አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
<<<<<<<<<<<<#ፍትሃዊው_ዳኛ!!>>>>>>>>>>

#አሜሪካ ውስጥ የ15 አመት ታዳጊ ሱቅ ሲሰርቅ ከዛም ሊያመልጥ ሲል አንዱን መደርደሪያ ሰበረ ይህ ፍትሃዊ ዳኛ የሰጠው ፍርድ!!

ዳኛው የክስተቱን ዝርዝር ሁኔታ ከሰማ በኋላ ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው።
"በእርግጥ የሆነ ነገር ሰረቅክ? ዳቦና አይብ ሰርቀህ መደርደሪያ ሰባበርክ?"

ልጁም አንገቱን ደፍቶ በአፍረት መለሰ፡-
አዎ.

ዳኛ፡ "ለምን ሰረቅክ?"

ታዲጊው ልጅ: በጣም ፈልጌው ነው

ዳኛ፡ ከመስረቅ ይልቅ መግዛት አልቻልክም ነበር?

ልጅ፡ ምንም ገንዘብ አልነበረኝም።

ዳኛ፡ ወላጆችህን ገንዘብ ልትጠይቅ ትችላለህ።

ልጅ፡ እኔ ያለኝ፣ አልጋ ላይ የተኛች እና ስራ የሌላት የታመመች እናቴን ብቻ ነው... ለሷ ስል ዳቦና አይብ ሰርቄያለሁ።

ዳኛ፡ እና አንተ... ምን እየሰራህ ነው? ሥራ የለህም?

ልጅ፡- የመኪና ማጠቢያ ሆኜ እሰራ ነበር። እናቴን ለመርዳት አንድ ቀን ዕረፍት ወሰድኩ፣ ለዚህም ነው ያባረሩኝ።

ከልጁ ጋር የነበረው ውይይት ካለቀ በኋላ ዳኛው ፍርዱን አስታወቁ፡-
“ሌብነት በተለይም #ዳቦ መስረቅ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው።
ለዚህ የስርቆት ወንጀል ሁላችንም ተጠያቂ ነን። ለዚህ የስርቆት ወንጀል ዛሬ እኔ ራሴን ጨምሮ እዚህ ክፍል ውስጥ የተገኘ ሁሉ ተጠያቂ ነው” አለ።

በመቀጠልም ሁሉም ተሰብሳቢዎች አሥር ዶላር ይቀጣሉ እና ማንም ሰው #10_ዶላር ሳይከፍል ከአዳራሹ አይወጣም.

ዳኛው ከኪሱ የ10 ዶላር ቢል አንሥቶ እስክሪብቶ አወጣና እንዲህ ብሎ መጻፍ ጀመረ።

"በተጨማሪም የተራበውን ልጅ ለፖሊስ ያደረሰው ሱቅ ባለቤት 1,000 ዶላር እንዲቀጣ አዝዣለሁ እና ቅጣቱ በአንድ ሰዓት ውስጥ ካልተከፈለ ሱቁ ተዘግቶ ይቆያል."

በአዳራሹ ውስጥ የነበሩት ሁሉ ለልጁ ይቅርታ ጠይቀው ሙሉ ገንዘቡን ሰጡት። ዳኛው እንባውን ለመደበቅ እየሞከረ ከችሎቱ ወጣ።

ተሰብሳቢዎቹ የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ ዓይናቸው በእንባ ተሞላ።

ዳኛው አክለውም “አንድ ሰው ዳቦ ሲሰርቅ ከተያዘ መላው የዚች ሀገር ህዝብና ህብረተሰብ ሊያፍር ይገባል” ሲሉም አክለዋል።
Source:- FB
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
#ፍትሃዊው_ዳኛ❗️❗️
#አሜሪካ ውስጥ የ15 አመት ታዳጊ ሱቅ ሲሰርቅ ከዛም ሊያመልጥ ሲል አንዱን መደርደሪያ ሰበረ ይህ ፍትሃዊ ዳኛ የሰጠው ፍርድ!! #አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Notice - For Law Exit Exam Candidates.docx
22 KB
Share 'Notice - For Law Exit Exam Candidates.docx'
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
የቅድመ ዝግጅት ማስታወቂያ

የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና ለመፈተን በዝግጅት ላይ ለምትገኙ ተፈታኞች (Exit Exam)

የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና ቀደም ሲል በተገለፀው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከግንቦት 29 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2014 ዓ.ም ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በመሰራት ላይ እንገኛለን፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የተፈታኞች ምዝገባ አንዱ እና ዋንኛው የቅድመ ፈተና አሰጣጥ ዝግጅት ተግባር ሲሆን ተፈታኞች ከታች የተዘረዘሩትን ነጥቦች ትኩረት በመስጠት ግንዛቤ እንዲጨብጡ እናሳስባለን፡፡
የምዝገባ ቀናት ማስታወቂያ - የተፈታኞች የምዝገባ ቀናት ከጥቂት ቀናት በኋላ ሲወሰን ለሁሉም አስፈታኝ ዩኒቨርሲቲዎች በደብዳቤ እና ለተፈታኞች “ አለ ” በሚለው የቴሌግራም ቻናል ይፋ ይደረጋል፡፡

የምዝገባ ቀናት ጊዜ ሰሌዳ ቆይታ - ከተፈታኞች ምዝገባ መጠናቀቅ በኋላ የፈተና ህትመት የሚካሄድበት ወቅት በመሆኑ እና ፈተናውን በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ለመስጠት ያለው ጊዜ አነስተኛ በመሆኑ የተፈታኞች ምዝገባ ቀናት ቆይታ የተፈታኞች ምዝገባ መጀመሩ በደብዳቤ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ሰባት የስራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡

ተፈታኞች ለምዝገባ እና ለመፈተን ሲመጡ በተጨማሪ ግንዛቤ የሚያስፈልጋቸው ሁኔታዎች -

በሚማርበት ዩኒቨርሲቲ ፈተናውን ለመውሰድ የተፈቀደለት እና የተመዘገበ መሆን አለበት፣
ለምዝገባ የተወሰነውን ክፍያ በዩኒቨርሲቲው ባንክ ሂሳብ ቁጥር ብቻ ገቢ ያደረገ መሆን አለበት፣ ከዩኒቨርሲቲው ባንክ ሂሳብ ቁጥር ውጭ በሌላ ተቋም ገቢ በማድረግ ደረሰኝ ማቅረብ ወይም ከምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ ውጪ ለዩኒቨርሲቲውም ገቢ በማድረግ ደረሰኝ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም፣ ፈተና ላይ ለመቀመጥም አያስችልም፣
ለመፈተን የተመዘገበ ስለመሆኑ በዩኒቨርሲቲው በኩል ስሙ ለኢንስቲትዩቱ የተላከ መሆን አለበት፣ በምዝገባ ጊዜ ገደብ ውስጥ ብቻ ስሙ በዩኒቨርሲቲው መዝጋቢነት እና በኢንስቲትዩ ማረጋገጫ ያልተላለፈ ተመዝጋቢ ፈተና ላይ መቀመጥ አይችልም፣
ወደፊት በሚገለፀው የምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ ብቻ የሚፈተንበትን ዩኒቨርሲቲ ምርጫ እንዲሁም በኤግዘምሽን ምክንያት የማይፈተናቸው ፈተናዎች ካሉ ማሳወቅ አለበት፣ ከምዘገባ ጊዜ ሰሌዳው ውጭ የሚቀርብ ኤግዘምሽን መረጃ እና የዩኒቨርሲቲ ለውጥ ተቀባይነት የለውም፣
በምዝገባ ወቅት የሚፈተንበትን ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ሲመርጥ ከተማረበት ዩኒቨርሲቲ ርቆ የሚገኝ ከሆነ ህጋዊ ምክንያት (የመስሪያ ቤት መታወቂያ፣ የነዋሪነት መታወቂያ፣ አስገዳጅ የስራ ወይም የፀጥታ ሁኔታ መረጃ፣ የሆስፒታል መረጃ፣ ሌሎች) ማሳየት / ማቅረብ አለበት፣ ጉዳዩም ለኢንስቲትዩቱ በደብዳቤ መድረስ ይገባዋል፣ በፈተና አሰጣጥ ወቅት የተፈታኞች መረጃ ማጣራት ሲደረግ ስህተት ሆኖ ከተገኘ ፈተናው ይሰረዝበታል፣
ከተማረበት ዩኒቨርሲቲ ውጭ ተመዝግቦ የተገኘ ተፈታኝ ወይም ያላስተማረውን ተማሪ መዝግቦ መረጃ ያስተላለፈ ዩኒቨርሲቲ የምዝገባው መረጃ ውድቅ የሚደረግበት ሲሆን ኃላፊነቱን ተፈታኙ / ዩኒቨርሲቲው የሚወስድ ይሆናል፣ ፈተና ላይ ለመቀመጥም አያስችልም፣
በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ዩኒቨርሲቲዎች የተመዝጋቢዎች ዝርዝር እና የተሰበሰበ ገንዘብ ገቢ ካላደረጉ ምንም ተፈታኝ እንዳልመዘገቡ ይቆጠራል / ኃላፊነት ይወስዳሉ፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ማንነትን የሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ፣ እስክሪቢቶ እና የተፈቀዱ ማጣቀሻዎችን ብቻ ይዞ መገኘት ይገባል፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ከተፈቀዱ ማጣቀሻዎች ውጪ ማንኛውንም ዓይነት ፅሑፍ ያለበት ወረቀትም ሆነ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ፣ የእጅ ሰዓት፣ ተፈታኙ ከስራ መደቡ አንፃር ህጋዊ የሆነ ሆኖም በፈተና ጣቢያ የማይፈቀድ ነገር ይዞ መገኘት እንዲሁም ሌሎች በፈተና አሰጣጥ ወቅት የማይፈቀዱ ነገሮችን ይዞ መገኘት አይቻልም፣ በአራተኛው የፈተና ቀናት ማንነትን ከሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ እና ከእስክሪቢቶ በስተቀር ምንም ነገር ይዞ መምጣት አይፈቀድም፡፡ በቅድመ ፈተና ፍተሻ ወቅት በፈተና መስጫ ግቢ እና ክፍል ውስጥ ይህ ሆኖ ከተገኘ ሙሉ የፈተና ውጤት ይሰረዛል፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ምንም ዓይነት ነገር መቀያየር እና መዋዋስ የማይቻል በመሆኑ ሁሉም ተፈታኝ በግሉ የሚጠቀምበትን ነገር ይዞ መገኘት ይገባዋል፣
የፈተና አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በተለያየ ህጋዊም ሆነ ህጋዊ ባለሆነ ምክንያት ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ አርፍዶ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተና ግቢም ሆነ ክፍል ውስጥ መግባት አይፈቀድም፣ በመሆኑም ለፍተሻ ሂደት እና ለቅድመ ዝግጅት ሲባል ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከሚሰጥበት ሰዓት አንድ ሰዓት ቀደም ብሎ ወደ ፈተና ጣቢያ ጊቢ እንዲደርስ ይመከራል፣
ውጤትን በተመለከተ ቅሬታ ካለ በዩኒቨርሲቲ በኩል በደብዳቤ ለኢንስቲትዩቱ የሚቀርብ ይሆናል፡፡

ኢንስቲትዩቱ -
መልካም የቅድመ ዝግጅት ጊዜ!
ማስታወሻ:- በቀጣይ ባሉት ቀናት እና ሳምንት ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ማስታወቂያዎችን ይከታተሉ / ለሌሎች ያሳውቁ፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig via @Lawsocieties
#በጋራ አብሮ የመስራት ውል (joint Venture Agreement)
በአዲሱ የንግድ ህግ አንቀጽ 234 መሰረት የአሽሙር ማህበር ማለት “ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸው በሚያደርጉት ስምምነት መሠረት የሚያቋቁሙት በሦስተኛ ወገኖች የማይታወቅ የሕግ ሰውነት የሌለው የንግድ ማኅበር ነው፡፡” በማለት ይገልጸዋል፡፡
በዚህ አንቀጽ መሰረት ይህ አይነት ማህበር ስለሌሎች የንግድ ማህበሮች የተደነገጉት የማስመዝገብ ስርዓቶች በዚህ ማህበር ላይ ተፈጻሚ እንደማይሆኑ ይገልጻል፡፡
በመሆኑም ተገልጋዮች በጋራ አብሮ የመስራት ውል(የአሽሙር ውል) ለመዋዋል ወደ መስሪያ ቤታችን ሲመጡ ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡
. በህግ አግባብ የተዘጋጀ የውል ሰነድ፣
. የተዋዋይ ወገኖች ወገኖች የተናጠል ወይም የየግላቸው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣
. ተዋዋይ የንግድ ማህበር ከሆነ የመመስረጃ ጽሁፍ፣ የንግድ ዋና ምዝገባ እና እንደአስፈላጊነቱ ቃለ-ጉባኤ፣
. በውል ሰነዱ ውስጥ በዝርዝር የተገለጸና ማስረጃ የሚያስፈልገው የባለቤትነት ወይም የመብት ማጣቀሻ ካለ ይህንኑ የሚያረጋግጣ ማስረጃ፣
. የተዋዋይ ወገኖች የታደሰ መታወቂያ፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተገልጋዮች የተባሉትን ዝርዝር ነገሮች አሟልተው ሲቀርቡ ለዚህ አገልግሎት የሚወስደው ጊዜ 25 ደቂቃ ነው፡፡
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ( share ) በማድረግ ብልሹ አሰራር እና ሙስናን ይከላከሉ፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig via @Lawsocieties
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የብሔራዊ የምስለ ችሎት ውድድር አሸናፊ ሆኗል።

ከ19 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የተወከሉ የሕግ ተማሪዎች በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ በቆየው የምስለ ችሎት/Moot Court የመጨረሻ ዙር ውድድር ተካፍለዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተወዳዳሪዎች መካከል የመጨረሻ ውድድር ተካሂዶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቋል።

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ እና አርሲ ዩኒቨርሲቲ ሦሥተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡

ብሔራዊ ውድድሩ "በስደተኞች ሕግ" ላይ ትኩረት ያደረገ እንደነበር ተገልጿል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሕግና ገቨርናንስ ኮሌጅ የሕግ ትምህርት ቤት ከሲቪል ሶሳይቲ ሪሶርስ ሴንተር (Civil Society Resource Center) ጋር በመተባበር ውድድሩን ማዘጋጀታቸው ተመላክቷል።
#አለ_ህግ #Ale_Hig via @Lawsocieties
Forwarded from አለሕግ🔵AleHig
የጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባሕል እና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የማኅበረሰብ-አቀፍ ጤና መድኅን ለመደንገግ የወጣውን ረቂቅ አዋጅ የውሳኔ ሐሳብ እና ሪፖርት መርምሮ 1273/2014 ሆኖ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል።
የብሄራዊ ደኅንነትና መረጃ አገልግሎት ሠራተኞች የማናቸውም ፖለቲካ ፓርቲ አባላት እንዳይሆኑ የሚያዝ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን ዋዜማ ራዲዮ ዘግቧል።

የሚንስትሮች ምክር ቤት መጋቢት ላይ የመራው ረቂቅ አዋጅ፣ የብሄራዊ ደኅንነትና መረጃ ተቋምን እንደገና ለማዋቀር የቀረበ ነው። ረቂቅ አዋጁ የተቋሙ ሠራተኞች በማንኛውም የፖለቲካ ቅስቀሳ እና ገቢ በሚያስገኝ ሌላ ተጨማሪ የሥራ መስክ እንዳይሰማሩ ጭምር ይከለክላል። የተቋሙ ሠራተኞች ከሥራው ባህሪ ጋር የሚመጣጠን በቂ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም እንዲከፈላቸው ለመንግሥት ጥያቄ እንደሚቀርብ የሚገልጠው ረቂቁ፣ የሠራተኛ ምልመላ፣ ቅጥር፣ ሙያዊ ስነ ምግባርና የስንብት ደንቦችን ጭምር አካቷል።ኢትዮ-መረጃ
#አለ_ህግ #Ale_Hig via @Lawsocieties
#Grammar Family There is a family in London whose surname is Grammar. There is a couple, Mr. Noun and Mrs. Verb.
The couple has three children: a son, Pronoun and two daughters, Adverb and Adjective.
The son (pronoun) has to do all the work of his father in his absence. The two daughters love each other but there is a difference in them. Adjective loves her father and brother and keeps praising them.
Adverb loves her mother more and she always modifies her when there is a need.
There are two servants in the family. Preposition and Conjunction.
The preposition is the chief servant. He is the official servant of his master.
Conjunction is the family servant and looks after every member of the family.
The Interjection joins the family in times of joy and sorrow.
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Forwarded from አለሕግ🔵AleHig
THE 3RD ANNUAL NATIONAL LAW RESEARCH CONFERENCE

ON "TAXATION SYSTEMS AND HUMAN RIGHTS IN ETHIOPIA"

Dilla University
Organized by:
Dilla University (DU) in Collaboration with Federal Justice and Law Institute (FJLS) and Ethiopian Law Schools' Consortium

Date: May 21, 2022 to May 22, 2022 Time: 2:30 LT Venue: Multi-Purpose Hall, Main Campus, Dilla University
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Senior Attorney, Bank of Abyssinia

 Bank Of Abyssinia (BOA)

 

 Addis Ababa, Ethiopia

 

 May 02, 2022

Full Time Banking Jobs in Ethiopia Legal Jobs in Ethiopia

JOB DESCRIPTION

Senior Attorney, Bank of Abyssinia

 

Job Requirements

Education: LLM/LLB Degree in Law
Experience: Minimum of 6/8 years banking experience, of which 4 years in the area of Law.

How to Apply

Only short-listed candidates will be contacted.

Applicants should attach their educational credentials & updated work experience in PDF format

Interested applicants who meet the above criteria are invited to apply within 5 consecutive days from the date of this advertisement using https://vacancy.bankofabyssinia.com

Note:- In person or postal application is not accepted.
😄
በደቡብ ሱዳን በአንዲት ሴት ግድያ ጥፋተኛ የተባለዉ በግ በሶስት ዓመት እስር እንዲቀጣ ተወስኗል🔴

በደቡብ ሱዳን በአንዲት አዛዉንት ደረት ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት በመፈጸም ለሞት ዳርጓል የተባለዉ በግ በሶስት አመት እስር እንዲቀጣ መወሰኑን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።የበጉ ባለቤትም ለተጎጂው ቤተሰብ አምስት ላሞችን እንዲከፍል በደቡብ ሱዳን ሩምቤክ ከተማ የሚገኘው የአካባቢው ፍርድ ቤት ብይን ሰጥቷል።

ሱዳን ቱዴይ ጋዜጣ እንደዘገበው በደቡብ ሱዳን ሌክ ግዛት የሚገኘው የሩምቤክ ፖሊስ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ሴትየዋን የገደለዉን በግ በቁጥጥር ስር አውሏል። በጉ በሴቲቱ ላይ ጥቃት ሰንዝሮ ከመሞቷ በፊት ደረቷ ላይ ብዙ ጊዜ እንደመታት ተነግሯል።

በልማዳዊ ህግ ማንኛውም የቤት እንስሳ ሰውን የገደለ እንደሆነ ለሟች ቤተሰብ ካሳ ይከፈለዋል የሚል መመሪያ ቢኖርም የቤት እንስሳ በእስር መቀጣቱን አነጋጋሪ ሆኗል።
[ዳጉ ጆርናል]
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
የኢትዮጵያ የህግ ምንጮች እና ተዋረድ

መግቢያ

ህጎች የተለያዩ መመዘኛዎችን መሰረት በማድረግ ሊከፋፈሉ ይችላሉ፡፡

በዚህ መሰረት “የሲቪል ሎው (civil law)” እና “የኮመን ሎው (common law)”፣ “ፐብሊክ ሎው (public law)” እና “የግል ህግ (private law)”፣ “የወንጀል ህግ” እና “የፍትሀብሄር ህግ”፣ “የስነ ስርዓት ህግ (procedural law)” እና “መሰረታዊ ህግ (substantive law) እና የመሳሰሉትን መስፈርቶች በመጠቀም ህጎችን ማከፋፈል ይቻላል፡፡ የሀገራት ህጎች በሁለት ዋና ዋና የህግ ስርዓቶች ማለትም የኮመን ሎው እና የሲቪል ሎው በሚል ይታወቃሉ፡፡ የሲቨል ሎው የህግ ስርዓት ተከታይ አገራት ፍትሀብሄርን የሚመለከት ዐብይ ህግ በአንድ ጥራዝ (codified) ታውጀው እና የወንጀል የሚመለከት ዐብይ ህግ በአንድ ጥራዝ (code) ታውጀው ይገኛሉ፡፡ እነዚህም በአገራችን አጠራር የፍትሀብሄር ህግ እና የወንጀል ህግ ተብለው ይታወቃሉ፡፡ ስለሆነም ይህን ስርዓት የሚከተሉ ሀገሮች ዋና የህግ ምንጭ በህግ አውጪ አካል ታውጀው የሚጠረዙ ህጎች ናቸው ማለት ነው፡፡ በሌላ በኩል የኮመን ሎው ስርዓትን የሚከተሉ ሀገሮች ዋና የህግ ምንጫቸው በህግ አውጪ አካል የሚወጡ ህጎች ሳይሆኑ በፍርድ ቤቶች በተመሳሳይ ጉዳይ ቀደም ብለው የተሰጡ አስገዳጅ ውሳኔዎች (precedent) ናቸው፡፡ እንዲሁም ያልተፃፉ ህጎችን ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡

በሀገራችንም የተለያዩ የህግ ምንጮች ያሉ ሲሆን የህጎች ተዋረድ ወይም የህግ የበላይነት ደረጃ (hierarchy of laws) በህግ ስርዓት ውስጥ ጉልህ ቦታ ካላቸው ጉዳዮች አንዱ ነው፡፡ በዚህ የንቃተ ህገ ፅሁፍ የኢትዮጵያ የህግ ምንጮችን እና የህጎቹን ተዋረድ ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡.......ይቀጥላል👇👇👇
.....የቀጠለ

1. የኢትዮጵያ ህግ ምንጮች (sources of Ethiopian laws)
በአገራችን ህጎች በፌደራል እና በክልል ደረጃ ወጥተው ስራ ላይ ይውላሉ፡፡ እነዚህም ህጎች በፌደራል እና በክልሎች የተለያዩ ምንጮች አሏቸው፡፡

1.1. የፌደራል የህግ ምንጮች
i. ህገ መንግስት (constitution)
የኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 9 ህገ መንግስት የሀገሪቱ የበላይ ሕግ እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡ ማንኛውም ህግ ለምሳሌ አዋጅ፣ ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከሕገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡ ይህ ማለት ህገ መንግስት የማንኛውም ህጎች መነሻ እና ምንጭ እንዲሁም ህጋዊነታቸውን (validation) የሚያገኙበት መሰረት ነው፡፡
ii. አለም አቀፍ ስምምነቶች (international treaties)
ሀገራት አለም አቀፍ ስምምነት ሲፈርሙ ስምምነቱን እንደ አንድ አለም አቀፍ ህግ እንተቀበሉ ማስረጃ ነው፡፡ የህገ መንግስቱ አንቀፅ 9 (4) እንደሚደነግገው ኢትዮጵያ ያፀደቀቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የሀገሪቱ ህግ አካል ናቸው፡፡ እነዚህ ስምምነቶች ስራ ላይ ለመዋል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅደቅ እና በነጋሪት ጋዜጣ ላይ ታትመው መውጣት አለባቸው፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የአገሪቱ ህግ አካል ሆነው ተግባራዊ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡
iii. ኮዶች (codes)
በሀገራችን በ1960ዎቹ አምስት ኮዶች ተዘጋጅተው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ እነዚህም የፍትሀ ብሄር ህግ፣ የንግድ ህግ፣ የባህር ህግ በ1960፣ የወንጀል ስነ ስርዓት ህግ በ1961 እና የፍትሀ ብሄር ስነ ስርዓት ህግ በ1965 ናቸው፡፡ እነዚህም ህጎች በነጋሪት ጋዜጣ በአዋጅ መልክ ታውጀው ስራ ላይ ውለዋል፡፡ ከዚህም በኃላ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ፣ የወንጀል ህግ እና አዲሱ የንግድ ህግ በኮድ መልክ ስራ ላይ የዋሉ የአገራችን የህግ ምንጮች ናቸው፡፡
iv. አዋጅ፣ ደንብ እና መመሪያ (proclamations, regulations & directives)
አዋጆች በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ደንቦች በሚኒስትሮች ምክር ቤት እና መመሪያዎች ደግሞ በፌደራል ሚኒስትሮች መስሪያ ቤቶች ወይም በሚስትሮች ምክር ቤት መመሪያ እንዲያወጡ በደንብ ውክልና በተሰጣቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ይወጣሉ፡፡ በተጨማሪም የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የማወጅ ስልጣን በህገ መንግስቱ ተሰጥቶታል፡፡ እነዚህም የህግ ክፍሎች ወይም አይነቶች የአገራችን የህግ ምንጭ በመሆን የሚያገለግሉ ሲሆኑ በስራ ላይ የሚውሉበትን ሁኔታ በተመለከተ በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ ይህም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይም በሚነስትሮች ምክር ቤት ከታወጁበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ የሚውሉ ወይም በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው ከወጡበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ የሚውሉ ናቸው፡፡
v. አስገዳጅ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች (precedent)
ይህ የህግ ምንጭ አይነት ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ በተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ አስገዳጅ ወይም ህግ የሚሆንበት ስርዓት ነው፡፡ በአገራችን ፍርድ ቤቶች የሚሰጧቸው ውሳኔዎች በተመሳሳይ ጉዳዮች ላይ እንደ ህግ እንደሚያገለግሉ እና አስገዳጅ እንደሆነ የሚገልፀው የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ነው፡፡ በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 10/2 ስር እንደተደነገገው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከአምስት ያላነሱ ዳኞች በተሰየሙበት የሰበር ችሎት የሚሰጠው የህግ ትርጉም በየትኛውም ደረጃ ላይ ባለ የፌደራል እና የክልል ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅነት ይኖረዋል ይላል፡፡ ይህ ማለት እነዚህ ውሳኔዎች የህግ ምንጭ ሆነው ስራ ላይ ይውላሉ ማለት ነው፡፡
vi. ልማዳዊ ህጎች (customary laws)
ልማዳዊ ህጎች በኢትዮጵያ ህጎች ውስጥ በተለያየ ጊዜ እንደምንጭ ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ ለምሳሌ የፍትሀ ብሄር ህጉን ያረቀቁት ፕሮፌሰር ሬኒ ዳቪድ በረቂቁ ውስጥ የኦርቶዶክስን ልማዳዊ ህግ ‘ፍትሀ ነገስትን‘ እንደምንጭ እንደተጠቀሙበት ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም በህገ መንግስቱ አንቀፅ 34/5 ስር እንደተደነገገው የግል እና የቤተሰብ ሕግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ፈቃድ በሀይማኖቶች ወይም በባሕሎች ሕጎች መሰረት መዳኘት እንደሚችሉ ያስቀምጣል፡፡ በመሆኑም ባህላዊ ወይም ልማዳዊ ህጎች እንደ አንድ የህግ ምንጭ ያገለግላሉ ማለት ነው፡፡

1.2. የክልል ህግ ምንጮች
i. የክልል ህገ መንግስት(state constitutions)
በኢፌድሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 52/2 ስር እንደተደነገገው ክልሎች የራሳቸው ህጎች ማውጣት ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ክልሎች የራሳቸው ህገ መንግስት ከፌደራል ህገ መንግስት ጋር በሚጣጣም መልኩ አውጥተዋል እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡ የክልል ህገ መንግስት በክልሎቹ ውስጥ የበላይ ህግ ነው፡፡
ii. የክልል አዋጆች (state proclamations)
የፌደራል ህገ መንግስት ክልሎች ለአስተዳደር በሚያመች መልኩ የክልሎቹን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት በማስገባት አዋጅ ማወጅ እንደሚችሉ ያስቀምጣል፡፡ በዚህ መሰረት ለምሳሌ ትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ እና የደ/ብ/ብ/ህ ክልል የራሳቸው የቤተሰብ ህግ አውጀዋል፡፡
iii. የክልል ደንቦች እና መመሪያዎች (state regulations & directives)
የፌደራል ህገ መንግስት የክልል አስፈፃሚ ምክር ቤቶች በክልል ወሰን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ እንደሚችሉ እንዲሁም ደንብ እና መመሪያዎችን ማውጣት እንደሚችሉ ስልጣን ሰጥቷቸዋል፡፡

2. የህጎች ተዋረድ (hierarchy of laws)
የህጎች ተዋረድ (hierarchy of laws) የህጎች የበላይነት ደረጃን ወይም የትኛው ህግ ከየትኛው ህግ የበላይ ህግ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ በአገራችን በህገ መንግስቱ አንቀፅ 9/1 ስር እንደተደነገገው ማንኛውም ህግ፣ ልማዳዊ ድርጊት እንዲሁም የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት እንደማይኖረው ይደነግጋል፡፡ ይህ ማለት በሀገሪቱ ውስጥ የህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ህገ መንግስቱ ነው ማለት ነው፡፡

የፌደራል ህገ መንግስት በፌደራልም ይሁን በክልል ደረጃ የህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነው፡፡ በመቀጠል የአገሪቱ የበላይ የህግ አውጪ አካል ማለትም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚያወጣቸው ህጎች ማለትም አዋጆች ይከተላሉ፡፡ የአለም አቀፍ ስምምነቶችን የህግ ተዋረድ በተመለከተ ወጥ የሆነ መግባባት ባይኖርም በህገ መንግስቱ ኢትዮጵያ የፈረመቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች የአገረቱ ህግ አካል ይሆናሉ ስለሚል ከአዋጅ ጋር ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ይቀመጣሉ የሚል ሀሳብ አለ፡፡ በህግ ተዋረድ በመቀጠል የሚመጡት በሚኒስትሮች ምክር ቤት የሚወጡት ደንቦች እና በሚኒስትር መስሪያ ቤቶች የሚወጡት መመሪያዎች በቅደም ተከተል ናቸው፡፡

በሌላ በኩል በተመሳሳይ ተዋረድ (hierarchy) ላይ ባሉ ህጎች መካከል መቃረን ሲኖር ተፈፃሚ የሚሆነው በጊዜ ዘግይቶ የወጣው ህግ (latest prevails) ነው፡፡ ይህ ማለት ዘግይቶ የወጣው ቀድሞ ከወጣው ይልቅ ተፈፃሚ ይሆናል ማለት ነው፡፡ እንዲሁም ልዩ ህግ (special law) ከጠቅላላ ህግ ይልቅ ቅድሚያ ተቀባይነት (special law prevails over general law) ይኖረዋል ማለት ነው፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties