አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.56K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት፣ መገልገል እና የወንጀል ተጠያቂነት
1. ሀሰተኛ ሰነድ እና አይነቱ
ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሀገርን ኢኮኖሚ እንዲሁም የዜጎችን መብትና ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ የወንጀል ተግባር ነው፡፡ ሀሰተኛ ሰነዶች ዝግጅት በረቀቀና እውነተኛውን በሚመስል መንገድ የሚፈፀም በመሆኑ ይህን ከባድ ወንጀል ለመከላከልና አጥፊዎችን ለመቅጣት ብሎም ህብረተሰቡ ከዚህ ወንጀል እራሱን እንዲጠብቅ ግንዛቤ መፍጠር ያስፈልጋል፡፡

ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀቱ በመንግስታዊና ህዝባዊ ድርጅቶች ሰነዶች ላይ የሚፈፀም ከሆነ በሙስና ወንጀል የሚያስጠይቅ ነው፡፡ መንግስታዊ ሰነድ ሲባል የሚኒስቴር መስሪያ ቤት ወይም የክልል ቢሮዎችና በየደረጃው ያሉ አስተዳደር መስሪያ ቤቶች የወጡ በማስመሰል የሚዘጋጅ ሲሆን ለምሳሌ የንግድ ወይም ኢንቨስትመንት ፈቃድ ወረቀቶች፣ የይለፍ ወረቀቶች፣ የብቃት ማረጋገጫዎች፣ የስራ ፈቃድ ወረቀቶች፣ የስራ ልምድ፣ የክፍያ ማዘዣዎች፣ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ወይም ሊብሬዎች፣ ወዘተ የሚያካትት ነው፡፡ የህዝባዊ ድርጅቶች ሰነድ ደግሞ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ወይም ተቋማት ሰነዶች ለምሳሌ የመጋዘን ደረሰኝ፣ የእቃ ማውጫ ፈቃድ፣ የትምህርት ማስረጃ፣ የባንክ ክፍያ ሰነዶች እና መሰል በእነዚህ ተቋማት የሚሰጡ ሰነዶችን የሚመለከት ነው፡፡ እነዚህን ሰነዶች ማዘጋጀትና መገልገል የሚያስከትለውን የወንጀል ተጠያቂነት ከዚህ እንደሚከተለው በዝርዝር ይቀርባል፡፡

2. ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት፣ መገልገል እና የሚያስከትለው የወንጀል ተጠያቂነት
ማንኛውም ሰው የሌላውን ሰው መብት ወይም ጥቅም ለመጉዳት ወይም ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ተገቢ ያልሆነ ማናቸውም መብት ወይም ጥቅም ለማስገኘት በማሰብ አንድ ፅሁፍ፣ መዝገብ ወይም ማንኛውም ሰነድ የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት በማስመሰል ያዘጋጀ ወይም የፈጠረ፤ በመንግስት ወይም በህዝባዊ ድርጅት መዝገብ፣ ፅሁፍ ወይም ሰነድ የሰፈረን እውነተኛውን ፅሁፍ በመለወጥ ወይም በመደለዝ፣ በሀሰተኛ ፊርማ፣ በእጅ በተደረገ ምልክት ወይም በጣት ፊርማ፣ በማህተም ወይም የሌለውን ስልጣን ወይም ችሎታ እንዳለው አስመስሎ በመፈረም ሀሰተኛ ሰነድ የፈጠረ እንደሆነ፤ አንድን የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰነድ በተለይ የፈራሚውን ስም ወይም ፊርማ ወይም የሰነዱን ይዘት፣ አሃዝ፣ ፍሬ ነገር ወይም ዝርዝር መግለጫ በሙሉ ወይም በከፊል በመለወጥ፣ በማሻሻል፣ በመቀነስ ወይም በመጨመር ወይም በማጥፋት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም ማናቸውንም ሀሰተኛ ፍሬ ነገር ያስገባ ወይም እንዲገባ ያደረገ እንደሆነ በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 23 መሰረት ከሶስት አመት እስከ አስር አመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ያስቀጣል፡፡
በተጨማሪም የዚህ ወንጀል አፈፃፀም በሚከተለው ሁኔታ ሊከብድ የሚችል ሲሆን ይኽውም ሰነዶቹን እንዲያዘጋጅ፣ እንዲመዘግብ እንዲጠብቅ ወይም ከነዚሁ ውስጥ ቅጂዎችን እንዲሰጥ ሀላፊነት በተሰጠው የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ እንደሆነ ወይም ሰነዱን በመገልገል የተገኘው ጥቅም ከፍተኛነት ወይም በግለሰብ፣ በመንግስት ወይም በህዝባ ድርጅት ወይም በህዝብ ጥቅም ላይ ያደረሰው ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነ ቅጣቱ ከአምስት አመት እስከ ሀያ አምስት አመት የሚደርስ እስራት ያስቀጣል፡፡

ሌላው መገንዘብ የሚገባን ጉዳይ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 23 (4) መሰረት በወንጀል የሚያስጠይቀው ሀሰተኛ ሰነዶችን ማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን ይዞ መገኘትና መገልገል ጭምር ሲሆን በዚህም መሰረት ወደ ሀሰት የተለወጠ ወይም በሀሰት የተዘጋጀ ሰነድ በቤቱ፣ በተሽከርካሪው፣ በኪሱ ወይም በማንኛውም አግባብ በቁጥጥሩ ስር የተገኘ እንደሆነ ከላይ በተጠቀሰው ቅጣት ጋር ተመሳሳይ በሆነ ይቀጣል፡፡ በተጨማሪም ማንኛውም ሰው ወደ ሀሰት በተለወጠ ወይም በሀሰት በተዘጋጀ ሰነድ እያወቀ የተገለገለበት እንደሆነ በተመሳሳይ ይቀጣል፡፡

በሉላ በኩል ከግብር አከፋፈል ጋር በተያያዘ ማንኛውም ሰው ሆን ብሎ ወይም በከባድ ቸልተኝነት ለገቢዎች ሚኒስቴር የተጭበረበሩ ሰነዶችን ያቀረበ በፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀፅ 118 መሰረት ከሶስት እስከ አስራ አምስት አመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል፡፡ በአንቀፅ 119 መሰረት ደግሞ እነዚህን የተጭበረበሩ ደረሰኞችን ያዘጋጀ፣ ያተመ፣ የሸጠ ወይም ያሰራጨ ወይም የተጠቀመ ከሰባት አመት እስከ አስር አመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል፡፡ የዚህን ወንጀል አፈፃፀም ለመከላከል ሲባል የተደነገገ ሌላ ጥፋት ሀሰተኛ ደረሰኞችን ለመስራት፣ ለማዘጋጀት ወይም ለማተም የሚያገለግል ማሽን፣ መሳሪያ ወይም ሶፍትዌር የያዘ፣ የሸጠ፣ ያከራየ ወይም በሌላ መንገድ ያቀረበ ማንኛውም ሰው ከአስር እስከ አስራ አምስት አመት እስራት እንደሚቀጣ በህጉ መደንገጉ ነው፡፡ በተመሳሳይ እነዚህን ሀሰተኛ ደረሰኞችን የያዘ፣ ያስቀመጠ፣ ለሽያጭ ያመቻቸ ወይ ሀሰተኛ ደረሰኞችን ጥቅም ላይ እንዲውሉ ያደረገ ከሶስት እስከ አምስት አመት እስራት ይቀጣል፡፡

ከጉምሩክ መንግስታዊ ስራዎች ጋር በተያያዘ ማንኛውም ሰው በጉምሩክ ኮሚሽን ላይ ጉዳት ለማድረስ ወይም ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ ኮሚሽኑ የሚጠቀምበትን ቅፅ፣ ማህተም፣ መታወቂያ፣ አርማ፣ የጉምሩክ ማሸጊያ ወይም ማናቸውም ሰነድ ወይም ምልክት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም አስመስሎ የሰራ ወይም ይህንኑ ያከፋፈለ፣ የተጠቀመ ወይም ለመጠቀም የሞከረ ወይም ለጉምሩክ ስነ ስርአት የሚቀርቡ ሰነዶችን የሰረዘ፣ የደለዘ፣ የፋቀ ወይም አስመስሎ የሰራ በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 አንቀፅ 167 እና በጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ 1160/2011 አንቀፅ 169(4) መሰረት ከአምስት እስከ አስር አመት እስራት ይቀጣል፡፡

ከላይ ከተመለከቱት መንግስታዊና ህዝባዊ ሰነዶችን ማዘጋጀትና መገልገል ወንጀል በተጨማሪ በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴ የምንጠቀምባቸውን ግላዊ ሰነዶችን በሀሰተኛ መንገድ ማዘጋጀትና መገልገል ከለይ ከተመለከተው ከባደ ሁኔታ ዝቅ ባለ በመለስተኛ ደረጃ በወንጀል የሚያስጠይቅ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ጥቅም ወይም መሻሻልን ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በማሰብ ተገቢ መብት ለማስገኘት የሚችሉ ፅሁፎችን፣ ግላዊ ሁኔታን የሚገልፁ ማስረጃዎችን ወይም ምስክርነትን ማስረጃዎችን ወይም ማናቸውንም አይነት ጉዳይ የሚመለከቱ የምስክርነት ማረጋገጫ ሰነዶችን ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ ወይም አስመስሎ የሰራ ወይም እያወቀ ይህን የመሰለውን ሰነድ እንዲገለገልበት ለሌላ ሰው መስጠት በ1996 ዓ/ም የወንጀል ህግ አንቀፅ 385 መሰረት በቀላል እስራት ወይም መቀጮ ያስቀጣል፡፡ ይህ ሰነድ የግል ጉዳይን የያዘ እንደሆነ ከአንድ አመት ባልበለጠ እስራት፣ ወይም ሰነዱ ህዝባዊ ባህሪ ያለው ሆኖ እንደመታወቂያ ወረቀት ወይም የልደት ምስክር ወረቀት ወይም የችግርተኛነት፣ የመልካም ጠባይ፣ የብቁነት ወይም ብቁ አለመሆን ማረጋገጫ ምስክርነት ወይም የህዝብ መዝገብ ወይም መቆጣጠሪያ ቅጂ እንደሆነ ከሶስት ወር በማያንስ እስራት ያስቀጣል፡፡

በሌለ በኩል ወንጀሉን የፈፀመው እነዚህን ሰነዶች እንዲያዘጋጅ፣ እንዲያስቀምጥ፣ እንዲጠብቅ ወይም እንዲሰጥ ሀላፊነት በተሰጠው የመንግስት ሰራተኛ እንደሆነ እና ይህን ወንጀል ያደረገው በሌላ ሰው መብት ላይ ጉዳት ለማድረስ ሳያስብ እንደሆነ ከስድስት ወር እስከ አምስት አመት በሚደርስ እስራት ወይም በመቀጮ ወይም በሁለቱም ያስቀጣል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ማንኛውም ሀኪም፣ የጥርስ ሀኪም፣ የመድሀኒት ቅመማ ባለሙያ፣ የእንስሳት ሀኪም፣ አዋላጅ ወይም በህክምና ሙያው ህክምናን በሚመለከት የምስክር ወረቀት ለመስጠት መብት ያለው ማንኛውም ሌላ ሰው የምስክር ወረቀት ስራ ላይ እንደሚውል እያወቀ ለተቀባዩ ሰው የማይገባ ጥቅም ለማስገኘት የሚችል ወይም የሌላውን ሰው ህጋዊ ጥቅም የሚጎዳ ሀሰተኛ የህክምና ምስክር ወረቀት አዘጋጅቶ ፅፎ የሰጠ በወንጀል ህግ አንቀፅ 387 መሰረት በቀላል እስራት ወይም በመቀጮ ይቀጣል፡፡ ይህ ወንጀል በመንግስት ሰራተኛ ከተፈፀመ ወይም ወንጀሉ በስጦታ ወይም በሌላ ጥቅም የተፈፀመ ከሆነ ቅጣቱ ከአስር እስከ አስራ አምስት አመት እስራት ይደርሳል፡፡ በመጨረሻም ማንም ሰው ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ሊገለገልባቸው በማሰብ ኦፊሴላዊ ፅሁፎችን፣ የምስክር ወረቀቶችን፣ ዲፕሎማዎችን ወይም ሰነዶችን ወደ ሀሰተኛነት ለመለወጥ ወይም በሀሰት ለመፍጠር የሚያገለግሉ መሳሪያዎችንና መስሪያዎችን ወይም ቁሳዊ ነገሮችን የሰራ፣ በእጁ ያስገባ፣ የያዘ፣ የሰጠ ወይም ለሽያጭ ወይም ለስጦታ ያቀረበ እንደሆነ በአንቀፅ 390 መሰረት ከአምስት አመት በማይበልጥ እስራት እና በመቀጮ ይቀጣል፡፡

በአጠቃላይ ከላይ ከተመለከቱት የሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል ወንጀሎች ሰፊ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገባና ህብረተሰቡ ከእነዚህ ወንጀሎች እራሱን ማራቅና መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡ እነዚህ ወንጀሎች በሀገርና በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርሱ ሲሆን የዜጎችን መብትና ጥቅም በማጭበርበር የሚያሳጡ ናቸው፡፡ በህግም የሚያስከትሉት ተጠያቂነት ሰፊና ከባድ ነው፡፡ ስለሆነም ሀሰተኛ ሰነዶች ከማዘጋጀት፣ እንዲዘጋጅ ከማድረግ፣ ይዘን ከመገኘት፣ ከመገልገል፣ ሀሰተኛ ሰነድ መስሪያ መሳሪያዎችን ይዞ ከመገኘት መቆጠብ ያስፈልጋል፡፡ በተጨማሪም እንዲህ ያለ ጥፋት መፈፀሙን ስናስተውል ለህግ አስከባሪ አካላት ማሳወቅ እና ተጠያቂነት እንዲኖር ለማድረግ መተባበር ያስፈልጋል፡፡
🟢 @lawsocieties
🟡 @lawsocieties
🔴 @lawsocieties
https://t.me/lawsocieties
በነጋሪ መተግበሪያ አዲሱን የፌዴራል ጠበቆች አዋጅን (አዋጅ ቁጥር 1249/2013) አካትተናል፤ ይህ አዋጅ የቀድሞ የፌዴራል የጥብቅና አዋጅ አዋጅ ቁጥር 199/1992 ሽሮ በአዲስ የተካ ሲሆን ይህ አዋጅ በቀድሞ አዋጅ ያልነበሩ አዳዲስ ሐሳቦችን ያካተተ ሲሆን ከዚህ አዋጅ ጋር ራስዎን ያስተዋውቁ፤

አዋጅ ቁጥር 1249/2013 - የፌደራል ጥብቅና አገልግሎት ፍቃድ አሰጣጥ እና አስተዳደር አዋጅ
http://negari.abyssinialaw.com/laws?id=1973
https://t.me/casemanagers
ጉዳይዎን እናስፈፅምልዎ ከግል ተቋማት ሆነ ከግለሰብ፣ ከመንግስት መስሪያቤት ጋር በተያያዘ ያሰቡትን እንፈፅምልዎ።
@Casemanager_bot
Screenshot_20211119-145340.jpg
269.3 KB
አዲሱን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1234/2013) በነጋሪ አንድሮይድ መተግበሪያ አካትተናል፤

ይህ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 25/1988 እና ማሻሻያ አዋጆቹን አዋጅ ቁ. 138/1991፣ አዋጅ ቁ. 254/1993፣ አዋጅ ቁ. 321/1995 እና አዋጅ ቁ. 454/1997 በሙሉ ሽሮ በአዲስ መልክ የወጣ ነው።

አዋጅ ቁጥር 1234/2013 - የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ
http://negari.abyssinialaw.com/laws?id=1983
@lawsocieties...........
ALE (Alternative Legal Education) All in one, for all.🔴አለ (አማራጭ የሕግ ትምህርት)ሁሉም በአንድ፣ ለሁሉም።🔴 @lawsocieties
Contact us: @LawsocietiesBot
lawsocieties@gmail.com
@lawsocieties
መሰረታዊ የህግ መረጃ እውቀት፤ ሀብት እና ሀይል ነው። ግዴታዎችንና መብቶችን ይወቁ።
ዳኞች ስራ ላይ ባሉ ህጎችና ፋይዳቸው ላይ የጽሁፍ ውጤቶችን ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ
**********************
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ዳኞች በስራ ላይ ባሉ ህጎችና ፋይዳቸው ላይ ጥናትና ምርምር በማካሄድ የጽሑፍ ውጤቶችን ማበርከት እንደሚጠበቅባቸው ገለጹ፡፡

አቶ ሰለሞን አረዳ ይህን የገለጹት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት በሆኑት በክቡር አቶ ተስፋዬ ነዋይ “የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ ሕጋዊና ኢኮኖሚያዊ ገጽታ” በሚል ርዕስ የታተመ መጽሐፍ የምረቃና የትችት መርሃ ግብር ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ነው፡፡

ጸሐፊው ዕረፍት በማይሰጥ የመንግስት ኃላፊነት ላይ የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ ባለፉት ሶስት ዓመታት ሶስት መጽሐፍትን ጽፈው ለህትመት ማብቃታቸው ለፌዴራል ዳኞች ትልቅ አርዓያነት ያለው ተግባር መሆኑን የተናገሩት ክቡር አቶ ሰለሞን አረዳ ዳኞች የመዝገብ ጫና ያለባቸው ቢሆንም ጊዜያቸውን ቆጥበው በሙያቸው ጥናትና ምርምር በማካሄድ ውጤቶቻቸውን በመጽሐፍ መልክ በማቅረብ ለማህበረሰቡ እውቀታቸውን ማካፈል ይችላሉ ብለዋል፡፡

በመጽሐፍ ምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የተሳተፉ ዳኞች በሰጡት አስተያየት ክቡር አቶ ተስፋዬ የፍርድ ቤት አመራር ሆነው በኢኮኖሚውና በህጉ ዘርፍ ትስስር በሚፈጥር ጉዳይ ላይ አስተማሪ የሚሆን መጽሐፍ ጽፈው ማሳተማቸው ቀላል እንዳልሆነ ገልጸው ዳኞች ለሚቀርቡላቸው በርካታ ጉዳዮች ዳኝነት ከመስጠት ባሻጋር ሌሎች የጎንዮሽ ስራዎችን መስራት እንደምንችል ተምሳሌት አድርገን የምንወስደው ነው ብለዋል፡፡ አቶ ተስፋዮ የፍርድ ቤት አመራር በመሆናቸው ኩራት እንደሚሰማቸው እና ለእርሳቸው ክብርም እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

የመጽሐፉ ምረቃ ፕሮግራም ከህግ ባለሙያዎች ማህበር በተገኘ ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን በመድረኩ የንግድና ኢንደስትሪ ሚኒስትር ሚኒስቴር ድኤታ አቶ ሐሰን መሃመድ ፣ የህግ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝደንት አቶ ፊሊፖስ ዓይናለም፣ እና የደራሲያን ማህበር ም/ሊቀመንበር ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ መጽሐፉ በሸማቾች፣ በንግድ ስርዓቱ ፣ በህግና በኢኮኖሚው ዘርፍ በሚያበረክተው አስተዋጽኦ ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ፌ/ጠ/ፍ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
አስቸኳይ የስልጠና ጥሪ ለፌዴራል #ጠበቆች
Ethio-Engineering Group Job 2021 at ethioengineering.com Vacancies

Ethio-Engineering Group Job 2021: Ethio-Engineering Group invites qualified and experienced applicants for the various positions. Ethio-Engineering Group is invites job seekers for appointment. It’s a great opportunity to work under them.

The interested applicants can apply online through the official career page of ኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ (Ethio-Engineering Group) before the closing date of application. For more information please read the full article.
The main aim to establish Ethio-Engineering Group has been to make a fundamental difference through a lead role in the industrialization of Ethiopia. 

Ethio-Engineering Group has been to make a fundamental difference through a lead role in the industrialization of Ethiopia.

Quick Details of Ethio-Engineering Group

Hiring Organization: Ethio-Engineering Group

Shortly Known as: EEG

Established Date: 1984

Organization Type: Government Agency

Organization Size: 500-1500 employees

Location: Addis Ababa, Ethiopia

Official Website: ethioengineering.com

EEG Ethiopia Job Notifications 2021

The Ethio-Engineering Group (ኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ) wants to recruit employees in the following vacant positions the details of which are mentioned below.

Vacancy Details

Position Title: Lawyer

Required Number: One (01)

Location: Addis Ababa (Head Office)

Type of Employment: Permanent

Salary: 4950, 6170, 7550 Birr

Qualifications: LLB Degree in relevant fields

Experience: At least 0/2/4/8 years of experience

Job Posted: 14 November 2021

Job Deadline: 26 November 2021


Ethio-Engineering Group Application Process

Interested and qualified applicants are invited to submit their application within 10 working days from his announcement at Addis Zemen, Ethiopian Herald newspaper and vacancy web pages to Head Office (Former Imperial hotel Building) Human Resource Management Support Process office No. 116. With the following documents.

Copies of experience letters and testimonials documents. You are welcome to submit a copy of the original and non returnable photocopy in person.

Evidence of work experience from non-governmental organizations and private organizations must be certified as taxable.

The work experience provided for the position must be relevant and directly related.
Terms of Reference /ToR/ to Legal Service Officer

ABOUT THE ECSF

The Ethiopian Civil Society Organizations Forum (ECSF has been established as a non-partisan, independent, inclusive and voluntary national platform with a focus on the common concerns and challenges of the Civil Society sector in Ethiopia. The Forum’s operational scope is at federal and regional levels with a focus on legal, institutional and operational issues and processes that commonly concerned the civil society sector in Ethiopia. 

The various Networks and Consortia of Civil Society organizations (named as ‘Civil Society Organizations’ in the recently ratified Proclamation No. 1113/2019) operating at Federal and Regional level thus came together and established the) ECSF in May 2013.

Vision

ECSF envisions seeing a strong and vibrant civil society sector for sustainable development.

Mission

ECSF aspires to ensure the existence of enabling environment for civil society organizations sector through strong representation, constructive dialogue and partnership using consortiums and other legal establishments as platform for action. 

ABOUT THE PROJECT

Title of the project:  Request for Applications (RFA) 1/2020 to improve citizen engagement in the legal and judicial reforms in Ethiopia

Implementing partner: Ethiopian Civil Society Organization’s Forum /ECSF/

Funding Partner: Feteh (Justice) Activity

Objectives of the project: Overall Objective: The project is aimed to enhance the ability of civil society organizations (CSOs) engagement in the legal and judicial reforms process.

Reports to:Program Manger

JOB SUMMARY

Under the supervision of the Program Manager, the Legal Services Officer (LSO) will coordinate the work of the ECSF legal works and facilitate project specific activities. He/she will play a leading role in both long-term strategic planning processes as well as in short-term project planning. The LSO will provide key legal expertise, including by analyzing and promoting media laws which are in conformity with the both international and national litigation, research and writing, training, policy development and standard-setting, campaigning and monitoring new developments. The LSO will be directly responsible for the implementation of one or more projects.

Major Duties and Responsibilities

Organizational Aspects:

Advise the executives and employees on changes to the laws affecting ECSF.

Review and advise management on legal implications of internal policies and procedures. Review and provide legal advice on Memorandum of Understanding [MOUs], Contract management, and tender documents preparations.

Review internal policies and ensure that they are in compliance with all statutory or legal requirements in Ethiopia.

Be actively engaged in the (i) strengthening networks of CSOs representing women, youth and/or PWD, (ii) Monitoring draft legislation for compliance with the rights of women, youth & PWD, (iii) Developing comprehensive report on overview of the proclamations/regulations enacted during the project’s term, (iv) developing MoU for the key activities executed with other stakeholders,

Take active role in the facilitation of discussion forums/events/forum/workshop in cooperation and consultation with relevant organs, such as  Federal Attorney General Office, ACSO, HoPR, DI, relevant CSOs etc

Review ongoing cases and advice management accordingly. Oversee lawsuits, possibly acting as chief litigator.

Communicate with relevant departments to ensure that where legal risks have been identified, appropriate courses of action have been taken.

Provide legal protection and risk management advice to management especially on contract management.

Provide and interpret legal information, conduct training and disseminate appropriate legal requirements to staff.

Review progress of outstanding litigation issues.

Formulate legal compliance check-lists for all the countries to be used for the purpose of ensuring that all information required is provided accordingly.
Continuously monitor compliance with statutory obligations in the countries and advise the ECSF management accordingly.

Prepare monthly and quarterly reports for the department for executive management meetings.

Other tasks may be assigned as necessary according to organizational needs.

Project Aspects:

 Support implementation of project activities as directed by the program Manager, based on approved work plan(s), budgeting, and other relevant framework;

Provide input into the annual work plan drafting process;

Contribute to regular programmatic reports to donors including monthly and quarterly performance reports;

Contribute regularly to monitoring & evaluation data collection;

Maintain crucial project documents which track project progress, file all project documents in an appropriate database, ensure that all documents are accurate and have been accepted by supervisor;

Identify any potential issues or risks that could affect the progression of the project, communicate these items with supervisor, and work to identify potential solutions;

Closely monitor the project schedule, monitoring deadlines for each project task, raise potential delays with the Project Manager;

Maintain and develop productive working relationships with partner organizations;

Other duties as assigned.

Job Requirements:

Profile, Required Qualifications and Skills

First degree in Law (LLB), Master’s degree is a plus.

3 -5 years of experience in providing legal services to civil society organizations in Ethiopia. Experience with international NGOs is a plus.

Demonstrate knowledge of and experience with laws dealing with civil societies in Ethiopia.

Experience working on USAID-funded programs, preferred

In-depth knowledge of regulatory laws (both national and International).

Excellent communication, negotiation and diplomatic skills.

Excellent command of English.

Proficiency in Word, Power point, Outlook and Excel

Real interest to work in civil society environment.

Demonstrated ability to draft memos, analysis and manuals in Amharic and English;

Experience working on research, analysis or content work in the law or related field.

Demonstrated professional experience and knowledge in election administration preferred;

How To Apply:

Interested applicants can submit their CV and Application letter within 7 working days to the Ethiopian Civil Society Organizations Forum /ECSF/ Office in Addis Ababa: Bole Sub-City, Around 22 Mazoriya, 100 mt from Awraris Hotel to the West, Next to Oasis Apartment Hotel; P. O. Box: 1270 code 100; E-mail: info@fcsf.net,bethlehemgetachew9@gmail.com,  Website: https://www.fcsf.net.

For any further information about this announcement, call @ 0912852814 or 0912375041