አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.86K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Transparency International Ethiopia is Looking Volunteers for Social media administration and moderators.‼️‼️‼️‼️

Share to your best friends and families‼️

volunteering program opportunities ......

Civics students
Political students
Psychology
Sociology
Law
Journalism.......E.T.C.....

ባሉበት ሁነው የሚያከናውኗቸው ቀላል የበጎ አድራጎት ስራዎች ውጭውን ሸፍነን ባሉበት በሚሰሩበት በሚማሩበት በሚኖሩበት ቦታ የሙስናን አስከፊነት ይናገሩ‼️
የመልካም ዜጋን ስብዕና ያካፍሉ‼️
ይህ መልካም አጋጣሚ ነው።

በቀኑ መጨረሻ የምስክር ወረቀት እናዘጋጃለን።
እንደ አሳዩት የስራ እንቅስቃሴ የስራ እድል እናመቻቻለን።
https://t.me/TransparencyEthiopia
November 17, 2020
November 17, 2020
November 17, 2020
November 17, 2020
Forwarded from Deleted Account
November 17, 2020
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
November 17, 2020
November 18, 2020
Forwarded from አለሕግ🔵AleHig
November 18, 2020
የውንብድና ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በጽኑ እስራት ተቀጣ
______________

በቦሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት የውንብድና ወንጀል የፈጸመው ተከሳሽ ዐቃቤ ሕግ በመሰረተው ክስ በ7 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ በእስራት ተቀጣ፡፡

የክስ መዝገቡ እንደሚያስረዳው ተከሳሽ የማይገባውን ብልጽግና ለማግኘት በማሰብ በቦሌ ክፍል ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል አካባቢ የሰሌዳ ቁጥር 03-2421 ኦሮ የሆነ በተለመዶ አባዱላ ተብሎ የሚጠራውን መኪና እያሽከረከረ ግብረ አበሮቹን ይዞ ወደ ግል ተበዳይ ሽኩር የሱፍ ሱቅ በመሄድ አንደኛው ያልተያዘው ግብረ አበሩ ባለሱቁን የ50 ብር ካርድ አልህ ወይ ብሎ በመጠቅ ካርዱን ሊሰጠው ወደ ውስጥ ሲገባ ያልተያዙት ሁለቱ ግብረ አበሮቹ ከመኪናው በመውረድ ተከትለው በመግባት አንደኛው ግብረ አበሩ በጩቤ አንገቱን ይዞ በማስፈራራት ሁለተኛው ግበረ አበሩ በስቁ ውስጥ የነበረውን 30‚000 ብር እና አጠቀላይ ከ51ሺ ብር በላይ የሚያወጡ ንብረቶችን ከወሰዱ በኋላ ተከሳሽ ይዞ በመሰወሩ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀመው የከባድ ውንብድና ወንጀል ተከሷል ዐቃቤ ህግም እንደ ክሱ አቀራረብ የሰውን እና የሰነድ ማስረጃዎችን አጠናቅሮ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 20ኛ ወንጀል ችሎት መዝገቡን መርምሮ ተከሳሽ የቤተስብ አስተዳዳሪ እና ሪከርድ የሌለበት መሆን ማቅለያ በመያዝ ጥቅምት 24 ቀን 3013 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ በ7 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎል፡፡
share ‼️🔴

https://t.me/lawsocieties
November 18, 2020
November 18, 2020
የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በጽኑ እስራት ተቀጣ
______________

በልደታ ክፍለ ከተማ የ12 ዓመቷን ታዳጊ አስገድዶ የደፈረው ተከሳሽ ዐቃቤ ሕግ በመሰረተው ክስ በ12 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ፡፡

ተከሳሽ አቶ ግርማዬ ገ/ስላሴ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 627(1)ን በመተላለፍ የ12 ዓመት ታዳጊና የልጁ ጓደኛ በሆነችው የግል ተበዳይ ላይ ሚያዚያ 08 ቀን 2008 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ሲሆን በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ልዩ ቦታው ልማት ምንጭ ተብሎ ከሚጠራው አከባቢ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ውስጥ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙን ዐቃቤ ሕግ ያቀረበው የክስ መዝገብ ያስረዳል፡፡

የዐቃቤ ሕግ ክስ በችሎቱ የተነበበለት ተከሳሽ በበኩሉ የቀረበበትን ክስ የማይቃወም መሆኑን ጥቅሶ የወንጀል ድርጊቱን ግን አልፈፀምኩም ጥፋተኛም አይደለሁም ሲል ክዶ የተከራከረ ሲሆን የመከላከያ ምስክሮቹንም ቃል አስደምጧል፡፡

ዐቃቤ ሕግም ተከሳሹ ወንጀሉን ሰለመፈጸሙ ያሰረዱልኛል ያልኳቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ ያቀረብኩ በመሆኔና የተከሳሽ ምስክሮችም የቀረበውን የወንጀል ድርጊት ማስረጃ የላስተባበሉ በመሆኑ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኝነት ወሳኔ ይሰጥልኝ በማለት ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል፡፡

ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ካደመጠ በኃላ ተከሳሽን በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ብሎታል፡፡

ክሱን የተመለከተው የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 7ኛ ወንጀል ችሎትም መዝገቡን መርምሮ ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ የወንጀል ሪከርድ የሌለበት፣የቤተሰብ አስተዳዳሪና ማህበራዊ ተሳትፎ ያለው መሆኑን እንዲሁም የአስም ህመምተኛ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ተከሳሽ በ12 ዓመት ጽኑ እስራ እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡
https://t.me/lawsocieties
November 18, 2020
November 18, 2020
November 19, 2020
ስድብ ተሰድቤያለሁ በሚል ምክንያት ከባድ የአካል ጉዳት ያደረሰው ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ።
------------------------------------------------

ተከሳሽ ሀይሉ ዳዲ ሳይና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 555 (ሐ) ላይ የተደነገገውን በመተላለፍ ተከሳሹ በሰው አካል ወይም ጤንነት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ጥቅምት 20/2013 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 11፡15 ሰዓት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው “ዕውቀትአምባ ትምህርት ቤት” ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ የግል ተበዳይ ወ/ሮ መስታውት ሀይሉን ብሄርን መሰረት ያደረገ ስድብ ሰድባኛለች በሚል ድንጋይ በመወርወር እና አፏን በመምታት የላይኛው የፊት ለፊት ጥርሷ እንዲሰበር እና የታችኛው ከንፈሯ እንዲሰነጠቅ በማድረግ በፈፀመው ከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል በዐቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል ።

ለፌደራሉ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ ወንጀል ችሎት ህዳር 08/2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት ዐቃቤ ህግ የተከሳሽን ጥፋተኝነት ለፍርድ ቤቱ ያስረዱልኛል ያላቸውን ዝርዝር የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን ተከሳሽ መከላከል ባለመቻሉ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ከዚህ በፊት የጥፋት ሪከርድ የሌለበት መሆኑ ፣ዝቅተኛ የትምህርት እና የኑሮ ደረጃ ከግምት ውስጥ በማስግባት እና ሶሰት የቅጣት ማቅለያዎች በመያዝ ተከሳሽን ያርማል መሰል አጥፊዎችን ያስተምራል በሚል በ2 ዓመት ከ3 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ።
https://t.me/lawsocieties
November 19, 2020
November 19, 2020
የኢትዮ-ቴሌኮምን ንብረት የሰረቁት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ፡፡
--------------------------------

ሸሽጉ ካሰዉ እና ሲሳይ ጌትነት የተባሉት 1ኛ እና 2ኛ የዐቃቤ ህግ ተከሳሾች የተከሰሱበትን ወንጀል የፈጸሙት የካቲት 15 ቀን 2012 ዓ.ም ሲሆን ቦታዉም በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 011 ልዩ ቦታዉ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አካባቢ ነዉ፡፡

ሁለቱም ተከሳሽ ግለሰቦች የማይገባቸዉን ብልጽግና ለራሳቸዉ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰዉ ለማስገኘት አስበዉ ንብረትነቱ የኢትዮ-ቴሌኮም የሆነና የህዝብ ስልክ ቋሚ መጠለያ /ቡዝ/ ሆኖ ሲያገለግል የነበረዉን ግምቱ 20000/ሀያ ሺህ ብር/ የሚገመት ብረት ካልተያዙት ግብረአበሮቻቸዉ በመቀናጀት እያንከባለሉ ሲወስዱ በአካባቢዉ ህብረተሰብ ተደርሶባቸዉ በቁጥጥር ስር ዉለዋል፡፡ ወንጀሉን በዋና አድራጊነት በመፈጸማቸዉም በከባድ የስርቆት ወንጀል ተከሰዋል፡፡

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 32/1/ሀ እና 669/1/ለ ስር የተደነገገዉን በመተላለፋቸዉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዉ መጋቢት 2 ቀን 2012 ዓ.ም ችሎት ቀርበዉ የእምነት ክህደት ቃላቸዉን ሲጠየቁ ሁለቱም ተከሳሾች ወንጀሉን እንዳልፈጸሙና ጥፋተኛም እንዳልሆኑ ክደዉ ተከራክረዋል፡፡

ሆኖም የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ የካ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረቡለትን የሰዉና የሰነድ ማስረጃዎችን መርምሮ የወንጀሉን መፈጸም ካረጋገጠ በኋላ የጥፋተኝነት ብይን ያስተላለፈባቸዉ ሲሆን ጥቅምት 10 ቀን 2013 ዓ.ም ባስቻለዉ 1ኛ ወንጀል ችሎት በ5 (አምስት) ዓመት ከ6 (ስድስት) ወራት እስራት እንዲቀጡ ወስኖባቸዋል፡፡
https://t.me/lawsocieties
November 19, 2020
Forwarded from Deleted Account
November 19, 2020
Forwarded from Biniam Ayalew
November 19, 2020
November 20, 2020
አለም አቀፍ የፍልሰት ስምምነት ሀገራዊ አፈጻጸም በተመለከተ ከባለድርሻ አካለት ጋር ውይይት ተካሄደ
___________

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ብሔራዊ የትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ብሔራዊ እና አለም አቀፍ መደበኛ የፍልሰት ቃል- ኪዳን ስምምነት አፈጻጸም ረቂቅ ሪፖርትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካለት ጋር ግብዓት የማሰባሰብ ውይይት ተካሄደ፡፡

በመድረኩ የብሔራዊ የትብብር ጥምረት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈትህያ ሰዒድ እንደተናገሩት አገራችን ደህንነቱና ሥርዓቱ የተጠበቀ አለም አቀፍ መደበኛ የፍልሰት ቃል- ኪዳን ስምምነት አፈጻጸም ሰነዱን ከፈረሙ አገራት መካከል እንዷ መሆኗን እና ስምምነቱን ወደ ተግባር ለማስገባት መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ፣ አለም አቀፍና አገር ውስጥ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የተሳተፉት ዘርፍ ብዙ ተግባራት ተከናውናል ብለዋል፡፡

ኃላፊዋ አያይዘውም አገራት በእንቅስቃሴ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን መብት ለመጠበቅ፣ ክብር፣ ደህንነትና ጥቅም የሚያስከብር አገልግሎቶችን የተሻለ ለማድረግ አለም አቀፍ የቃልኪዳን ስምምነት (GCM) በ2018 በሞሮኮ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ተቋማት በተቋማቸው የተከናወኑ እና ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ተግባራት ሪፖርት የሚያቀርቡበት የአሰራርና አደረጃጀት ሥርዓት የተዘረጋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ወ/ሮ ፈትህያ ሰዒድ አክለውም አገራቸን ስምምነት ሰነዱን ከፈረመች ጀምሮ የሕግ ማዕቀፎችን በመፈተሸና በማሻሻል የዜጎችን መብትና ደህንነት የሚያረጋግጡ እንቅስቃሴ ሂደት ውስጥ የገቡ ዜጎቻችን ሆነ ሌሎችን መብቶቻቸውን የሚያረጋግጡ ሆነው እንዲገኙ የተለያዩ አዋጆችን በማውጣት፣ አደረጃጀቶችንና አሰራሮች በመዘርጋት፤ የተግባር ክንውን ሪፖርት ጉዳዩ የሚመለከታቸው መረጃ የሚሰጡ ባለድርሻ አካላትን በማሰባሰብ የተዘጋጀ ሲሆን በጉዳዩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ ለመፍጠር እና ተጨማሪ ግብዓት ለማሰባስብ የውይይት መድረኩ አላማ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በውይይት መድረኩ ሰላም ሚኒስቴር፣ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ኤጀንሲ፣ የፌ/የከተሞች ስራ እድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ፣ ሴቶችን፣ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር፣ ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ፣ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ዜጎች ከተለያዩ አገራት ሲመለሱ የምክር፣ የመጠለያ አገልግሎት የሚሰጡ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅቶችና የሀይማኖት ተቋማት ተወካዮች በቀረበው ሪፖርት ላይ ውይይት በማድረግ ተጨማሪ ግብዓት ሰጥተዋል፡፡

በመጨረሻም ለሁለት ቀን በሚደረገው የውይይት መድረክ በሀገር ደረጃ በመሪዎች የሚፈረሙ ስምምነቶች ከመፈረም ውጭ ምን ውጤት አመጡ የሚለውን በማየትና የአገራችን ዜጎች መብት፣ ደህንነታቸውን እና እንቅስቃሴያቸውን በተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰሩ ያሉ ውጤታማ ስራዎችን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በማስተዋወቅ ከሌሎች የአለም አገራት ጋር በመቀናጀት፣ ትብብር እና ድጋፍ ለማግኘት የሚያስችል የተሟላ የሰነድ በማዘጋጀት ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል እንደሚላክ ወ/ሮ ፈትህያ አያይዘው ገልጸዋል፡፡
https://t.me/lawsocieties
November 20, 2020