ለ) የኣቀራረቡ ፎርም ሲታይ ደግሞ በቁ.130 (1) ወይም (2) መሰረት የሚቀርበው መቃወሚያም ሆነ ዓቃቤ ሕጉ ለመቃወሚያው የሚሰጠው መልስ ሁሉ በቃል መቅረብ እንዳለበት ከቁ.131 (1) መረዳት ይቻላል፡፡ ተደጋጋሚ ስልጠናዎች እየተሰጡ ኣሁን ኣሁን እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም በተግባር ሲሰራበት የነበረና ኣሁንም ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል ብሎ በኣስተማማኝ መናገር የማይቻለው፤ መቃወሚያ ለማቅረብ ጊዜ መስጠት ፣ መቃወሚያው በፅሑፍ ማቅረብ ፣ ዓ/ሕግ የመቃወሚያው ግልባጭ እንዲደርሰው ማድረግ ፣ ዓ/ሕግ በሚሰጠው ቀነ ቀጠሮ መልሱ በፅሑፍ ያቀርባል ፣ ተከሳሹ በበኩሉ የመልስ መልስ በፅሑፍ ለማቅረብ ጊዜ ይሰጠዋል ፣ በመጨረሻ ፍ/ቤቱ የተከሳሽ መቃወሚያና የዓ/ሕግ መልስ ከሕጉ ጋር ኣገናዝቦ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ይሰጣል፤ ምናልባት ምርመራው ያላለቀ ከሆነ ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠት እንደተጠበቀ ሆኖ ፍ/ቤቱ ብይን ይሰጣል፡፡ ይህ የተንዛዛ ኣካሄድ ሕጉ ከሚያዘው ውጭ መሆኑን ግንዛቤ ሊወሰድበት ይገባል፡፡
ሐ) ከመቃወሚያ ጋር ተያይዞ ሌላ መታየት ያለበት ነጥብ በመቃወሚያነት መቅረብ ያለበት በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ከተዘተዘሩት ምክንያቶች ሲገኝ ብቻ ነው ወይስ ከዚያ ውጭ የሆኑ ምክንያቶች ሲገኙም ማቅረብ ይፈቀደል የሚለው ነው፡፡ በዚህ ዙርያ ሁለት ኣስተሳሰቦች ይራመዳሉ፡፡ በአንድ በኩል በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ባይሸፈንም የክሱ መሰማት ሂደት እንዳይቀጥል የሚያደርጉ ሌሎቸ ምክንያቶች በተገኙ ጊዜም ተከሳሽ እንዲያነሳ ሊፈቀድለት ይገባል የሚሉ ኣሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቁ.130 ሌላ የመቃወሚያ ነጥብ በማይጨምር ሁኔታ (exclusively) ዘርዝሮ ያስቀመጠ በመሆኑ ከዚያ ውጭ የሚቀር ተቃውሞ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባም የሚል ሓሳብ የሚያራምዱ አሉ ብቻ ሳይሆን ኣብዛኛው ጊዜ በተግባር የሚሰራበትም ይህ ኣቋም ነው ፡፡ እንደ የሞጁሉ ኣዘጋጅ እምነትም በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 130 ስር የማይሸፈን የተቃውሞ ነጥብ በሚነሳበት ጊዜ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባውም፤ ምክንያቱም በዛ ስር ያልተጠቀሰ ነጥብ በማያካትት እና በተሟላ ሁኔታ (exclusively and exhaustively) የተቀረፀ ነው፡፡
2. መቃወሚያውን ስለመመርመርና ስለመወሰን
በቁ. 13. (2) መሰረት የሚቀርበውን ማንኛውንም መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ በመዝገቡ ከፃፈ በላ ዓ/ሕጉ መልስ እንዳለው ይጠይቃል፡፡ የቀረበውን መቃወሚያ ሕግን በመጥቀስ ለመወሰን የሚቻል ከሆነ ወይም ዓ/ሕጉ መቃወሚያውን ካልተቃወመ ፍ/ቤቱ ወድያው ይወስናል (ቁ. 131 (1)) ፡፡ ፍ/ቤቱ ጉዳዩን ለማጣራት ማስረጃ መቅረቡ ኣስፈላጊ ሆኖ ካገኘውና ማስረጃ ሳይቀርብ ወድያው ውሳኔ (ብይን) መስጠት የማይቻል በሆነ ጊዜ ኣስፈላጊው ማስረጃ እንዲቀርብ ማዘዝ ይችላል (ቁ. 131 (3)) ፡፡ የተፈለገው ማስረጃ አስቀርቦ ከመረመረ በላ ፍ/ቤቱ ወዲያው ውሳኔ መስጠት እንዳለበት ቁጥር 131 (4) ይደነግጋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመቃወሚያው ላይ የሚሰጠው ውሳኔ /ብይን/ እንደየ መቃወሚያው ዓይነት ሊለያይ ይችላል፡፡ ይኸዉም፡-
ሀ) የቀረበው መቃወሚያ የሕግ ድጋፍ የሌለው ከሆነ ወይም በማስጃ ካልተደገፈ መቃወሚያውን ውድቅ ያደርጋል ፣
ለ) በቁ. 130/ 2/ለ/፣ /ሐ/፣ ወይም/ሰ/ መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱን ዘግቶ ተከሳሹን ያሰናብታል ፣
ሐ) በቁ.130/2/ሀ/ መሰረት የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ጉዳዩ በተጀመረበት ፍ/ቤት እንዲቀጥል በማዘዝ መዝገቡን ይዘጋል ፣
መ) በቁ. 130(2) (መ) መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱ ተነጥሎ እንዲታይ ያዝዛል ፣
ሠ) በቁ. 130 /2/ሠ/ የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ኣስፈላጊው ፈቃድ እስኪሰጥ መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል ፣
ረ) በቁ. 130/2/ረ/ የቀረበ ከሆነ ደግሞ ኣስቀድሞ መፈፀም ያለበት ስርዓት እስኪፈፀም መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል፡፡
ከዚህ በላይ በፊደል “ለ” የተጠቀሰውን እንዳለ ሆኖ ተከሳሹ ሙሉ በሙሉ ሃላፊ ባለመሆኑ ክሱ በተዘጋ ጊዜ የተከሳሹ ሁኔታ በፀጥታ ወይም በህዝብ ሰላማዊ ኑሮ ላይ ሁከት ወይም ኣደጋ የሚያደርስ መስሎ ከታየው ተከሳሹ ተገቢ በሆነ ስፍራ ወይም ሕክምና በሚያገኝበት ቦታ ተወስኖ እንዲቀመጥ ፍ/ቤቱ ያዝዛል ( የወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 208 እና የወ/ሕግ ዓንቀፅ 130 እስከ 132 ) ፡፡
via #Legal_Service
©Tsegaye Demeke
ሐ) ከመቃወሚያ ጋር ተያይዞ ሌላ መታየት ያለበት ነጥብ በመቃወሚያነት መቅረብ ያለበት በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ከተዘተዘሩት ምክንያቶች ሲገኝ ብቻ ነው ወይስ ከዚያ ውጭ የሆኑ ምክንያቶች ሲገኙም ማቅረብ ይፈቀደል የሚለው ነው፡፡ በዚህ ዙርያ ሁለት ኣስተሳሰቦች ይራመዳሉ፡፡ በአንድ በኩል በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ.130 ላይ ባይሸፈንም የክሱ መሰማት ሂደት እንዳይቀጥል የሚያደርጉ ሌሎቸ ምክንያቶች በተገኙ ጊዜም ተከሳሽ እንዲያነሳ ሊፈቀድለት ይገባል የሚሉ ኣሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቁ.130 ሌላ የመቃወሚያ ነጥብ በማይጨምር ሁኔታ (exclusively) ዘርዝሮ ያስቀመጠ በመሆኑ ከዚያ ውጭ የሚቀር ተቃውሞ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባም የሚል ሓሳብ የሚያራምዱ አሉ ብቻ ሳይሆን ኣብዛኛው ጊዜ በተግባር የሚሰራበትም ይህ ኣቋም ነው ፡፡ እንደ የሞጁሉ ኣዘጋጅ እምነትም በወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 130 ስር የማይሸፈን የተቃውሞ ነጥብ በሚነሳበት ጊዜ ተቀባይነት ሊያገኝ ኣይገባውም፤ ምክንያቱም በዛ ስር ያልተጠቀሰ ነጥብ በማያካትት እና በተሟላ ሁኔታ (exclusively and exhaustively) የተቀረፀ ነው፡፡
2. መቃወሚያውን ስለመመርመርና ስለመወሰን
በቁ. 13. (2) መሰረት የሚቀርበውን ማንኛውንም መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ በመዝገቡ ከፃፈ በላ ዓ/ሕጉ መልስ እንዳለው ይጠይቃል፡፡ የቀረበውን መቃወሚያ ሕግን በመጥቀስ ለመወሰን የሚቻል ከሆነ ወይም ዓ/ሕጉ መቃወሚያውን ካልተቃወመ ፍ/ቤቱ ወድያው ይወስናል (ቁ. 131 (1)) ፡፡ ፍ/ቤቱ ጉዳዩን ለማጣራት ማስረጃ መቅረቡ ኣስፈላጊ ሆኖ ካገኘውና ማስረጃ ሳይቀርብ ወድያው ውሳኔ (ብይን) መስጠት የማይቻል በሆነ ጊዜ ኣስፈላጊው ማስረጃ እንዲቀርብ ማዘዝ ይችላል (ቁ. 131 (3)) ፡፡ የተፈለገው ማስረጃ አስቀርቦ ከመረመረ በላ ፍ/ቤቱ ወዲያው ውሳኔ መስጠት እንዳለበት ቁጥር 131 (4) ይደነግጋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመቃወሚያው ላይ የሚሰጠው ውሳኔ /ብይን/ እንደየ መቃወሚያው ዓይነት ሊለያይ ይችላል፡፡ ይኸዉም፡-
ሀ) የቀረበው መቃወሚያ የሕግ ድጋፍ የሌለው ከሆነ ወይም በማስጃ ካልተደገፈ መቃወሚያውን ውድቅ ያደርጋል ፣
ለ) በቁ. 130/ 2/ለ/፣ /ሐ/፣ ወይም/ሰ/ መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱን ዘግቶ ተከሳሹን ያሰናብታል ፣
ሐ) በቁ.130/2/ሀ/ መሰረት የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ጉዳዩ በተጀመረበት ፍ/ቤት እንዲቀጥል በማዘዝ መዝገቡን ይዘጋል ፣
መ) በቁ. 130(2) (መ) መሰረት የቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት ካገኘ ክሱ ተነጥሎ እንዲታይ ያዝዛል ፣
ሠ) በቁ. 130 /2/ሠ/ የቀረበ መቃወሚያ ከሆነ ኣስፈላጊው ፈቃድ እስኪሰጥ መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል ፣
ረ) በቁ. 130/2/ረ/ የቀረበ ከሆነ ደግሞ ኣስቀድሞ መፈፀም ያለበት ስርዓት እስኪፈፀም መዝገቡን ለጊዜው ይዘጋዋል፡፡
ከዚህ በላይ በፊደል “ለ” የተጠቀሰውን እንዳለ ሆኖ ተከሳሹ ሙሉ በሙሉ ሃላፊ ባለመሆኑ ክሱ በተዘጋ ጊዜ የተከሳሹ ሁኔታ በፀጥታ ወይም በህዝብ ሰላማዊ ኑሮ ላይ ሁከት ወይም ኣደጋ የሚያደርስ መስሎ ከታየው ተከሳሹ ተገቢ በሆነ ስፍራ ወይም ሕክምና በሚያገኝበት ቦታ ተወስኖ እንዲቀመጥ ፍ/ቤቱ ያዝዛል ( የወ/መ/ሕ/ስ/ስ/ቁ. 208 እና የወ/ሕግ ዓንቀፅ 130 እስከ 132 ) ፡፡
via #Legal_Service
©Tsegaye Demeke
ውል ማለት ምን ማለት ነው ? የዉል አመሠራረት ሲባልስ በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል?
***
ሰላም እንዴትናችሁ ውድ የፌስቡክ ገጻችን ተከታታዮች ለዛሬ ውል ሲባል ምን ማለት ነው? የዉል አመሠራረት ሲባልስ በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አንድ የጹሁፍ ጥንቅር ወደ እናንተ ልናደርስ ወደድን መልካም ንባብ ተመኘን፡፡
የሰዉ ልጆች በዚች ምድር ላይ ሲኖሩ የተለያዩ ህጋዊ ውጤት ያላቸዉን ድርጊቶች ያከናዉናሉ፡፡ ለአብነትም ቤት ይከራያሉ ያከራያሉ፣ ጋብቻ ይፈፅማሉ፣ ንብረት ይሸጣሉ ይገዛሉ፣ ወዘተ፡፡ ህጋዊ ዉጤትም ከሚያስከትሉ ተግባራት አንዱ ውል ነዉ፡፡ ውል ሰዎች በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሕይወታቸዉ ዉስጥ ከሚያከናውኗቸው የግንኙነት መገለጫዎች አንዱ ሲሆን ከፍትሐብሔር ግዴታ አንዱ ዘርፍ ነው፡፡
ሰዎች በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴያቸዉ ዉስጥ የተለያዩ ውሎችን ይፈፅማሉ፡፡ ወደ ሱቅ ሂደዉ ሸቀጥ ሲገዙ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ ታክሲ ሲጠቀሙ፣ ለንግድም ሆነ ለመኖሪያ ቤት ሲከራዩ፣ ወዘተ፡፡ እኒህ የውል ግዴታ ዉስጥ የሚገቡት የማህበረሰቡ አካል የሆኑ ሰዎች ናቸዉ፡፡ በሌላ አባባል ውል የሚኖረዉ የውል ግዴታ ውስጥ የሚገቡ (የሚዋዋሉ) ሰዎች ሲኖሩ ነዉ፡፡ ሰዎች ስንል በፍትሐብሔር ህጉ መሰረት የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ህጋዊ ሰዉነት የተሰጣቸው ድርጅቶች ናቸዉ፡፡ ውድ አንባቢያን ለመግቢያ ያክል ይህን ካልን አሁን ደግሞ የውልን ትርጓሜ እናያለን
ውል ማለት ምን ማለት ነው
ውል ምን ማለት ነዉ? የሚለዉን ስንመለከት የዘርፉ ሙሁራን እና የፍትሐብሔር ህጋችን የተቀራረበ ትርጉም ሰጥተውት እናገኛለኝ፡፡ በእዉቁ የህግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎዉ ላይ “ዉል ማለት በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸዉ አንድን ድርጊት ለማድረግ ወይንም ላለማድርግ በመስማማት ግዴታ የሚፈጥሩበት መንገድ ነዉ” ሲል ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ ፕሮፌስር ጥላሁን ተሾመ የኢትዮጳያ የዉል ህግ መሰረተ ሀሳቦች በሚለዉ መፅሃፋቸዉ ዉስጥ “ዉል አንድን ግዴታ ወይም ከዚሁ ግዴታ የተያያዙ ሌሎች በርከት ያሉ ግዴታዎችን የሚያቋቁም ተግባርን የሚያመለክት አነጋገር ነዉ፡፡ በዚህ ግዴታ ባለገንዘብ የሆነዉ ወገን አንድ ነገር እንዲፈጸምለት የመጠየቅ መብት የሚኖረዉ ሲሆን ባለዕዳዉ ደግሞ አንድን ነገር የመፈጸም ግዴታ ይጠበቅበታል” በማለት አብራርተዉ ገልፀዉታል፡፡ እንዲሁም በፍትሐብሔር ህጋችን መፅሃፍ አምስት ስለ ግዴታዎች በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1675 ላይ “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መሀል የሚደረግ ስምምነት ነዉ” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡
የዉል አመሠራረት
ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ስምምነት ነዉ፡፡ ነገር ግን ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ ለአፈፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡ ይህም ማለት ተዋዋይ ወገኖች የተስማሙበትን ነገር እንደ ስምምነታቸዉ ባይፈፅሙ ያልፈፀሙትን ነገር በህግ ተገደዉ እንዲፈፅሙ ይደረጋሉ፡፡ ይህም የሚያሳየን ዉል በተስማሚዎቹ አካላት መካከል እንደ ህግ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ነዉ፡፡
ዉል በተወያይ ወገኖች መካከል ህጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ አስቀድሞ የዉል አመሰራረቱ ህጋዊ መስፈርቱን ማሟላት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ስለ ዉል አመሰራረት በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1678 ላይ በግልፅ እንደተቀመጠዉ የሚፀና ዉል ነዉ ለማለት መሟላት ያለባቸዉን ሁኔታዎች አስቀምጧል፡፡ እነሱም፡
1ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል መሆኑን፡፡ ይህም ማለት በህግ ፊት የሚፀና ዉል ለማድረግ ተዋዋዮች በህግ ችሎታ ያላቸዉ መሆን አለባቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ላይ ስለ ችሎታ በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 192 ላይ በመርህ ደረጃ ማንኛዉም ሰዉ በህግ ችሎታ እንደሌለዉ ካልተገለፀ በቀር ማንኛዉንም ህጋዊ ድረጊት ለማድረግ ችሎታ እንዳለዉ እንደሚቆጠር ተደንግጓል፡፡ በዚሁ ህግ አንቀፅ 193 ላይ እንደተደነገገዉ እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡ ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ህጋዊ ተግባር ነዉ ስለሆነም እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ዉል መዋዋል አይችልም፡፡
2ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ መሆኑ፡፡ ይህም ማለት ተወያይ ወገኖች ዉል ዉስጥ የሚገቡት ያለማንም ጫና አድራጊነት በራሳቸዉ ፍቃድ መሆን አለበት ማለት ነዉ፡፡ አንድ የዉል ግዴታ የተቋቋመ መሆኑ የሚረጋገጠዉ የተዋዋዮቹ ፈቃድ በህግ አግባብ መገለፁ ሲታወቅ ነዉ፡፡ ተዋዋዮቹ በመሀከላቸዉ በህግ ፊት የሚፀና ግዴታ ለማቋቋምና ይህም ግዴታ በሚያስከትለዉ ዉጤት ለመገዛት ስምምነት ያላቸዉ መሆኑ ይፋ ሲያደርጉ ፈቃዳቸዉን ገለፁ እንላለን፡፡ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀፅ 1679 ላይ ይህን አባባላችን በሚያጠናክር መልኩ “ዉል ተዋዋዮች በገቡባቸዉ ግዴታዎችና እነዚህም አስገዳጅ እንዲሆኑ የተስሚ መብትን በሚገልፀዉ የፈቃድ መስጠት ላይ የተመሰረተ ነዉ” በማለት ተደንግጓል፡፡
3ኛ. ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት (ዉል ዉስጥ የሚገቡበት) ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆኑ፡፡ የዉሉ ፍሬ ነገር በሰዉ ልጅ አቅም መፈጸም የሚችል እና ህጋዊና ሞራላዊ የሆነ መሆን አለበት፡፡ በሰዉ ልጅ አቅም መፈፀም የሚቻል ተግባር ማለት የሰዉ ልጅ በተፈጥሮዉ ማከናዉን የሚችለዉ ማለት ነዉ፡፡ ለአብነት የዉሉ ፍሬ ነገር እንደ እርግብ መብረር ቢሆን በሰዉ ልጅ ተፈጥሮ የማይቻል ተግባር ነዉ፡፡ ሌለዉ የዉሉ ፍሬ ነገር በህግ ያልተከለከለ ወይም ህገ-ወጥ እና በህብረተሰቡ ባህልና ወግ ተቀባይነት ያለዉ ነገር ላይ (በሌላ አባባል ከህብረተሰቡ ሞራል ጋር ያልተቃረነ ያልሆነ) መሆን አለበት፡፡ ለአብነት ፍሬ ነገሩ ሰዉ ለመግደል ቢሆን በህግ የተከለከለ ነዉ፡፡
4ኛ. የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ በህግ (ፎርም) ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጡ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም የማያስፈልግ መሆኑ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀፅ 1678(3) ላይ እንደተደነገገዉ በግልፅ በህግ ይህን የዉል ፎርም ተከተሉ ተብሎ ካልተደነገገ በቀር ተዋዋይ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት አይነት ማድረግ ይችላሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዚሁ ህግ አንቀፅ 1719(1) ላይ ተዋዋይ ወገኖች የመዋዋል ነፃነት እንዳላቸዉ ሁሉ የሚዋዋሉበትን ዉል አቀራረፅ የመወሰን ነፃነትም እንዳለቸዉ በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በተለየ ሁኔታ በህግ ዉሉ በዚህ መልክ ይቀመጥ ካልተባለ በስተቀር ተዋዋዮቹ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት ፎርም ማድረግ ይችላሉ፡፡
ውድ አንባቢያን ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁን በዚሁ አበቃን በቀጣይ የቤት ኪራይ ውል ሲባል ምን ማለት ነው በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አርዕስት አንድ ጥንቅር ከትበን ወደ እናንተ እናደርሳለን እስክንገናኝ መልካም ጊዜ ተመኝን ሰላም፡፡
https://t.me/lawsocieties
***
ሰላም እንዴትናችሁ ውድ የፌስቡክ ገጻችን ተከታታዮች ለዛሬ ውል ሲባል ምን ማለት ነው? የዉል አመሠራረት ሲባልስ በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አንድ የጹሁፍ ጥንቅር ወደ እናንተ ልናደርስ ወደድን መልካም ንባብ ተመኘን፡፡
የሰዉ ልጆች በዚች ምድር ላይ ሲኖሩ የተለያዩ ህጋዊ ውጤት ያላቸዉን ድርጊቶች ያከናዉናሉ፡፡ ለአብነትም ቤት ይከራያሉ ያከራያሉ፣ ጋብቻ ይፈፅማሉ፣ ንብረት ይሸጣሉ ይገዛሉ፣ ወዘተ፡፡ ህጋዊ ዉጤትም ከሚያስከትሉ ተግባራት አንዱ ውል ነዉ፡፡ ውል ሰዎች በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሕይወታቸዉ ዉስጥ ከሚያከናውኗቸው የግንኙነት መገለጫዎች አንዱ ሲሆን ከፍትሐብሔር ግዴታ አንዱ ዘርፍ ነው፡፡
ሰዎች በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴያቸዉ ዉስጥ የተለያዩ ውሎችን ይፈፅማሉ፡፡ ወደ ሱቅ ሂደዉ ሸቀጥ ሲገዙ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመንቀሳቀስ ታክሲ ሲጠቀሙ፣ ለንግድም ሆነ ለመኖሪያ ቤት ሲከራዩ፣ ወዘተ፡፡ እኒህ የውል ግዴታ ዉስጥ የሚገቡት የማህበረሰቡ አካል የሆኑ ሰዎች ናቸዉ፡፡ በሌላ አባባል ውል የሚኖረዉ የውል ግዴታ ውስጥ የሚገቡ (የሚዋዋሉ) ሰዎች ሲኖሩ ነዉ፡፡ ሰዎች ስንል በፍትሐብሔር ህጉ መሰረት የተፈጥሮ ሰዎች ወይም ህጋዊ ሰዉነት የተሰጣቸው ድርጅቶች ናቸዉ፡፡ ውድ አንባቢያን ለመግቢያ ያክል ይህን ካልን አሁን ደግሞ የውልን ትርጓሜ እናያለን
ውል ማለት ምን ማለት ነው
ውል ምን ማለት ነዉ? የሚለዉን ስንመለከት የዘርፉ ሙሁራን እና የፍትሐብሔር ህጋችን የተቀራረበ ትርጉም ሰጥተውት እናገኛለኝ፡፡ በእዉቁ የህግ መዝገበ ቃላት ብላክስ ሎዉ ላይ “ዉል ማለት በሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በመካከላቸዉ አንድን ድርጊት ለማድረግ ወይንም ላለማድርግ በመስማማት ግዴታ የሚፈጥሩበት መንገድ ነዉ” ሲል ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ ፕሮፌስር ጥላሁን ተሾመ የኢትዮጳያ የዉል ህግ መሰረተ ሀሳቦች በሚለዉ መፅሃፋቸዉ ዉስጥ “ዉል አንድን ግዴታ ወይም ከዚሁ ግዴታ የተያያዙ ሌሎች በርከት ያሉ ግዴታዎችን የሚያቋቁም ተግባርን የሚያመለክት አነጋገር ነዉ፡፡ በዚህ ግዴታ ባለገንዘብ የሆነዉ ወገን አንድ ነገር እንዲፈጸምለት የመጠየቅ መብት የሚኖረዉ ሲሆን ባለዕዳዉ ደግሞ አንድን ነገር የመፈጸም ግዴታ ይጠበቅበታል” በማለት አብራርተዉ ገልፀዉታል፡፡ እንዲሁም በፍትሐብሔር ህጋችን መፅሃፍ አምስት ስለ ግዴታዎች በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1675 ላይ “ዉል ማለት ንብረታቸዉን የሚመለከቱ ግዴታዎችን ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸዉ ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መሀል የሚደረግ ስምምነት ነዉ” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡
የዉል አመሠራረት
ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ስምምነት ነዉ፡፡ ነገር ግን ዉል ስምምነት ቢሆንም ከሌሎች ስምምነቶች የሚለየዉ ለአፈፀሙ ከበስተጀርባዉ የሕግ ድጋፍ ያለዉ ስምምነት መሆኑ ላይ ነዉ፡፡ ይህም ማለት ተዋዋይ ወገኖች የተስማሙበትን ነገር እንደ ስምምነታቸዉ ባይፈፅሙ ያልፈፀሙትን ነገር በህግ ተገደዉ እንዲፈፅሙ ይደረጋሉ፡፡ ይህም የሚያሳየን ዉል በተስማሚዎቹ አካላት መካከል እንደ ህግ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ነዉ፡፡
ዉል በተወያይ ወገኖች መካከል ህጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ አስቀድሞ የዉል አመሰራረቱ ህጋዊ መስፈርቱን ማሟላት አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ስለ ዉል አመሰራረት በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 1678 ላይ በግልፅ እንደተቀመጠዉ የሚፀና ዉል ነዉ ለማለት መሟላት ያለባቸዉን ሁኔታዎች አስቀምጧል፡፡ እነሱም፡
1ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ ለመዋዋል ችሎታ ባላቸዉ ሰዎች መካከል መሆኑን፡፡ ይህም ማለት በህግ ፊት የሚፀና ዉል ለማድረግ ተዋዋዮች በህግ ችሎታ ያላቸዉ መሆን አለባቸዉ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን ላይ ስለ ችሎታ በሚደነግገዉ ክፍል አንቀፅ 192 ላይ በመርህ ደረጃ ማንኛዉም ሰዉ በህግ ችሎታ እንደሌለዉ ካልተገለፀ በቀር ማንኛዉንም ህጋዊ ድረጊት ለማድረግ ችሎታ እንዳለዉ እንደሚቆጠር ተደንግጓል፡፡ በዚሁ ህግ አንቀፅ 193 ላይ እንደተደነገገዉ እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ሰዉ ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ችሎታ እንደሌለዉ ይቆጠራል፡፡ ከላይ እንደተገለፀዉ ዉል ህጋዊ ተግባር ነዉ ስለሆነም እድሜዉ ለአቅመ አዳም/ሄዋን ያልደረሰ/ሰች ወይም አይምሮዉ ህመም ያለበት ወይም በፍርድ ቤት የተከለከለ ሰዉ ዉል መዋዋል አይችልም፡፡
2ኛ. ዉል የሚፈፀመዉ በተወያያቹ ነፃ ፍቃድ ብቻ መሆኑ፡፡ ይህም ማለት ተወያይ ወገኖች ዉል ዉስጥ የሚገቡት ያለማንም ጫና አድራጊነት በራሳቸዉ ፍቃድ መሆን አለበት ማለት ነዉ፡፡ አንድ የዉል ግዴታ የተቋቋመ መሆኑ የሚረጋገጠዉ የተዋዋዮቹ ፈቃድ በህግ አግባብ መገለፁ ሲታወቅ ነዉ፡፡ ተዋዋዮቹ በመሀከላቸዉ በህግ ፊት የሚፀና ግዴታ ለማቋቋምና ይህም ግዴታ በሚያስከትለዉ ዉጤት ለመገዛት ስምምነት ያላቸዉ መሆኑ ይፋ ሲያደርጉ ፈቃዳቸዉን ገለፁ እንላለን፡፡ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀፅ 1679 ላይ ይህን አባባላችን በሚያጠናክር መልኩ “ዉል ተዋዋዮች በገቡባቸዉ ግዴታዎችና እነዚህም አስገዳጅ እንዲሆኑ የተስሚ መብትን በሚገልፀዉ የፈቃድ መስጠት ላይ የተመሰረተ ነዉ” በማለት ተደንግጓል፡፡
3ኛ. ተወያይ ወገኖች የሚዋዋሉበት (ዉል ዉስጥ የሚገቡበት) ጉዳይ በእርግጠኝነት የሚቻል እና ህጋዊና ሞራላዊ ጉዳይ ላይ መሆኑ፡፡ የዉሉ ፍሬ ነገር በሰዉ ልጅ አቅም መፈጸም የሚችል እና ህጋዊና ሞራላዊ የሆነ መሆን አለበት፡፡ በሰዉ ልጅ አቅም መፈፀም የሚቻል ተግባር ማለት የሰዉ ልጅ በተፈጥሮዉ ማከናዉን የሚችለዉ ማለት ነዉ፡፡ ለአብነት የዉሉ ፍሬ ነገር እንደ እርግብ መብረር ቢሆን በሰዉ ልጅ ተፈጥሮ የማይቻል ተግባር ነዉ፡፡ ሌለዉ የዉሉ ፍሬ ነገር በህግ ያልተከለከለ ወይም ህገ-ወጥ እና በህብረተሰቡ ባህልና ወግ ተቀባይነት ያለዉ ነገር ላይ (በሌላ አባባል ከህብረተሰቡ ሞራል ጋር ያልተቃረነ ያልሆነ) መሆን አለበት፡፡ ለአብነት ፍሬ ነገሩ ሰዉ ለመግደል ቢሆን በህግ የተከለከለ ነዉ፡፡
4ኛ. የዉል አቀራረጹ ወይም አፃፃፉ በህግ (ፎርም) ተለይተዉ የተቀመጡ ወይም ተዋዋይ ወገኖች ተለይቶ እንዲቀመጡ ከተስማሙበት የዉል ጉዳይ በቀር የተለየ የዉል ፎርም የማያስፈልግ መሆኑ፡፡ በፍትሐብሔር ህጋችን አንቀፅ 1678(3) ላይ እንደተደነገገዉ በግልፅ በህግ ይህን የዉል ፎርም ተከተሉ ተብሎ ካልተደነገገ በቀር ተዋዋይ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት አይነት ማድረግ ይችላሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዚሁ ህግ አንቀፅ 1719(1) ላይ ተዋዋይ ወገኖች የመዋዋል ነፃነት እንዳላቸዉ ሁሉ የሚዋዋሉበትን ዉል አቀራረፅ የመወሰን ነፃነትም እንዳለቸዉ በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በተለየ ሁኔታ በህግ ዉሉ በዚህ መልክ ይቀመጥ ካልተባለ በስተቀር ተዋዋዮቹ ወገኖች ዉላቸዉን በፈለጉት ፎርም ማድረግ ይችላሉ፡፡
ውድ አንባቢያን ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁን በዚሁ አበቃን በቀጣይ የቤት ኪራይ ውል ሲባል ምን ማለት ነው በአገራችን የህግ ማዕቀፍ እንዴት ይታያል በሚል አርዕስት አንድ ጥንቅር ከትበን ወደ እናንተ እናደርሳለን እስክንገናኝ መልካም ጊዜ ተመኝን ሰላም፡፡
https://t.me/lawsocieties
Telegram
ሕግ ቤት
ሕግ ቤት Access legal information
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ ያማክሩ
@HigBet #ሕግ_ቤት
lawsocieties@gmail.com
https://www.facebook.com/Ethiopianlegalinfo/
በመኪና የሚደርስ ጉዳት ሃላፊነት የማን ነዉ ❓
የመኪና አደጋውን ያደረሰው ሰዉ መኪናዉን ለማንቀሳቀስ ወይም ለመንዳት ያልተፈቀደለት ሰው እንኳን ቢሆን መኪናዉ ለሚያደርሰዉ ጉዳት የመኪናዉ ባለቤት አላፊ ይሆናል ::
የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 2ዐ81 /1/ እንደሚያመለክተዉ : "አደጋውን ያደረሰው ሰዉ መኪናዉን ለማሽከርከር ያልተፈቀደለት ሰው ሆኖ ይህ ያልተፈቀደለት ግለሰብ እየነዳ ጉዳት ቢያደርስ የመኪናዉ ባለቤት አላፊ ይሆናል" :: ነገር ግን አደጋው በደረሰ ጊዜ መኪናው ተስርቆበት ከሆነና ይህንንም ማስረዳት ከቻለ የመኪናዉ ባለቤት ለደረሰዉ ጉዳት አላፊ አይሆንም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በቁጥር 2ዐ82/1/ መሠረት አንድ ሰው መኪናውን ለግል ጥቅሙ ሲገለገልበት መኪናው ጉዳት ካደረሰ ለደረሰው ጉዳት አላፊ ሊሆን የሚችለው ይህ ሰው ነው፡፡
አንድ የመኪና ባለቤት መኪናውን ለማንቀሳቀስ ሠራተኛ ሊቀጥር ይችላል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ መኪናዉ ጉዳት ያደረሰዉ በሠራተኛው ጥፋት ካለሆነ በስተቀር በቁጥር 2ዐ82/2/ መሠረት መኪናዉ ላደረሰዉ ጉዳት አላፊ የሚሆነው የመኪናዉ ባለቤት ነው፡፡
ሳሙኤል ግርማ
#ሕግ_አገልግሎት_
#Ethiopia #LegalService #Lawyer #Samuel Girma
የመኪና አደጋውን ያደረሰው ሰዉ መኪናዉን ለማንቀሳቀስ ወይም ለመንዳት ያልተፈቀደለት ሰው እንኳን ቢሆን መኪናዉ ለሚያደርሰዉ ጉዳት የመኪናዉ ባለቤት አላፊ ይሆናል ::
የፍትሀብሄር ህግ ቁጥር 2ዐ81 /1/ እንደሚያመለክተዉ : "አደጋውን ያደረሰው ሰዉ መኪናዉን ለማሽከርከር ያልተፈቀደለት ሰው ሆኖ ይህ ያልተፈቀደለት ግለሰብ እየነዳ ጉዳት ቢያደርስ የመኪናዉ ባለቤት አላፊ ይሆናል" :: ነገር ግን አደጋው በደረሰ ጊዜ መኪናው ተስርቆበት ከሆነና ይህንንም ማስረዳት ከቻለ የመኪናዉ ባለቤት ለደረሰዉ ጉዳት አላፊ አይሆንም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በቁጥር 2ዐ82/1/ መሠረት አንድ ሰው መኪናውን ለግል ጥቅሙ ሲገለገልበት መኪናው ጉዳት ካደረሰ ለደረሰው ጉዳት አላፊ ሊሆን የሚችለው ይህ ሰው ነው፡፡
አንድ የመኪና ባለቤት መኪናውን ለማንቀሳቀስ ሠራተኛ ሊቀጥር ይችላል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ መኪናዉ ጉዳት ያደረሰዉ በሠራተኛው ጥፋት ካለሆነ በስተቀር በቁጥር 2ዐ82/2/ መሠረት መኪናዉ ላደረሰዉ ጉዳት አላፊ የሚሆነው የመኪናዉ ባለቤት ነው፡፡
ሳሙኤል ግርማ
#ሕግ_አገልግሎት_
#Ethiopia #LegalService #Lawyer #Samuel Girma
የሰ/መዝ/188483
===/////====
~~~
★የክልል ፍርድ ቤቶች በህገ መንግስቱ የተሰጣቸው ውክልና እስካልተነሳ ድረስ በግዛት ክልላቸው የተፈጠሩ የፌደራል ጉዳዬችን አይቶ የመወሰን ስልጣን ያላቸው መሆኑን እና
★የፌደራል ፍ/ቤቶችም በክልሎች የሚፈጠሩ የፌደራል ጉዳዬችን የማየት ስልጣን አለን በሚል ከክልል ፍ/ቤቶች ወስደው የማየት ስልጣን የሌላቸው ስለመሆኑ
#Via
#henoktayelawoffice
===/////====
~~~
★የክልል ፍርድ ቤቶች በህገ መንግስቱ የተሰጣቸው ውክልና እስካልተነሳ ድረስ በግዛት ክልላቸው የተፈጠሩ የፌደራል ጉዳዬችን አይቶ የመወሰን ስልጣን ያላቸው መሆኑን እና
★የፌደራል ፍ/ቤቶችም በክልሎች የሚፈጠሩ የፌደራል ጉዳዬችን የማየት ስልጣን አለን በሚል ከክልል ፍ/ቤቶች ወስደው የማየት ስልጣን የሌላቸው ስለመሆኑ
#Via
#henoktayelawoffice
ተቋሙ ለስራ ክፍል ሃላፊዎችና ቡድን መሪዎች በጸደቁ ሁለት መመሪያዎች ላይ ስልጠና ሰጠ፡፡
*****
ስልጠናው የሲቪል ማህበረሰብ ፈንድ ለማስተዳደር የወጣ መመሪያ ቁጥር 848 እና የሙያ ማህበራትን ለመደገፍና ለማስተዳደር የወጣ መመሪያ ቁጥር 849 ላይ ነው፡፡
በስልጠናው የጋራ ግንዛቤ በመያዝ እውቀትን መሰረት ያደረገ ውሳኔ እና አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከጸደቁት 4 መመሪያዎች በተጨማሪ ሌሎች በርካታ መመሪያዎች እየተዘጋጁ መሆኑን በመግለጽ በቀጣይም በየግዜው የሚጸድቁ መመሪያዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡
Agency_for_Civil_Society
https://t.me/GudayAsfetsami
*****
ስልጠናው የሲቪል ማህበረሰብ ፈንድ ለማስተዳደር የወጣ መመሪያ ቁጥር 848 እና የሙያ ማህበራትን ለመደገፍና ለማስተዳደር የወጣ መመሪያ ቁጥር 849 ላይ ነው፡፡
በስልጠናው የጋራ ግንዛቤ በመያዝ እውቀትን መሰረት ያደረገ ውሳኔ እና አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከጸደቁት 4 መመሪያዎች በተጨማሪ ሌሎች በርካታ መመሪያዎች እየተዘጋጁ መሆኑን በመግለጽ በቀጣይም በየግዜው የሚጸድቁ መመሪያዎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡
Agency_for_Civil_Society
https://t.me/GudayAsfetsami
ምክር ቤቱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አነሳ
.
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነሳ፡፡
.
ምክር ቤቱ በስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እንዲነሳ ወስኗል፡፡
.
ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት ከዛሬ ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግ ተወስኗል፡፡
.
በተመሳሳይ የፍትህ አካላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ የጀመሯቸውን ጉዳዮች በመደበኛው የፍትህ አሰሰጣጥ ስርአት እንዲያጠናቅቁም ነው የተወሰነው፡፡
በሃይለየሱስ ስዩም ኤፍ ቢ ሲ
.
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነሳ፡፡
.
ምክር ቤቱ በስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እንዲነሳ ወስኗል፡፡
.
ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት ከዛሬ ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግ ተወስኗል፡፡
.
በተመሳሳይ የፍትህ አካላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ የጀመሯቸውን ጉዳዮች በመደበኛው የፍትህ አሰሰጣጥ ስርአት እንዲያጠናቅቁም ነው የተወሰነው፡፡
በሃይለየሱስ ስዩም ኤፍ ቢ ሲ