የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማዘመን እና ለማሻሻል የሚረዱ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት
ን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ ውጤታማ፤ ጥራት ያለው፤ ቀልጣፋ እና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡
ፍርድ ቤቱ በዲጂታል የታገዘ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ እውን ለማድረግ የአይሲቲ መሠረተ ልማት ግንባታ የማከናወን፤ የመተግበሪያዎችን የማልማት እና አስፈላጊ ግብዓቶችን የማሟላት ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ቴክኖሎጂውን ከማልማት እና መሠረተ ልማት ከመገንባት ጎን ለጎን የዲጂታል አገልግሎቱን ለመተግበር የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እና የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡
በአዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀጽ 50 መሠረት ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ የተደገፈ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን አሰራር ስርዓት እንደሚዘረጉ እና የስርዓቱ አተገባበር በመመሪያ እንደሚወሰን ተመልክቷል፡፡
ይህ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኤሌክትሮኒክ ዘዴ አቤቱታ አቀራረብ፤ ሙግት ማከናወን እና የሪከርድ አሰራር እና አስተዳደር መመሪያ (ረቂቅ) የተዘጋጀውም ይህንኑ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለመምራት የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ለማበጀት ሲሆን በዝግጅት ሂደቱም ከፍርድ ቤት ባሻገር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎ በግብዓት ከዳበረ በኋላ ይህ ረቂቂ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡
ን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ ውጤታማ፤ ጥራት ያለው፤ ቀልጣፋ እና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡
ፍርድ ቤቱ በዲጂታል የታገዘ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ እውን ለማድረግ የአይሲቲ መሠረተ ልማት ግንባታ የማከናወን፤ የመተግበሪያዎችን የማልማት እና አስፈላጊ ግብዓቶችን የማሟላት ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ቴክኖሎጂውን ከማልማት እና መሠረተ ልማት ከመገንባት ጎን ለጎን የዲጂታል አገልግሎቱን ለመተግበር የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እና የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡
በአዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀጽ 50 መሠረት ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ የተደገፈ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን አሰራር ስርዓት እንደሚዘረጉ እና የስርዓቱ አተገባበር በመመሪያ እንደሚወሰን ተመልክቷል፡፡
ይህ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኤሌክትሮኒክ ዘዴ አቤቱታ አቀራረብ፤ ሙግት ማከናወን እና የሪከርድ አሰራር እና አስተዳደር መመሪያ (ረቂቅ) የተዘጋጀውም ይህንኑ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለመምራት የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ለማበጀት ሲሆን በዝግጅት ሂደቱም ከፍርድ ቤት ባሻገር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎ በግብዓት ከዳበረ በኋላ ይህ ረቂቂ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡