አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
17.09.14 Revised Notice - For Law Exit Exam Candidates.docx
27.5 KB
Share '17.09.14 Revised Notice - For Law Exit Exam Candidates.docx'
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና
ለመፈተን በዝግጅት ላይ ለምትገኙ ተፈታኞች


የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና አስተዳደር በ 17 / 09 / 2014 ዓ.ም በተገለፀው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ዋና እና ዝርዝር ሂደቱ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ በዚህ መሰረት
የተፈታኞች ምዝገባ መረጃ -
የተፈታኞች ምዝገባ ቀናት ከግንቦት 18 - 26 ቀን 2014 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ ሰባት የስራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡
መደበኛ ተፈታኞች በተመሩበት ዩኒቨርሲቲ የሚመዘገቡ እና የሚፈተኑ በመሆኑ መረጃቸውን በተመለከተ ዩኒቨርሲቲው ኃላፊነት ይወስዳል፣
የቀን መደበኛ ያልሆኑ፣ የግል እና ድጋሚ የሚፈተኑ እና ሌሎች ተፈታኞች በተማሩበት ዩኒቨርሲቲ ብቻ ይመዘገባሉ፣ ኤግዘምሽን ማድረግ የሚፈልጉትን ፈተና መረጃ ይሰጣሉ፣ የሚፈተኑበትን ዩኒቨርሲቲ ይመርጣሉ፣
ተፈታኞች የመፈተኛ ጣቢያ ሲመርጡ ከታች በተጨማሪ ማብራሪያው ላይ የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ፈተና በሚሰጥበት ወቅት ሊፈተኑበት የሚችሉበትን እርግጠኛ የሆኑበት ቦታ መምረጥ ይገባል፣
በልዩ ሁኔታ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተምረውና ተፈትነው የነበረ፣ በድጋሚ መፈተን የሚፈልጉ ከሆነ በትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በማመልከት፣ ክፍያ በመፈፀም እና ምርጫቸውን በማሳወቅ ይፈተናሉ፣
አንድ ተፈታኝ በተፈታኝነት ለመመዝገብ ብር 850.00 (ስምንት መቶ ሃምሳ ብር) በዩኒቨርሲቲው የባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ ማድረግ ይጠበቅበታል፣ ከዩኒቨርሲቲው ሂሳብ ቁጥር ውጪ ገቢ ማድረግ ተቀባይነት የለውም፣ ለፈተናም አይቀመጥም፣

የፈተና አስፈጻሚዎች እና ተፈታኞች ገለፃ (ኦረንቴሽን) መረጃ
አረንቴሽን ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ፈተና በሚሰጥበት ዩኒቨርሲቲ ብቻ ይሆናል፡፡
ኦረንቴሽን ለመውሰድ ተፈታኙ ስሙ በመፈተኛ ጣቢያ እንዲፈተን የተላለፈ እና የምዝገባ ቁጥር ያለው መሆን አለበት፣
ተፈታኙ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ እና ሌሎች የፈተና አሰጣጥ ሂደት የሚፈቅዳቸውን ሁኔታዎች ማሟላት አለበት፣
ዓይነ ስውራን ተፈታኞች ከኦረንቴሽን በፊት ፈተናውን የሚያነብላቸው አንባቢ በሚፈተኑበት ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ፈተና ጉዳይ አስተባባሪ በማመልከት በደብዳቤ እንዲገለፅላቸው ማድረግ ይጠበቃል፣ ወይም አንባቢ እንዲመደብላቸው ማመልከት ይጠበቅባቸዋል፣
ተፈታኞች የፈተና ጣቢያ ለውጥ የሚፈልጉ ከሆነ በምዝገባ ወቅት ሊያመለክቱ ይገባል፣ ሆኖም ስማቸው ከተላለፈ በኋላ የፈተና ጣቢያ ለውጥ የሚጠይቁ ወይም በፈተና መስጫ ወቅት በፈተና ጣቢያው ቢገኙ ለመፈተን የማይፈቀድላቸው በመሆኑ የፈተና ደንብ መተላለፍ እንደፈጸሙ ይቆጠራል፣

ለተፈታኞች ፈተና የሚሰጥበት ቀናት
ፈተና የሚሰጥበት ቀናት ከሰኔ 21 - 24 ቀን 2014 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ አራት የስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 - 6፡00 ሰዓት ብቻ ይሆናል፡፡
ተፈታኞች ፈተና በሚሰጥበት ቀን ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ፣ ስክርቢቶ እና የተፈቀዱ ማጣቀሻዎችን በመያዝ ማለዳ ከ 1፡00 - 1፡30 ሰዓት ፈተና በሚሰጥበት ግቢ መድረስ አለባቸው፣
ያልተፈቀዱ ማንኛውንም ነገር ይዞ መምጣት አይፈቀድም፣ ይዞ የተገኘ ተፈታኝ የፈተና ደንብ መተላለፍ እንደፈፀመ ተቆጥሮ የፈተናው ውጤት በከፍል ወይም በሙሉ የሚሰረዝበት ይሆናል፣
ዓይነስውራን ተፈታኞች ከላይ የተገለፁት እንደተጠበቁ ሆኖ ፈተናውን የሚያነብላቸው አንባቢ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፣ ወይም አንባቢ ባለሙያ ይመደብላቸዋል፣
የፈተና አሰጣጥ ከተጀመረበት ሰዓት ጀምሮ ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ግቢም ሆነ ወደመፈተኛ ክፍል መግባት አይፈቀድለትም፣
ዝርዝር ነጥቦች
ተፈታኞች ከምዝገባ እና ከፈተና አሰጣጥ ሂደት ጋር በተያያዘ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ተጨማሪ ግንዛቤ እንዲጨብጡ እናሳስባለን፡፡
ተፈታኞች ለምዝገባ እና ለመፈተን ሲመጡ በተጨማሪ ግንዛቤ የሚያስፈልጋቸው ሁኔታዎች -
በሚማርበት ዩኒቨርሲቲ ፈተናውን ለመውሰድ የተፈቀደለት እና የተመዘገበ መሆን አለበት፣
ለምዝገባ የተወሰነውን ብር 850.00 (ስምንት መቶ ሃምሳ ብር) ክፍያ በዩኒቨርሲቲው ባንክ ሂሳብ ቁጥር ብቻ ገቢ ያደረገ መሆን አለበት፣ ከዩኒቨርሲቲው ባንክ ሂሳብ ቁጥር ውጭ በሌላ ተቋም ገቢ በማድረግ ደረሰኝ ማቅረብ ወይም ከምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ ውጪ ለዩኒቨርሲቲው ገቢ በማድረግ ደረሰኝ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም፣ ፈተና ላይ ለመቀመጥም አያስችልም፣
ለመፈተን የተመዘገበ ስለመሆኑ በዩኒቨርሲቲው በኩል ስሙ ለኢንስቲትዩቱ የተላከ መሆን አለበት፣ በምዝገባ ጊዜ ገደብ ውስጥ ብቻ ስሙ በዩኒቨርሲቲው መዝጋቢነት እና በኢንስቲትዩ ማረጋገጫ ያልተላለፈ ተመዝጋቢ እንዲሁም የምዝገባ ቁጥር ያልተሰጠው ተፈታኝ እንዳልተመዘገበ ተቆጥሮ ፈተና ላይ መቀመጥ አይችልም፣
ከላይ በተገለፀው የምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ ብቻ የሚፈተንበትን ዩኒቨርሲቲ ምርጫ እንዲሁም በኤግዘምሽን ምክንያት የማይፈተናቸው ፈተናዎች ካሉ ማሳወቅ አለበት፣ ከምዘገባ ጊዜ ሰሌዳው ውጭ የሚቀርብ ኤግዘምሽን መረጃ እና የዩኒቨርሲቲ ለውጥ ተቀባይነት የለውም፣
በምዝገባ ወቅት የሚፈተንበትን ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ሲመርጥ ከተማረበት ዩኒቨርሲቲ ርቆ የሚገኝ ከሆነ ህጋዊ ምክንያት (የመስሪያ ቤት መታወቂያ፣ የነዋሪነት መታወቂያ፣ አስገዳጅ የስራ ወይም የፀጥታ ሁኔታ መረጃ፣ የሆስፒታል መረጃ፣ ሌሎች) ማሳየት / ማቅረብ አለበት፣ ጉዳዩም ለኢንስቲትዩቱ በደብዳቤ መድረስ ይገባዋል፣ በፈተና አሰጣጥ ወቅት የተፈታኞች መረጃ ማጣራት ሲደረግ ስህተት ሆኖ ከተገኘ ፈተናው ይሰረዝበታል፣
ከተማረበት ዩኒቨርሲቲ ውጭ ተመዝግቦ የተገኘ ተፈታኝ ወይም ያላስተማረውን ተማሪ መዝግቦ መረጃ ያስተላለፈ ዩኒቨርሲቲ የምዝገባው መረጃ ውድቅ የሚደረግበት ሲሆን ኃላፊነቱን ተፈታኙ / ዩኒቨርሲቲው የሚወስድ ይሆናል፣ ፈተና ላይ ለመቀመጥም አያስችልም፣
በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ዩኒቨርሲቲዎች የተመዝጋቢዎች ዝርዝር እና የተሰበሰበ ገንዘብ ገቢ ካላደረጉ ምንም ተፈታኝ እንዳልመዘገቡ ይቆጠራል / ኃላፊነት ይወስዳሉ፣
የፈተና አሰጣጥ ገለፃ (ኦረንቴሽን) ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ሲሆን ፈተና የሚሰጠው ከሰኔ 21 - 24 ቀን 2014 ዓ.ም ይሆናል፣ በመሆኑም በዚህ ሳምንት ተፈታኞች ማንነትን የሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ፣ እስክሪቢቶ እና የተፈቀዱ ማጣቀሻዎችን ብቻ ይዞ መገኘት ይገባቸዋል፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ከተፈቀዱ ማጣቀሻዎች ውጪ ማንኛውንም ዓይነት ፅሑፍ ያለበት ወረቀትም ሆነ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ፣ የእጅ ሰዓት፣ ተፈታኙ ከስራ መደቡ አንፃር ህጋዊ የሆነ ሆኖም በፈተና ጣቢያ የማይፈቀድ ነገር ይዞ መገኘት እንዲሁም ሌሎች በፈተና አሰጣጥ ወቅት የማይፈቀዱ ነገሮችን ይዞ መገኘት አይቻልም፣ በአራተኛው የፈተና ቀናት ማንነትን ከሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ እና ከእስክሪቢቶ በስተቀር ምንም ነገር ይዞ መምጣት አይፈቀድም፡፡ በቅድመ ፈተና ፍተሻ ወቅት በፈተና መስጫ ግቢ እና ክፍል ውስጥ ይህ ሆኖ ከተገኘ ሙሉ የፈተና ውጤት ይሰረዛል፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ምንም ዓይነት ነገር መቀያየር እና መዋዋስ የማይቻል በመሆኑ ሁሉም ተፈታኝ በግሉ የሚጠቀምበትን ነገር ይዞ መገኘት ይገባዋል፣
የፈተና አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በተለያየ ህጋዊም ሆነ ህጋዊ ባልሆነ ምክንያት ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ አርፍዶ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተና ግቢም ሆነ ክፍል ውስጥ መግባት አይፈቀድም፣ በመሆኑም ለፍተሻ ሂደት እና ለቅድመ ዝግጅት ሲባል ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከሚሰጥበት ሰዓት አንድ ሰዓት ቀደም ብሎ ወደ ፈተና ጣቢያ ጊቢ እንዲደርስ ይመከራል፣
ውጤትን በተመለከተ ቅሬታ ካለ ወደፊት በሚገለፀው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በአካል በመቅረብ ወይም በዩኒቨርሲቲ በኩል በደብዳቤ ለኢንስቲትዩቱ የሚቀርብ ይሆናል፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Exit Exam
ፈተናው የሚሰጥበት ቀናት ከሰኔ 21 - 24 ቀን 2014 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ አራት የስራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 - 6፡00 ሰዓት ብቻ ይሆናል፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
የመብራት ሃይል ሰራተኛው ፍቅረኛውን ለማግኘት መብራት በተደጋጋሚ ሲያቋርጥ ተደረሰበት!

የሴት ጓደኛውን በድብቅ ለማግኘት ሲል በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያቋርጠው የመብራት ኃይል ሰራተኛ ድርጊቱ ተደረሰበት።
በህንድ ምስራቃዊ ቢሃር ፑርኒያ ወረዳ በምትገኛው የጋኔሽፑር አነስተኛ መንደር፣ አመሻሽ ላይ ጀምበር ከጠለቀች ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የሚከሰተው ተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ነዋሪዎችን ለምንታት ፈትኗል። በመብራት ሃይል መስሪያ ቤቱ ምንም አይነት የኃይል ችግር አለመኖሩን እና በአጎራባች መንደሮች ውስጥ ተመሳሳይ ክስተት አለማጋጠሙ የችግሩ መንስኤ ምን እንደሆነ ለማወቅ እንዳይቻል አድርጓል።
በሁኔታው የተበሳጩት የመንደሩ ነዋሪዎች የኃይል የመቆራረጥ ችግር የተከሰተበትን ጊዜ በትኩረት መከታተል ይጀምራሉ።ሁልጊዜ አመሻሽ ሊጨላልም ሲል በመንደሩ መብራት እንደሚጠፋ ይረዳሉ።
መብራት የሚጠፋው ከ2 እስከ 3 ሰዓት ሲሆን በስተመጨረሻ ድርጊቱን የሚፈፅመው ግለሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ሰራተኛ እንደሆነ ይደረስበታል።ግለሰቡ ይህንን አሻጥር ፍቅረኛውን ለማግኘት እንደሚፈፅም አምኖ በመቀበሉ ክስ ባይመሰረትበትም በመንደሩ ነዋሪዎች ድብደባ ተፈፅሞበታል።
ስለ ሚስጥራዊው የፍቅር ግንኙነት ያወቁ የመንደሩ ሽማግሌዎች ሁለቱ ፍቅረኛሞች እንዲጋቡ በማስገደዳቸው የመንደሩ ምክር ቤት አባላት በተገኙበት ጋብቻ ፈፅመዋል።
>ዳጉ ጆርናል
#አለ_ህግ
https://t.me/lawsocieties
New at Commercial Bank of Ethiopia(Call for Written Exam )

🔰 Position: for Legal Trainee

🔰 ሙሉ ዝርዝሩን ለመመልከት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
👇 👇
👉Read Here:- https://bit.ly/3lBopwU
#Moot_Court

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አዘጋጅነት ላለፉት 4 ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲካሄድ የቆየው 2ኛው ሀገር አቀፍ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የምስለ-ችሎት (Moot Court) ውድድር ግንቦት 20/ 2014 ዓ.ም. አዲስ አበባ በተካሄደው የፍጻሜ ዝግጅት ፍፃሜውን አግኝቷል።

በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶች ዙርያ ያተኮረው የዘንድሮው ውድድር ፦

➡️ በአዲስ አበባ፣
➡️ አዳማ፣
➡️ ሀዋሳ፣
➡️ ሆሳዕና፣
➡️ ሚዛን፣
➡️ ጋምቤላ፣
➡️ አሶሳ፣
➡️ ሰመራ፣
➡️ ሐረር፣
➡️ ድሬዳዋ፣
➡️ ጅግጅጋ እና ጎንደር ከተሞች የተካሄዱ ሲሆን በ10 ክልሎች እና 2 ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ 63 የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና 130 ተወዳዳሪ ተማሪዎች ተሳትፈውበታል፡፡

በክልላዊ የቃል ክርክር ውድድሮች 1ኛ እና 2ኛ የወጡ 24 ተወዳዳሪ ቡድኖች የጽሑፍ ክርክራቸውን ለኢሰመኮ በመላክ የተወዳደሩ ሲሆን፣ ከእነዚህ መካከል ከፍተኛ ነጥብ ያስመዘገቡ 8 ቡድኖች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከግንቦት 15-20 ቀን 2014 ዓ.ም በሩብ ፍፃሜ እና ግማሽ ፍፃሜ ዙሮች ተወዳድረዋል።
ከነዚህም ውስጥ ከወላይታ ከተማ፣ ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት የመጡት ተማሪ ሳያት ደሳለኝ እና ተማሪ አስቻለው ማቴዎስ እንዲሁም፣ ከጎንደር ከተማ፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኮሙኒቲ ት/ቤት የመጡት ተማሪ ብሌን ሙሉጌታ እና ተማሪ አማኑኤል ዋሴ ግማሽ ፍፃሜ አሸናፊዎች በመሆን ለፍፃሜ ውድድር መቅረብ ችለዋል።
ዛሬ በተደረጉው ውድድር ተማሪ ብሌን ሙሉጌታ እና ተማሪ አማኑኤል ዋሴ #ከጎንደር_ዩኒቨርሲቲ_ኮሙኒቲ_ትምህት_ቤት የ2ኛው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የምስለ-ችሎት ውድድር አሸናፊ ሆነዋል፡፡
(ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ እና ፎቶዎች ከላይ ተያይዟል)
#EHRC
#tikvahethiopia @lawsocieties
ሁለት ነገር!
1. ከብዙ ጥረት በኋላ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት የከፈተ በመሆኑ እንኳን ደስ ያለን!

2. የሕግ ዲግሪ በኤክስቴንሽን መማር ለምትፈልጉ ሁሉ እነሆ እድሉ ተመቻችቷል፤ ጊዜው ሳያልፍ ይመዝገቡ! ዝርዘሩን ከተለጠፈው ማስታዎቂያ ማግኘት ይችላሉ!
በካሊድ ከበደ
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
#NIB International Bank#

▪️1 - IT Security Officer
▪️2 - Senior Research and Development Officer
▪️3 - Manager, Legal Advisory and Research Devision
▪️4 - Driver I
▪️5 - Motorcyclist
▪️Find More Details Here
👇👇👇👇👇
https://bit.ly/38Hed2d
Or
https://bit.ly/3itGSsV

▪️Deadline - June 06/2022