አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
Le amhara kll judgeship wastna miyasfelgu negerochn bitipositiln
about the negative impacts of improper time management and corruption among the community.
https://telegram.me/lawsocieties
ልጠጣ ብለን መንግሥትን እንደማናስፈቅደው ሁሉ ስብሰባው ወይም መሰብሰቡ በአሻህ ወይም በፈለክ ጊዜ የምታደረገው ነው፡፡ ለዚህ ዓይነት ስብሰባ ዓይነተኛ ምሳሌ የሚሆኑት ሰርግ፣ ልደት፣ ኮንሰርት፣ ማንኛውም ዓይነት ምርቃት፣ የእድር ስብስባ፣ ተሰብስቦ መወያየት፣ መመካከር፣ ሀሳብ መለወጥ፣ በየካፍቴሪያው ሻይ ቡና መባባል እንዲሁም እንደ ስብሰባ የማይቆጠሩ ተራ ስብሰቦዎች ሲሆኑ ከጀምሩም የተለየ ጭንቀትና ጥንቃቄ የማያስፈልጋቸው የዕለት ተዕለት ጉዳዮች ናቸው፡፡
ይሁን እንጅ ይህ ዓይነቱ ስብሰባ የሌሎችን መብት የሚነካ ለሰላም እና ለደህንነት አስጊ መሆን የለበትም እስከተባለ ድረስ ስብሰባው ቅድመ ፈቃድ የማያስፈልገው ቢሆንም ከሰው ቁጥር ብዛት፣ ከስብሰባው ቦታ እና ከስብሰባው ወይም ከስብስቡ ባህሪ አኳያ በአንድ በኩል የተሰብሳቢዎቹን ሰላም እና ደህንነት በሌላ በኩሉ ከስብሰባው ውጭ ያሉ ማህበረሰቦች መብት እና በስብሰባዎቹ ላይ ከፍ ሲል የተጣሉ ገደቦችን ውጤታማ በማድረግ ሰላማዊ ስብሰባ ለማድረግ አስቀድሞ ለመንግሥት አካል ማሳወቅ፣ በመንግሥት በኩል ቅድመ ዝግጅት አድርጎ የሰው ሀይል እንዲመድብ፤ አዘጋጁም ከቁጥጥሩ የወጣ የፀጥታ ችግር እንዳይገጥመው በተለይም መንግሥት አስቀድሞ ካልተነገረው ሁሉንም ስብሰባ በራሱ ያውቃል ለማለት ስለሚያስቸግር አስቀድሞ ማሳወቅ ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው፡፡ አስቀድሞ ማሳወቅ አስቀድሞ ከማስፈቀድ እጅግ የተለየ በመሆኑ በዚህ ስብሰባ ላይ በሕግ የተጣለ አስቀድሞ የማስፈቀድ ግዴታ የለም፡፡
ሕዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ
ይህ ስብሰባ ስብሰባ እንደመሆኑ ከፍ ሲል በተገለፁት መደበኛ የስብሰባ ዓይነት የተቀመጡ መመዘኛዎች ይመለከተዋል፡፡ ይህ ስብሰባ ከፍ ሲል ከተገለፀው የስብሰባ ዓይነት የሚለየው በአዋጅ ቁጥር 3/83 አንቀፅ 4 መሠረት ስብሰባው ከመዳረጉ ከ48 ሰዓታት በፊት በጽሑፍ ለከተማው አስተዳደር ወይም ከከተማ ውጭ ከሆነ ለወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት የማሳወቅ ግዴታ የስብሰባው አዘጋጅ ድርጅት፣ ቡድን ወይም ግለሰብ ያለበት በመሆኑ ነው፡፡
ስብሰበባው ከሚያነሳው ጉዳይ ባህርይ በአብዛኛው መንግሥትን ከመቃወም ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ይነሱበታል ተብሎ የሚታሰብ የስብሰባ ዓይነት በመሆኑ አስቀድሞ ማስታወቅ አንድም ወዳልተፈለገ ብጥብጥ እና ግርግር እንዳያመራ በመንግሥትም ሆነ በሌሎች አካላት በተሰብሳቢዎች ላይ ጥቃት እንዳይደርስ እንዲሁም ስብሰባው የሌሎች ሕዝቦችን ሰላም ደህንነት ስጋት ላይ እንዳይጥል የሚመለከተው አካል ተገቢው ቅድመ ዝግጅትና ጥበቃ እንዲያደርግ ለማስቻል ነው፡፡
ጊዜና ቦታን መቀየር እንጂ መከልከል የማይቻል ስለመሆኑ
ምንም እንኳ ይህ ዓይነቱ ስብሰባ ወይም ሰልፍ ቅድመ ማሳወቅ እንደ ቅድመ ሁኔታ የተቀመጠበት ቢሆንም የሚመለከተው አስተዳደር አካል ለሕዝብ ጥቅም፣ ለሰላም፣ ሁከትና ግርግር ለማስቀረት በቂ ምክንያት ሲኖር ብቻ የስብሰባውን ጊዜና ቦታ ሊቀየር ከሚችል በቀር በስብሰባው በአጠቃላይ እንዲቀር ለማድረግ በፍፁም አይችልም፡፡
ስብሰባው ለጊዜው እዚህ ቦታ አይደረግም ወይም በዚህ ሰዓት አይደረግም የሚል ከሆነም የመሰብሰብ ጥያቄው በቀረበለት በ12 ሰዓት ውስጥ በጽሑፍ የስብሰባውን ጊዜ ወይም ቦታ የቀየረበትን በቂ ምክንያት በመግለጽ ለአዘጋጆቹ የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
የተከለከሉ ቦታዎች
ስብሰባው ቅድመ እውቅናን እንጂ መከልከልን አያስከትልም የቦታና የጊዜ ለውጥ እንጂ ጭራሹኑ ሊቀር አይችልም የተባለ ቢሆንም ከስብሰባው ባህሪ አንፃር ስብሰባው ከሚደረግባቸው ቦታዎች አኳያ ገደቦች በአዋጁ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ ይሄውም በሕዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ በኤንባሲዎች በአለምአቀፍ ድርጅቶች የሥራ ቦታና መኖሪያ ስፍራ፣ በቤተክርስቲያን፣ በመስጊድ በጸሎት ቤቶች፣ በሆስፒታልና በመካነ መቃብር ዙሪያ ሊደረግ አይችልም፡፡
እንዲሁም በኤሌክትሪክ ማመንጫዎች፣ ግድቦች እንዲሁም አደጋ ሊያስከትሉ በሚችሉ ማንኛውም ቦታዎች ሊደረግ አይችልም፡፡ በሌላ በኩል ስብሰባው የሚደረገው በጦር ሀይሎች በጥበቃና የሕዝብን ሰላምና ደህንነት በሚቆጣጠሩ የመንግሥት የሥራ ክፍሎች አካባቢ ከሆን ከነዚህ ቦታዎች 500 ሜትር ርቀት ውጭ መደረግ ይገባዋል፡፡
የአዘጋጆቹና የመንግሥት ተጠያቂነት
ስብሰባው የሚያደርገው እንዲሁ መብት ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የተሻለ ለውጥና ልዩነት ለመፍጠር እንደመሆኑ ስብሰባው ከፍ ሲል የተገለፁትን ገደቦች በማለፍ የጣሰው ሕግ በሕዝብ ላይ ያደረሰው ጉዳት ካለ አዘጋጆቹ የተቀመጠው ገደብ በማለፍ ለፈፅሟቸው ስህተቶች ተጠያቂ ሲሆኑ የፀጥታ አስከባሪዎችና መንግሥት ደግሞ በጥበቃና ጥንቃቄ ጉድለት በሕዝብ ወይም በግለሰቦች ላይ ጉዳት ቢደርስ በሕግ ተጠያቂዎች ይሆናሉ፡፡
በዛሬው ሰልፍ ክልከላ ላይ ፖሊስ የጣሳቸው ተግባራት
የሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 25 /እኩልነት/
ፖሊስ ስልፍ ወይም ስብሰባ ፈቃጅ እና ከልካይ አለመሆኑ አንደ ተጠበቀ ሆኖ ያለምንም በቂ ምክንያት ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ስነስረአቶችን ጥበቃ አድርጎ ፖለቲካዊ ለሆኑ ጉዳዮች ጥበቃ አለማድረግ ወይም ሰልፉ መደረጉ የሚያስከትለውን ከፖሊስ አቅም በላይ የሆነ የደህንነት አደጋ ሳይገልፅ በደፈና የሚደረግ ሰልፍ የለም ማለቱ ተገቢነት የሌለው እና መረታዊውን የዴሞክረሲ መሰረት እኩልነትን የጣሰ ተግባር ነው፡፡ ፡፡
የሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 29 የአመለካከትና የሀሳብ ነፃነት
ማንም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የመሰለውን አመለካከት የመያዝ መብት ያለው ሲሆን ይህ ነፃነቱን በቃልም ሆነ በጽሑፍ ወይም በስነ ጥበብ ወይም በአደባባይ የማሰራጨት የመግለፅ መብት አለው፡፡ ሰለማዊ ሰልፍ ደግሞ ይህ መብት በከፍታ ከሚገለፅበት መንገድ አንዱ ነው፡፡ይህም ሰልፉ አለመደረጉ ይህን መሰራታዊ ሃሳብን የመግለፅ መብት ይጥሳል የዝግጅቱን ቀን ጠብቆ ከመከልከል ተገቢው ጥበቃና ድጋፍ ማድረግ እንጂ መከልከል በሕግ የተፈቀደ አይደለም፡፡
የሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 30 መሣሪያ ሳይዝ ከሌሎች ጋር መሰለፍ
ይህ የስብሰባ ዓይነት ከፍ ሲል በተገቢው መንገድ ተብራርቷል፡፡ መሰባሰቡ የሌሎች ሰላም ደህንነት መብት እንዳይነካ አዘጋጆቹ ካለባቸው ሀላፊነትና ተጠያቂነት ውጭ በሕግ የተፈቀደ መብት ስለሆነ የሚከለከል ሳይሆን ለህዝብ ጥቅም ሲባል ብቻ ከይቅርታ ጋር ወደለ፤ላ ግዜ የሚሻገር መብት እንጅ ጭርሽ እንዳይደርግ የሚከለከል መብት አይደለም፡፡
ፖሊስ ፈቃጅ እና ከልካይ ስላለመሆኑ
አንድን ሰልፍ ወይም ስብሰባ ማሳወቅ የሚገባው ሰልፉ ለሚደረግበት አስተዳደር እንጅ ለፖሊስ አይደለም አስተዳደሩ ነው ሰልፉ ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግለት የሚያሳውቀው በመሆኑም ፖሊስ የሚደረግ ሰልፍ የለም በማት የሰጠው መግለጫ በስሜ የአላግባብ መግለጫ ወጥጧል ጀከሚለው ሃሳብ በቀር ተገቢነት የሌለው ነው፡፡
መደምደሚያ
በአጠቃላይ ከፍ ሲል በተዘረዘሩት ምክንያቶች የሰልፉ ክልከላ መሠረታዊ የሆኑ የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌዎች የጣሰ በመሆኑ ሕገ ወጥ ድርጊት ሲሆን ድርጊቱን በፈፀሙ ሰዎች ላይም ሕጋዊ ሀላፊነት የሚያስከትል ነው፡፡
በሌላ በኩል በአሁኑ ግዜ በሥራ ላይ ያለው ሕግ ስለ ሕዝባዊ ፖለቲካዊ ስብሰባ ብቻ የወጣ ሌሎች ስብሰባዎችን የማይመለከት በመሆኑ በሕገ መንግሥቱ ማንኛውንም ስብሰባ በተገቢው ሥርዓት ለማከናውን ሥርዓት ደንብ እንዲወጣ ቢያዝም ይህ ባለመደረጉ ከፍተኛ መደናገር እና የመብት ጥሰት እያስከተለ ይገኛል፡፡ በመሆኑም አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕግ በሕገ መንግሥቱ ለስብሰባ በተሰጠው ትርጉም ልክ በአግባቡ ሥራ ላይ እንዲውል በዳበረ ሕግ ሊተካ ይገባዋል፡፡
ምንጭ፦ሙሉጌታ በላይ
We can give any legal analysis from lawyer’s perspective............................Amazing
እነብርጋዲዬር ጄኔራል ተፈራ ማሞ በዋስ ተለቀቁ፡፡
ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 03/2012 ዓ/ም (አብመድ) ከሰኔ 15 ጥቃት ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በማረፊያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ የነበሩት ብርጋዲዬር ጄኔራል ተፈራ ማሞ፣ ኮሎኔል አለበል አማረ እና ኮሎኔል ባምላኩ ዐባይ እያንዳንዳቸው በአስር ሺህ ብር ዋስ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ተለቀቁ፡፡

በሰኔ 15 ጥቃት ተጠርጥረው ጉዳያቸው እየተጣራ በእስር የቆዩት ተጠርጣሪዎቹ ባለፈው ሐሙስ ዋስትና ጠይቀው ነበር፤ መዝገቡን ተመልከቶ ውሳኔ ለመስጠትም ለዛሬ ተቀጥሮ ነበር፡፡ https://t.me/lawsocieties
#Sauli_Niinistö

የፊንላንድ ፕሬዚዳንት ሶሊ ኒኒስቶ ከነገ ጀምሮ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ። የ71 ዓመቱ ፕሬዚዳንት በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ እንደሚገቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

Via ENA https://t.me/lawsocieties
ይሕን ያዉቁ ነበር….., [15.10.19 09:33]
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ፋይል ለማስከፈት መሟላት ስለሚኖርባቸው ጉዳዮች

ሰላም እንዴት ናችሁ! ዛሬ የሰበር ቅሬታ ወይም አቤቱታ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቅረብ መሟላት ስላለባቸው ጉዳዮች አጭር ነገር ልናስታውሳችሁ ወደድን፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ጉዳይ በስር ፍርድ ቤት መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት በመሆኑም በሰበር ሊታረምልኝ ወይም ሊታይልኝ ይገባል የሚል አንድ አቤቱታ አቅራቢ ማሟላት የሚገባቸው ወይም ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገቡ ሁኔታዎችን እንደሚከተለው አቅረበናል፡፡

ሰበር ሰሚ ችሎት አንድን ጉዳይ ለማቅረብ መረጋገጥ ከሚገባቸው ነገሮች መካከል አንድ የስር ፍርድ ቤት ሰነዶች ይገኝበታል፡፡ በዚህም መሠረት ጉዳዩ ከወረዳ፤ ከማህበራዊ ፍርድ ቤትወይም ከመጀመሪያ ፍ/ቤት ወይም ከከፍተኛ ፍ/ቤት ወይም ከክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ወይም ከክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከተነሳ በጉዳዩ ቅር የተሰኙበት ውሳኔው /የውሳኔ ሰነዱ/
1. ቀኑ እና የፋይል ቁጥሩ የሚነበብ
2. የተሰየሙ ዳኞች ስም ያለው
3. የተከራካሪ ወገኖች ስም ያለው
መሆኑን በትክክል ያረጋግጡ!

የውሳኔ ሰነዱ ከላይ የተገለጹትን ነገሮች ሟሟላቱን ካረጋገጡ በኋላ በሁሉም ውሳኔዎች ወይም የውሳኔ ሰነዶች ላይ የየፍ/ቤቱ ማኅተም በግልጽ የሚታይና ስርዝ ድልዝ የሌለው መሆኑን ማረጋገጥ አይዘንጉ፤ በተጨማሪ የመጨረሻው ፍርድ ቤት የሰጠው መሸኛ መሠረት በማድረግ የገፆች ብዛት እንደየ ፍርድ ቤቱ ትክክለኛነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል፤ በተጨማሪም የፍ/ቤቶቹ ውሳኔዎች በግልጽ የሚነበቡና ተከታታይነት ያላቸው መሆናቸው አረጋግጠው ማቅረብ አለብዎት፡፡

የውሳኔ ሰነዶቹ ትክክለኛ መረጃ እና መኅተም መያዛቸውን ካረጋገጡ በኋላ የመጨረሻው ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ/ትዕዛዝ/ብይን ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ 90 ቀን በመቁጠር ጳጉሜን ጨምሮ ቀኑ ያላለፈበት መሆኑን ማረጋገጥ አለበዎት፡፡ ውሳኔው ከተሰጠ 90 ቀን ያለፈው እንደሆነ ከሕግ ባለሙያ ጋር ተነጋግረው የማስፈቀጃ ጥያቄ እንዲያቀርብ ማድረግ ይኖርበዎታል፤

የሰበር ቅሬታውን ወይም አቤቱታውን የሚያመለክቱት ራስዎ /በግልዎ/ ከሆነ ቅሬታው(አቤቱታው) ላይበሁሉምገጾች ላይመፈረምዎን አይዘንጉ! የሰበር ቅሬታውን ወይም አቤቱታውን የሚያቀርቡት ማረሚያ ቤት ሆነው እንደሆነ (አቤቱታው) ላይ ከርሶ ፊርማ በተጨማሪ የማረምያቤቱማህተምመኖሩን ያረጋግጡ፤

የሰበር ቅሬታዎን ወይም አቤቱታዎን በራስዎ ማቅረብ ካልቻሉና ሌላ ሰው የወከሉ እንደሆነ የተወካዩ ፊርማ በሁሉም ገጾች ላይ ማኖርና የውክልና ማስረጃ ማያያዝዎን አይዘንጉ! ውክልናው በአማርኛ ከሆነ የውክልና ኮፒ፣ ውክልናው በክልል ቋንቋ የተጸፈ ከሆነ ወደ አማርኛ የተተረጎመ ከዋናው ኮፒ ጋር በመያያዝ መቅረብዎን አይዘንጉ!

የሰበር ቅሬታዎን ወይም አቤቱታዎን በጠበቃ የሚያቀርቡ ከሆነ ጠበቃው ቅሬታው ወይም አቤቱታው ላይ መፈረሙን፣ የውክልና ማስረጃ ማያያዙን ያረጋግጡ! ውክልናው በአማርኛ ከሆነ የውክልናው ኮፒ፤ በሌላ ቋንቋ ከሆነ ደግሞ ወደ አማርኛ አስተርጉመው የአማርኛ ትርጉም በተጨማሪ የዋናው ኮፒ መያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

ከላይ የተገየፁት ውሳኔዎች፤ ውክልና፤ የጥብቅና አገልግሎት ውል፤ የተገደደበት ወረቀት/ትእዛዝ በክልል ቋንቋ የተጻፉ ከሆነ በሕጋዊ ትርጉም ጽ/ቤት ወደ አማርኛ ተተርጉመው ትርጎሞቻቸው መያያዝ አለባቸው፡፡ https://t.me/lawsocieties
Ęphřëm Ťĕ§fąhůñ, [16.10.19 10:13]
Sile re exit exam mereja bitadersun senil beakbrot entykal