስቃሴ የሚያስከትለው ጉዳት የጎላ ነው። አንድ ተራ ሰው በሰራው ስህተት ጉዳዩ ተራ ሆኖ ሊቀር ቢችልም፣ እንደ ጃኒ ያሉ ብዙ ተከታይ እና አድማጭ ያላችሁ ሰዎች ግን የሚፈጠረው መዘዝ እጅግ ትልቅ ነው። ተጠንቀቁ!
በተለይ "የአፍ ወለምታ" እና መሰል ንግግሮች የሚያስከትሉትን የህግ ተጠያቂነት አቅልላችሁ እንዳትመለከቱ። ያላሰባችሁት ንግግር ከባድ የህግ መዘዝ ሊያስከትል ይችላል።
የሕግ አማካሪ ወይም ቋሚ ጠበቃ ይኑራችሁ!
ይህ በጣም አስፈላጊ ነገር ነው። ስራችሁን እና ንግግራችሁን ከህግ አንፃር ሳንሱር የሚያደርግ እና ከህዝብ ጋር ከመድረሱ በፊት አስፈላጊውን እርምጃ የሚወስድ የህግ አማካሪ ያስፈልጋችኋል። ይህ ከብዙ ችግሮች ሊታደጋችሁ ይችላል። የጃኒ እና በእስር ላይ የሚገኙ ቲክቶከሮች እና ጉዳዮች ይህንን ፍላጎት በግልጽ ያሳያሉ።
#አላውቅም"፣ #ቀልድ ነው"፣ "#እድሜዬ አልደረሰም" - እነዚህ የህግ መከላከያ ሊሆኑ አይችሉም!
ምንም እንኳን ታሳቢ የሚደረጉ ሁኔታዎች ቢኖሩም በወንጀል ሕጉ መሰረት ጉዳዩ የሚታየው በህጉ ላይ በተመለከቱት መደበኛ ድንጋጌዎች መሰረት ነው። ስለዚህ፣ እድሜም ሆነ የትምህርት ደረጃ ለፈጸሙት ወንጀል መከለያ ሊሆን እንደማይችል ልብ ይበሉ።
ማህበረሰብን/ህዝብን/ብሄርን ማጥላላት ወንጀል ነው፣ ያስጠይቃልም!
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስትለጥፉ ወይም ስትናገሩ ዘርን፣ ሀይማኖትን፣ ብሄርን ወይም ማንኛውንም የማህበረሰብ ክፍል የሚያንቋሽሽ ወይም ጥላቻን የሚያነሳሳ ነገር ከመናገር ተቆጠቡ። ይህ በህግ የሚያስቀጣ ወንጀል መሆኑን አትርሱ።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምታደርጉትን እንቅስቃሴ በጥንቃቄ እንድታደርጉት አሳስባለሁ። ህጉን ማወቅ ከችግር ያድናል!
Mikias Melak AleHig
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ