አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.86K photos
25 videos
1.86K files
3.58K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
#AddisAbaba

" በ3 ወራት ውስጥ 943 ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዲፈቻዎች ምዝገባ ተከናውኗል !! "

የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከፌደራል የመጀመርያ ፍርድ ቤት ጋር  የፍቺ እና ጉዲፈቻ ውሳኔዎችን መዝግቦ በአንድ መስኮት አገልግሎት ለመስጠት የጋራ ስምምነት ፈጽመው እየሰሩ ሲሆን ላለፉት 3 ወራት ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን አፈፃፀም በጋራ ገምግመዋል።

በዚህም ወቅት በቀረበ ሰነድ 996 ተገልጋዮች በ3 ወራት የኩነት ምዝገባ አገልግሎቱን በፍርድ ቤቶች በአንድ መስኮት ማግኘታቸው ተመላክቷል።

ከዚህም ውስጥ ውሳኔ ያገኙ 943
#ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው #ጉዲፈቻዎች በወቅቱ ምዝገባ በማድረግ በአንድ ማዕከል በፍ/ቤቶች አገልግሎት መሰጠቱ ተመላክቷል።

Via
https://t.me/addisvaitalpress/9155

@tikvahethiopia
👍10😁21😢1😭1
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማዘመን እና ለማሻሻል የሚረዱ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት
ን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡን በቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ ውጤታማ፤ ጥራት ያለው፤ ቀልጣፋ እና ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ይታመናል፡፡
ፍርድ ቤቱ በዲጂታል የታገዘ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ እውን ለማድረግ የአይሲቲ መሠረተ ልማት ግንባታ የማከናወን፤ የመተግበሪያዎችን የማልማት እና አስፈላጊ ግብዓቶችን የማሟላት ስራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ቴክኖሎጂውን ከማልማት እና መሠረተ ልማት ከመገንባት ጎን ለጎን የዲጂታል አገልግሎቱን ለመተግበር የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ እና የአሰራር ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡
በአዋጅ ቁጥር 1234/13 አንቀጽ 50 መሠረት ፍርድ ቤቶች በቴክኖሎጂ የተደገፈ የዳኝነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችላቸውን አሰራር ስርዓት እንደሚዘረጉ እና የስርዓቱ አተገባበር በመመሪያ እንደሚወሰን ተመልክቷል፡፡
ይህ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የኤሌክትሮኒክ ዘዴ አቤቱታ አቀራረብ፤ ሙግት ማከናወን እና የሪከርድ አሰራር እና አስተዳደር መመሪያ (ረቂቅ) የተዘጋጀውም ይህንኑ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለመምራት የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ለማበጀት ሲሆን በዝግጅት ሂደቱም ከፍርድ ቤት ባሻገር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎ በግብዓት ከዳበረ በኋላ ይህ ረቂቂ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡
4👍2