አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Forwarded from ..?
ሰላም አለ ህጎች እንዴት ናችሁ ነፃ የህግ ማማከር አገልግሎት እንሰጣለን የሚል ማስታወቂያ አይቼ ነው ፍቃደኛ ከሆናችሁ .... ፍቺ በንብረት ላይ ስላለው consequence ነው! እንደሚታወቀው በእኛ ህግ መሰረት personal property ብሎ ያስቀመጣቸው ነገሮች በፍቺ ግዜ የባለ ንብረቱ እንደሚሆን ያስቀምጣል! ነገር ግን የኔ ጥያቄ personal property ላይ በጋራ እያሉ ተጨማሪ ነገር add ቢያደርጉበት ውጤቱ ምን ይሆናል? መለትም ለምሳሌ ሚስት ባዶ መሬት ከቤተሰቦቿ ብትወርስና በትዳር ዘመኗ በጋራ ቤት ቢሰሩበት በፍቺ ጊዜ እንዴት ይሆናል?
Forwarded from ሕግ ቤት
The Ethiopian Law Schools Association (ELSA) has joined the International Association of Law Schools (IALS).
______________________
IALS is an association of more than 230 law schools and departments from over 70 countries representing more than 10,500 law faculty members.

By joining this association ELSA will have an open and independent forum for sharing experiences and discussing diverse ideas about legal education throughout the world.

It is to be recalled that ELSA was established in August, 2021 with the support of Feteh.
Via Feteh Activity Ethiopia
የፌደራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 ይዟቸዉ የመጣ አዳዲስ ነገሮች
-----------------------------------------------

እንደሚታወቀዉ የፌደራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 (ካሁን በዉሀላ አዲሱ የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ተብሎ የሚጠራዉ) ፀድቆ ወደተግባር ገብቷል፡፡ በዚህ አጭር ፅሁፍ አዋጁ ይዛቸዉ የመጣዉን አዳዲስ ነገሮች በሁለት ከፍል ለመቃኘት አንሞክራለን፡፡ የመጀመሪያዉ ክፍል ከፍ/ቤት የለት ተለት ስራ ጋር የተያያዙ ድንጋጌዎችን የምንቃኝ ሲሆን ሁለተኛዉ ክፍል ደግሞ አስተዳደራዊ እንድምታ ያላቸዉን አንቀፆችን ለመቃኝት እንሞከራለን፡፡

“መሰረታዊ የህግ ስህተት” ለሚለዉ ፅንስ ሐሳብ ትርጉም የተሰጠዉ ስለመሆኑ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገመንግስት የፌደራልና የክልል የፍርድ ቤት መዋቅር እንደሚቋቋም በመደንገግ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት “መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት” ያለባቸዉን ማናቸዉንም ዉሳኔዎች የማየት ስልጣን የሰጠዉ ቢሆንም “መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት” ለሚለዉ ፅንስ ሐሳብ በቀደሙት ህጎች ትርጉም ያልተሰጠዉ ወይም በዚህ ፅንስ ሐሳብ ስር ሊሸፈኑ የሚችሉ የህግ ስህተቶችን ለመለየት የሚያስችል መስፈርት ያልተቀመጠ በመሆኑ በፍትህ ስርአቱ ወጥነትና ተገማችነት ላይ የራሱን የሆነ ጥቁር ጥላ አሳርፏል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ተመሳሳይ ጭብጥ የያዙ ጉዳዮችን አንዱን መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት አለበት ብሎ ሲቀበል ሌላኛዉን ደግሞ መሰረታዊ የሆነ የህግ ግድፈት የለበትም በማለት መዝገቡን ዘግቶ ባለጉዳዮዎችን ማሰናበቱ ነዉ፡፡ በርግጥ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ምኛዉንም መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ያበትን ጉዳይ ሰበር እንዲያይና ዉሳኔዉም አስገዳጅ እንዲሆን መደረጉ በመላ ሀገሪቷ ወጥነት ያለዉ የህግ ትርጉም እንዲኖር የሚያደርግ ቢሆንም “መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት” ማለት ምን ማለት ነዉ? ለሚለዉ ጥያቄ በህግ ምላሽ ያልተሰጠዉ በመሆኑ በጠቅላይ ፍ/ቤት የሚታዩ ጉዳዮች ወጥነትና ተገማችነት እንዳይኖረዉ ከማድረጉም በሻገር ዜጎች ላልተገባ ወጪና እንግልት እንዲዳረጉ እድል ፈጥሯል፡፡

ይህንን ችግ በሚቀርፍ መልኩ አዲሱ የፍ/ቤቶች አዋጅ በአንቀፅ 2 ንዑስ አንቀፅ 4 ስር መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ማለት ምን ማለት እንደሆነና በዚህ ፅንስ ሀሳብ ስር ሊሸፈኑ የሚችሉ የህግ ስህተቶችን ለመለየት የሚያስትል መለያ መስፈርት አስቀምጣል፡፡ መዚህ አንቀፅ መሰረት መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት ማለት ቀጥሎ ከተዘረዘሩት መካከል አንዱ እና ፈትህን የሚያዛባ ጉልህ የህግ ስህተት ያለበትን በዚህ አዋጅ አንቀፅ 10 መሰረት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሊታዩ የሚችሉ የመጨረሻ ዉሳኔ፣ ፍርድ፣ ብይን፣ ትእዛዝ ናቸዉ፡-

ሀ. የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌዎች የሚቃረን፣
ለ. ሕግን አላግባብ የሚተረጉም ወይም ለጉዳዩ አግባብነት የሌለዉን ሕግ የሚጠቅስ፣
ሐ. ለክርክሩ አግባብነት ያለዉ ጭብጥ ሳይያዝ ወይም ከክርክሩ ጋር የማይዛመድ አግባብነት የሌለዉ ጭንጥ ተይዞ የተወሰነ፣
መ. በዳኝነት ታይቶ ሊወሰን የሚገባዉን ጉዳይ ውድቅ በማድረግ የተወሰነ፤
ሠ. በፍርድ አፈጻጸም ሂደት ከዋናዉ ፍርድ ጋር የማይገኛኝ ጥእዛዝ የተሰጠበት፣
ረ. ጉዳዩን አይቶ የመወሰን የዳኝነት ሥልጣን ሳይኖር የተወሰነ፣
ሰ. የአስተዳደር አካል ወይም ተቋም ከህግ ዉጭ የሰጠዉ ዉሳኔ፣
ሸ. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አስገዳጅ ዉሳኔ በመቃረን የተወሰነ፡፡ በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የታዩ ጉዳዮችን በሰበር የማየት ስልጣን የጠበበ ስለመሆኑ

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 78 መሰረት የፌዴራልና የክልል ፍ/ቤት እራሳቸዉን በቻሉ መልኩ የተቋቋሙ ሲሆን በአንቀፅ 80 ንዑስ አንቀፅ 3(ሀ ና ለ) መሰረት የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት በክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የታዩ ጉዳዮችን ጨምሮ ማንኛዉንም መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበትን ወሳኔ የማየት ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡ ይህንን ስልጣን መሰረት በማድረግ የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበትን ማንኛዉንም ወሳኔ እያየ የቆየ ቢሆንም እዲሱ የፌዴራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ይህንን ስልጣን አጥብቦታል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በክልሎች ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጡ ዉሳኔዎችን በሰበር ማየት የሚችለዉ ዉሳኔዎቹ የህገ-መንግስቱን ድንጋጌዎች ወይም አስገዳጅ የሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት የሰበር ዉሳኔዎችን በመቃረን የተሰጡ ዉሳኔዎች እንደሆኑ ወይም ክፍተኛ የህዝብ ጥቅም ወይም ሐገራዊ ፍይዳ ባለዉ ጉዳይ ላይ የክልሉን ህግ ያለ አግባብ በመተርጎም ወይም አግባብነት የሌለዉን ህግ በመጥቀስ የተሰጠ ዉሳኔ ከሆነ ብቻ ስለመሆኑ በአዋጁ አንቀፅ 10 ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ይህ ድንጋጌ የሰበር ችሎቱን የመዝገብ ፍሰት በመቀነስ የተፋጠነ ፍትን ለመስጠት የሚያስችል ቢሆንም ወጥነት ያለዉን የህግ ትርጉም በመላ ሀገሪቷ እንዲኖር ከማስቻል አንፃር ዉስንነት ሊኖረዉ ይችላል፡፡
የፍታብሔር ፍ/ቤቶች የስረነገር ስልጣን ስለመሻሻሉ
በቀድሞ የፌደራል ፍ/ቤቶች አዋጅ ቁጥር 25/88 መሰረት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት እስከ አምስት መቶ ሺ ብር(500‚000.00) የሚደርሱ ክፍተኛዉ ፍ/ቤት ደግሞ ከአምስ መቶ ሺ ብር በላይ የሆኑ የፍታብሔር ጉዳዮችን የማየት የስረ ነገር ስልጣን የነበረዉ ቢሆንም በአዲሱ አዋጅ አንቀፅ 11(1) አና 14 መሰረት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት እስከ አስር ሚሊዮን ብር(10‚000‚000.00) የሚደርሱ ክፍተኛዉ ፍ/ቤት ደግሞ ከአስር ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የፍታብሔር ጉዳዮችን የማየት የስረ ነገር ስልጣን ተሰጥቶታል፡፡

የሰብአዊ መብጥ ጥሰትን የሚመለከቱ አቤቱታዎች ተቀብሎ ተገቢ የሆነ ዉሳኔ የመስጠት ስልጣን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የተሰጠ ስለመሆኑ
የፌደራል ፍ/ቤቶች አዋጅ አንቀፅ 11(3) ላይ እንደተደነገገዉ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ማንኛዉም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግስት ምዕራፍ ሶስት ስር የሰፈሩትን መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶቸችን ለማስከበር የሚያስችል ተገቢ የሚለዉን ፍርድ፣ ትዕዛዝ ወይም ዉሳኔ የመስጠት ስልጣን የተሰጠዉ ሲሆን በዚሁ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 4 ስር ማንኛዉም በጉዳዩ ላይ መብት ወይም ጥቅም ወይም በቂ ምክንያት ያለዉ ሰዉ የመሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች ጥሰትን በሚመለከት አቤቱታ የማቀረብ መብት ያለዉ ስለመሆኑ ተደንግጓል፡፡ በአለማቀፍ የሰብአዊ መብት ሰነዶች ከሰብአዊ መብቶች ጋር በተያያዘ የኢትዮጲያ መንግስት ሶስት መሰረታዊ ግዴታዎች የተጣለበት ሲሆን ከነዚህ መካከል ሰብአዊ መብቶችን የማክበር፣ የማስከበር ግዴታዎች ይገኙበታል፡፡ ይህ ድንጋጌ መንግስት በህገ-መንግስቱና በአለማቀፍ የሰብአዊ መብቶች ህግጋት የተጣለበትን የማክበርና የማስከበር ግዴታ እንዲወጣ ከማስቻሉም ባሻገር በሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተጎጂ የሆኑ ፣ ያላግባብ በእስርላይ ያሉ ወይም አቤቱታ ማቀረብ በማይቻልበት ሁኔታ ዉስጥ ያሉ ግለሰቦች በአፋጣኝ ፍትህ እንዲያገኙ እድል ይፈጥራል፡፡

ለአዲስ አበባና ድሬዳዋ የአስተዳደር ወይም ከተማ ነክ ፍ/ቤቶች የተሰጡ የፍታብሔር የዳኝነት ስልጣን
የአዲስ አበባና ድሬዳዋ አስተዳደር ፍ/ቤቶች በከተማዉ ቻርተር መሰረት የተሰጣቸዉ የዳኝነት ስልጣን እንደተጠበቀ ሆኖ በአዲሱ አዋጅ አንቀፅ 5 ንዑስ አንቀፅ 1(ደ) መሰረት በከተማዎቹ በሚኖሩ ግለሰቦች መሀከል የሚደረጉ እስከ አምስት መቶ ሺ ብር /500‚000/ ድረስ የሚደርሱ የገንዘብ ፣ ዉልና የብድር ጉዳዮችን የማከራከርና ዉሳኔ የመስጠት ስልጣን ተሰጥታቸዋል፡፡
Source:- FDRE Attorney General የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
#አለ_ህግ #Ale_Hig
አለሕግAleHig ️ pinned «ሰላም አለ ህጎች እንዴት ናችሁ ነፃ የህግ ማማከር አገልግሎት እንሰጣለን የሚል ማስታወቂያ አይቼ ነው ፍቃደኛ ከሆናችሁ .... ፍቺ በንብረት ላይ ስላለው consequence ነው! እንደሚታወቀው በእኛ ህግ መሰረት personal property ብሎ ያስቀመጣቸው ነገሮች በፍቺ ግዜ የባለ ንብረቱ እንደሚሆን ያስቀምጣል! ነገር ግን የኔ ጥያቄ personal property ላይ በጋራ እያሉ ተጨማሪ…»
ማስታወቂያ ለጥብቅና ፈቃድ ተፈታኞች❗️🙏
ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጥብቅና ፈቃድ ለማግኘት ለፈተና የተቀመጣችሁ የህግ ባለሙያዎች የፈተና ውጤት ለመሳወቅ የተዘጋጀውን ማስታወቂያ ከዚህ በታች አጋርተናል፡፡

በፈተናው ውጤት ላይ ቅሬታ ያላችሁ ከዛሬ ግንቦት 05 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ቅሬታ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑም በማስታወቂያው ተገልጿል፡፡

ላልደረሳቸው በማጋራት እንድታግዙን እንጠይቃለን
#አለ_ህግ #Ale_Hig
🔴Exit Exam🙏የሕግ መዉጫ ፈተና

ሠላም እንዴት ናችሁ ዉድ የ2014 የሕግ መዉጫ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ፣
ፈተናው 🔴 ከግንቦት 29 እስከ ሠኔ 5 የሚሠጠዉ ፈተና እስካሁን ምንም ለዉጥ ያልተደረገ መሆኑን አዉቃችሁ ዝግታችሁን እንድትቀጥሉ እየገለጽን ለውጥ የሚኖር ከሆነ የምናሳዉቅ መሆናችንን እንገልፃለን።

መሥፍን እሸቱ የ ሕግ ት/ ቤቶች አስተባባሪ
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
#Update
.
የ2014አም መውጫ ፈተና አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ግንቦት ወር መጨረሻ እንደሚሰጥ ይታመናል።ከዚህ በፊት በፃፍኩት ፅሁፍ ላይም ተፈታኞች መዘናጋት እንደሌለባችሁና ጥናታችሁን በአግባቡ ልታጠኑ እንደሚገባ አሳውቄ ነበር።በግል መስመር እጅግ በጣም ብዙ ተፈታኞች በእርግጥም ፈተናው ግንቦት ወር ላይ ይሰጣል ወይ እያላችሁኝ ነው።እኔም በተደጋጋሚ እንደምገልፀው አድስ ነገር እስካልተፈጠረ ድረስና ባለድርሻ አካላቱ ተራዝሟል እስካላሉ ድረስ ሳትዘናጉ ጥናታችሁን ተከታተሉ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታም ፈተናው ግንቦት ወር እንደሚሰጥ እናምናለን ብለዋል የELSA ፕሬዝደንትና የኮንሰርቲየሙ ዋና ፀሃፊ።
.
.
#Ahmed.M
Forwarded from Qualitymovbot
የተለያዩ ጠቃሚ የህግ የቴሌግራም ቻናሎች መካከል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ስሞች በመንካት ቤተሰብ ይሁኑ❗️🙏
<<<<<<<<<<<<#ፍትሃዊው_ዳኛ!!>>>>>>>>>>

#አሜሪካ ውስጥ የ15 አመት ታዳጊ ሱቅ ሲሰርቅ ከዛም ሊያመልጥ ሲል አንዱን መደርደሪያ ሰበረ ይህ ፍትሃዊ ዳኛ የሰጠው ፍርድ!!

ዳኛው የክስተቱን ዝርዝር ሁኔታ ከሰማ በኋላ ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው።
"በእርግጥ የሆነ ነገር ሰረቅክ? ዳቦና አይብ ሰርቀህ መደርደሪያ ሰባበርክ?"

ልጁም አንገቱን ደፍቶ በአፍረት መለሰ፡-
አዎ.

ዳኛ፡ "ለምን ሰረቅክ?"

ታዲጊው ልጅ: በጣም ፈልጌው ነው

ዳኛ፡ ከመስረቅ ይልቅ መግዛት አልቻልክም ነበር?

ልጅ፡ ምንም ገንዘብ አልነበረኝም።

ዳኛ፡ ወላጆችህን ገንዘብ ልትጠይቅ ትችላለህ።

ልጅ፡ እኔ ያለኝ፣ አልጋ ላይ የተኛች እና ስራ የሌላት የታመመች እናቴን ብቻ ነው... ለሷ ስል ዳቦና አይብ ሰርቄያለሁ።

ዳኛ፡ እና አንተ... ምን እየሰራህ ነው? ሥራ የለህም?

ልጅ፡- የመኪና ማጠቢያ ሆኜ እሰራ ነበር። እናቴን ለመርዳት አንድ ቀን ዕረፍት ወሰድኩ፣ ለዚህም ነው ያባረሩኝ።

ከልጁ ጋር የነበረው ውይይት ካለቀ በኋላ ዳኛው ፍርዱን አስታወቁ፡-
“ሌብነት በተለይም #ዳቦ መስረቅ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው።
ለዚህ የስርቆት ወንጀል ሁላችንም ተጠያቂ ነን። ለዚህ የስርቆት ወንጀል ዛሬ እኔ ራሴን ጨምሮ እዚህ ክፍል ውስጥ የተገኘ ሁሉ ተጠያቂ ነው” አለ።

በመቀጠልም ሁሉም ተሰብሳቢዎች አሥር ዶላር ይቀጣሉ እና ማንም ሰው #10_ዶላር ሳይከፍል ከአዳራሹ አይወጣም.

ዳኛው ከኪሱ የ10 ዶላር ቢል አንሥቶ እስክሪብቶ አወጣና እንዲህ ብሎ መጻፍ ጀመረ።

"በተጨማሪም የተራበውን ልጅ ለፖሊስ ያደረሰው ሱቅ ባለቤት 1,000 ዶላር እንዲቀጣ አዝዣለሁ እና ቅጣቱ በአንድ ሰዓት ውስጥ ካልተከፈለ ሱቁ ተዘግቶ ይቆያል."

በአዳራሹ ውስጥ የነበሩት ሁሉ ለልጁ ይቅርታ ጠይቀው ሙሉ ገንዘቡን ሰጡት። ዳኛው እንባውን ለመደበቅ እየሞከረ ከችሎቱ ወጣ።

ተሰብሳቢዎቹ የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ ዓይናቸው በእንባ ተሞላ።

ዳኛው አክለውም “አንድ ሰው ዳቦ ሲሰርቅ ከተያዘ መላው የዚች ሀገር ህዝብና ህብረተሰብ ሊያፍር ይገባል” ሲሉም አክለዋል።
Source:- FB
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
#ፍትሃዊው_ዳኛ❗️❗️
#አሜሪካ ውስጥ የ15 አመት ታዳጊ ሱቅ ሲሰርቅ ከዛም ሊያመልጥ ሲል አንዱን መደርደሪያ ሰበረ ይህ ፍትሃዊ ዳኛ የሰጠው ፍርድ!! #አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
Notice - For Law Exit Exam Candidates.docx
22 KB
Share 'Notice - For Law Exit Exam Candidates.docx'
#አለ_ህግ #Ale_Hig @Lawsocieties
የቅድመ ዝግጅት ማስታወቂያ

የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና ለመፈተን በዝግጅት ላይ ለምትገኙ ተፈታኞች (Exit Exam)

የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና ቀደም ሲል በተገለፀው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከግንቦት 29 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2014 ዓ.ም ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በመሰራት ላይ እንገኛለን፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የተፈታኞች ምዝገባ አንዱ እና ዋንኛው የቅድመ ፈተና አሰጣጥ ዝግጅት ተግባር ሲሆን ተፈታኞች ከታች የተዘረዘሩትን ነጥቦች ትኩረት በመስጠት ግንዛቤ እንዲጨብጡ እናሳስባለን፡፡
የምዝገባ ቀናት ማስታወቂያ - የተፈታኞች የምዝገባ ቀናት ከጥቂት ቀናት በኋላ ሲወሰን ለሁሉም አስፈታኝ ዩኒቨርሲቲዎች በደብዳቤ እና ለተፈታኞች “ አለ ” በሚለው የቴሌግራም ቻናል ይፋ ይደረጋል፡፡

የምዝገባ ቀናት ጊዜ ሰሌዳ ቆይታ - ከተፈታኞች ምዝገባ መጠናቀቅ በኋላ የፈተና ህትመት የሚካሄድበት ወቅት በመሆኑ እና ፈተናውን በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ለመስጠት ያለው ጊዜ አነስተኛ በመሆኑ የተፈታኞች ምዝገባ ቀናት ቆይታ የተፈታኞች ምዝገባ መጀመሩ በደብዳቤ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ሰባት የስራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡

ተፈታኞች ለምዝገባ እና ለመፈተን ሲመጡ በተጨማሪ ግንዛቤ የሚያስፈልጋቸው ሁኔታዎች -

በሚማርበት ዩኒቨርሲቲ ፈተናውን ለመውሰድ የተፈቀደለት እና የተመዘገበ መሆን አለበት፣
ለምዝገባ የተወሰነውን ክፍያ በዩኒቨርሲቲው ባንክ ሂሳብ ቁጥር ብቻ ገቢ ያደረገ መሆን አለበት፣ ከዩኒቨርሲቲው ባንክ ሂሳብ ቁጥር ውጭ በሌላ ተቋም ገቢ በማድረግ ደረሰኝ ማቅረብ ወይም ከምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ ውጪ ለዩኒቨርሲቲውም ገቢ በማድረግ ደረሰኝ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም፣ ፈተና ላይ ለመቀመጥም አያስችልም፣
ለመፈተን የተመዘገበ ስለመሆኑ በዩኒቨርሲቲው በኩል ስሙ ለኢንስቲትዩቱ የተላከ መሆን አለበት፣ በምዝገባ ጊዜ ገደብ ውስጥ ብቻ ስሙ በዩኒቨርሲቲው መዝጋቢነት እና በኢንስቲትዩ ማረጋገጫ ያልተላለፈ ተመዝጋቢ ፈተና ላይ መቀመጥ አይችልም፣
ወደፊት በሚገለፀው የምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ ብቻ የሚፈተንበትን ዩኒቨርሲቲ ምርጫ እንዲሁም በኤግዘምሽን ምክንያት የማይፈተናቸው ፈተናዎች ካሉ ማሳወቅ አለበት፣ ከምዘገባ ጊዜ ሰሌዳው ውጭ የሚቀርብ ኤግዘምሽን መረጃ እና የዩኒቨርሲቲ ለውጥ ተቀባይነት የለውም፣
በምዝገባ ወቅት የሚፈተንበትን ዩኒቨርሲቲ ምርጫ ሲመርጥ ከተማረበት ዩኒቨርሲቲ ርቆ የሚገኝ ከሆነ ህጋዊ ምክንያት (የመስሪያ ቤት መታወቂያ፣ የነዋሪነት መታወቂያ፣ አስገዳጅ የስራ ወይም የፀጥታ ሁኔታ መረጃ፣ የሆስፒታል መረጃ፣ ሌሎች) ማሳየት / ማቅረብ አለበት፣ ጉዳዩም ለኢንስቲትዩቱ በደብዳቤ መድረስ ይገባዋል፣ በፈተና አሰጣጥ ወቅት የተፈታኞች መረጃ ማጣራት ሲደረግ ስህተት ሆኖ ከተገኘ ፈተናው ይሰረዝበታል፣
ከተማረበት ዩኒቨርሲቲ ውጭ ተመዝግቦ የተገኘ ተፈታኝ ወይም ያላስተማረውን ተማሪ መዝግቦ መረጃ ያስተላለፈ ዩኒቨርሲቲ የምዝገባው መረጃ ውድቅ የሚደረግበት ሲሆን ኃላፊነቱን ተፈታኙ / ዩኒቨርሲቲው የሚወስድ ይሆናል፣ ፈተና ላይ ለመቀመጥም አያስችልም፣
በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ዩኒቨርሲቲዎች የተመዝጋቢዎች ዝርዝር እና የተሰበሰበ ገንዘብ ገቢ ካላደረጉ ምንም ተፈታኝ እንዳልመዘገቡ ይቆጠራል / ኃላፊነት ይወስዳሉ፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ማንነትን የሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ፣ እስክሪቢቶ እና የተፈቀዱ ማጣቀሻዎችን ብቻ ይዞ መገኘት ይገባል፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ከተፈቀዱ ማጣቀሻዎች ውጪ ማንኛውንም ዓይነት ፅሑፍ ያለበት ወረቀትም ሆነ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ፣ የእጅ ሰዓት፣ ተፈታኙ ከስራ መደቡ አንፃር ህጋዊ የሆነ ሆኖም በፈተና ጣቢያ የማይፈቀድ ነገር ይዞ መገኘት እንዲሁም ሌሎች በፈተና አሰጣጥ ወቅት የማይፈቀዱ ነገሮችን ይዞ መገኘት አይቻልም፣ በአራተኛው የፈተና ቀናት ማንነትን ከሚገልጽ ህጋዊ መታወቂያ እና ከእስክሪቢቶ በስተቀር ምንም ነገር ይዞ መምጣት አይፈቀድም፡፡ በቅድመ ፈተና ፍተሻ ወቅት በፈተና መስጫ ግቢ እና ክፍል ውስጥ ይህ ሆኖ ከተገኘ ሙሉ የፈተና ውጤት ይሰረዛል፣
በፈተና አሰጣጥ ወቅት ምንም ዓይነት ነገር መቀያየር እና መዋዋስ የማይቻል በመሆኑ ሁሉም ተፈታኝ በግሉ የሚጠቀምበትን ነገር ይዞ መገኘት ይገባዋል፣
የፈተና አሰጣጥ ከተጀመረ በኋላ በተለያየ ህጋዊም ሆነ ህጋዊ ባለሆነ ምክንያት ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ አርፍዶ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተና ግቢም ሆነ ክፍል ውስጥ መግባት አይፈቀድም፣ በመሆኑም ለፍተሻ ሂደት እና ለቅድመ ዝግጅት ሲባል ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከሚሰጥበት ሰዓት አንድ ሰዓት ቀደም ብሎ ወደ ፈተና ጣቢያ ጊቢ እንዲደርስ ይመከራል፣
ውጤትን በተመለከተ ቅሬታ ካለ በዩኒቨርሲቲ በኩል በደብዳቤ ለኢንስቲትዩቱ የሚቀርብ ይሆናል፡፡

ኢንስቲትዩቱ -
መልካም የቅድመ ዝግጅት ጊዜ!
ማስታወሻ:- በቀጣይ ባሉት ቀናት እና ሳምንት ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ማስታወቂያዎችን ይከታተሉ / ለሌሎች ያሳውቁ፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig via @Lawsocieties
#በጋራ አብሮ የመስራት ውል (joint Venture Agreement)
በአዲሱ የንግድ ህግ አንቀጽ 234 መሰረት የአሽሙር ማህበር ማለት “ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸው በሚያደርጉት ስምምነት መሠረት የሚያቋቁሙት በሦስተኛ ወገኖች የማይታወቅ የሕግ ሰውነት የሌለው የንግድ ማኅበር ነው፡፡” በማለት ይገልጸዋል፡፡
በዚህ አንቀጽ መሰረት ይህ አይነት ማህበር ስለሌሎች የንግድ ማህበሮች የተደነገጉት የማስመዝገብ ስርዓቶች በዚህ ማህበር ላይ ተፈጻሚ እንደማይሆኑ ይገልጻል፡፡
በመሆኑም ተገልጋዮች በጋራ አብሮ የመስራት ውል(የአሽሙር ውል) ለመዋዋል ወደ መስሪያ ቤታችን ሲመጡ ማሟላት የሚገባቸውን መስፈርቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡
. በህግ አግባብ የተዘጋጀ የውል ሰነድ፣
. የተዋዋይ ወገኖች ወገኖች የተናጠል ወይም የየግላቸው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣
. ተዋዋይ የንግድ ማህበር ከሆነ የመመስረጃ ጽሁፍ፣ የንግድ ዋና ምዝገባ እና እንደአስፈላጊነቱ ቃለ-ጉባኤ፣
. በውል ሰነዱ ውስጥ በዝርዝር የተገለጸና ማስረጃ የሚያስፈልገው የባለቤትነት ወይም የመብት ማጣቀሻ ካለ ይህንኑ የሚያረጋግጣ ማስረጃ፣
. የተዋዋይ ወገኖች የታደሰ መታወቂያ፡፡
ማሳሰቢያ፡- ተገልጋዮች የተባሉትን ዝርዝር ነገሮች አሟልተው ሲቀርቡ ለዚህ አገልግሎት የሚወስደው ጊዜ 25 ደቂቃ ነው፡፡
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ( share ) በማድረግ ብልሹ አሰራር እና ሙስናን ይከላከሉ፡፡
#አለ_ህግ #Ale_Hig via @Lawsocieties
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የብሔራዊ የምስለ ችሎት ውድድር አሸናፊ ሆኗል።

ከ19 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የተወከሉ የሕግ ተማሪዎች በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ በቆየው የምስለ ችሎት/Moot Court የመጨረሻ ዙር ውድድር ተካፍለዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተወዳዳሪዎች መካከል የመጨረሻ ውድድር ተካሂዶ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቋል።

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ እና አርሲ ዩኒቨርሲቲ ሦሥተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡

ብሔራዊ ውድድሩ "በስደተኞች ሕግ" ላይ ትኩረት ያደረገ እንደነበር ተገልጿል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሕግና ገቨርናንስ ኮሌጅ የሕግ ትምህርት ቤት ከሲቪል ሶሳይቲ ሪሶርስ ሴንተር (Civil Society Resource Center) ጋር በመተባበር ውድድሩን ማዘጋጀታቸው ተመላክቷል።
#አለ_ህግ #Ale_Hig via @Lawsocieties