የገንዘብ_ሚኒስቴር_መመሪያ_ቁጥር_1063_2017.pdf
5.8 MB
#ታክስ #ኦዲት
የገንዘብ ሚኒስቴር፥ የታክስ ኦዲት የሚከናወንበትን ሥርዓት እና የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የሚወጣበትን አኳኋን ለመወሰን መመሪያ አውጥቷል።
መመሪያው ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ ስራ ላይ ውሏል።
መመሪያው ስለ አጠቃላይ ኦዲት ምን ይላል ?
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ ኦዲት የሚያከናውነው ፦
- በስጋት ግምገማ ወቅት ታክስ ከፋዩ በህግ በተደነገገው መሰረት የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ገቢውን የማስታወቅ እና ታክስ የመክፈል ግዴታውን ያልተወጣ መሆኑ ሲታወቅ እና ይህም ሁኔታ የተለያዩ ታክሶችን የሚመለከት ሲሆን፤
- ሌላ አይነት ኦዲት በመደረግ ላይ ባለበት ጊዜ የተገኙ ታክስ ከፋዩ የፈጸማቸው ተገቢ ያልሆኑ አድራጎቶች ኦዲቱ በማይሸፍናቸው በሌሎች ታክሶች ላይ ጭምር ውጤት ያላቸው መሆኑ ሲታወቅ፤
- ታክስ ከፋዩ ኦዲት እንዲደርግ ሲጠየቅ እና በታክስ ባለስልጣኑ አጠቃላይ ኦዲት አስፈላጊ መሆኑ ሲታመንበት፤
- አግባብነት ባላቸው በሌሎች የታክስ ህጎች በተገለጹ ሌሎች ምክንያቶች፤
- ታክስ ከፋዩ በጭብጥ ኦዲት ተደርጎ አከራካሪ ከሆነ እና በቅሬታ ጽ/ቤት በኩል አጠቃላይ ኦዲት እንዲደረግ ትዕዛዝ ሲሰጥ፤ ... ነው ይላል።
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ አዲት በሚያከናውንበት ጊዜ ፦
° ተገቢ ያልሆነ የሂሳብ ስሌት፣ ግድፈት፤
° ገቢን ማሳነስ፤
° ተገቢ ያልሆነ የታክስ አሰያየም
° በታክስ ማስታወቂያ ወይም ስሌት ረገድ የተፈጸመ ሌላ ማናቸውም ጥፋት ያለመኖሩን ለማረጋገጥ፤ ሁሉንም ወይም የተወሰኑትን የታክስ አይነቶች በሚመለከት ዝርዝር እና ጥልቀት ያለው ምርመራ ማድረግ እንዳለበት መመሪያው ላይ ሰፍሯል።
ይህ የማጣራት ተግባር አግባብነት እስካለው ድረስ የህግ ድንጋጌዎችን ተከትሎ መፈጸም እንዳለበትም ይገልጻል።
(ሙሉ መመሪያው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የገንዘብ ሚኒስቴር፥ የታክስ ኦዲት የሚከናወንበትን ሥርዓት እና የታክስ ስሌት ማስታወቂያ የሚወጣበትን አኳኋን ለመወሰን መመሪያ አውጥቷል።
መመሪያው ከትላንትና በስቲያ ጀምሮ ስራ ላይ ውሏል።
መመሪያው ስለ አጠቃላይ ኦዲት ምን ይላል ?
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ ኦዲት የሚያከናውነው ፦
- በስጋት ግምገማ ወቅት ታክስ ከፋዩ በህግ በተደነገገው መሰረት የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ገቢውን የማስታወቅ እና ታክስ የመክፈል ግዴታውን ያልተወጣ መሆኑ ሲታወቅ እና ይህም ሁኔታ የተለያዩ ታክሶችን የሚመለከት ሲሆን፤
- ሌላ አይነት ኦዲት በመደረግ ላይ ባለበት ጊዜ የተገኙ ታክስ ከፋዩ የፈጸማቸው ተገቢ ያልሆኑ አድራጎቶች ኦዲቱ በማይሸፍናቸው በሌሎች ታክሶች ላይ ጭምር ውጤት ያላቸው መሆኑ ሲታወቅ፤
- ታክስ ከፋዩ ኦዲት እንዲደርግ ሲጠየቅ እና በታክስ ባለስልጣኑ አጠቃላይ ኦዲት አስፈላጊ መሆኑ ሲታመንበት፤
- አግባብነት ባላቸው በሌሎች የታክስ ህጎች በተገለጹ ሌሎች ምክንያቶች፤
- ታክስ ከፋዩ በጭብጥ ኦዲት ተደርጎ አከራካሪ ከሆነ እና በቅሬታ ጽ/ቤት በኩል አጠቃላይ ኦዲት እንዲደረግ ትዕዛዝ ሲሰጥ፤ ... ነው ይላል።
የታክስ ባለስልጣን አጠቃላይ አዲት በሚያከናውንበት ጊዜ ፦
° ተገቢ ያልሆነ የሂሳብ ስሌት፣ ግድፈት፤
° ገቢን ማሳነስ፤
° ተገቢ ያልሆነ የታክስ አሰያየም
° በታክስ ማስታወቂያ ወይም ስሌት ረገድ የተፈጸመ ሌላ ማናቸውም ጥፋት ያለመኖሩን ለማረጋገጥ፤ ሁሉንም ወይም የተወሰኑትን የታክስ አይነቶች በሚመለከት ዝርዝር እና ጥልቀት ያለው ምርመራ ማድረግ እንዳለበት መመሪያው ላይ ሰፍሯል።
ይህ የማጣራት ተግባር አግባብነት እስካለው ድረስ የህግ ድንጋጌዎችን ተከትሎ መፈጸም እንዳለበትም ይገልጻል።
(ሙሉ መመሪያው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia