April 8
April 8
ሰላም ሚኪ የህግ ተማሪዎች externship payment የሚመለከት መረጃ ፈልገን ነው inbox ያደረግነው። እባክህ መረጃው ካለህ ተባበረን። በዚህ አመት የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም ህግ ትምህርት በሚሰጡ ዩንቨርስቲዎች የፈፀሙት ክፍያ ከ 20,000 ብር በላይ ነው የእኛ ዩንቨርስቲ ግን 11,000 ብር ብቻ ነው። ለምን ይኽን ያህል ልዩነት እንደፈጠረ አልገባንም በቀን ከምግብ እና ሌሎች ወጭዎች ውጭ ለትራንስፖርት ብቻ 100 ብር እናወጣለን በሳምንት 4 ቀን እንሰራለን ክፍያው current inflation rate ያገናዘበ አይደለም። እና እባክህን በዚህ ጉዳይ የምታጋራን ካለ በትህትና እንጠይቅሀለን። እናመሰግናለን።
April 9
externship payment አከፋፈል እና መጠኑን የያዘ መመሪያ ወይም ደብዳቤ ሊሆን ይችላል ማንኛውም ሰነድ ያላችሁን እንድታጋሩን በአክብሮት እንጠይቃለን።
April 10
ከማይንቀሳቀስ ንብረት ጋር በተያያዘ የመንደር ውል ህጋዊ የሚሆንባቸው 5/አምስት/ ሁኔታዎች
የማንይቀሳቀስ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል በ ፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካልተደረገ ተቀባይነት የለውም። ነገር ግን ከተወሰኑ የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በመነሳት የመንደር ውል ህጋዊ ተብለው የሚቆጠሩበት ሁኔታዎች አሉ። እነዚህ 5 ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው።
🥇 ኛ የሽያጭ ውል መኖሩ ከታመነ ወይም ካልተካደ
🥈 ገዢ ውል እንዲፈፀምለት ክስ አቅርቦ ከሳሽ መከላከያ መልሱ ላይ በመካከላቸው ውል መኖሩን ካመነ ወይም ካልካደና በሌሎች ነጥቦች ላይ መልስ ከሰጠ ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት አልተደረገም ብሎ ውድቅ ሊያደርገው አይችልም።
🥉 ኛ በማህበር በመደራጀት የተሰራ ቤት በሽያጭ ማስተላለፍ (ሰ/መ/ቁጥር 36294 ቅፅ 8)
✏️ በማህበር በመደራጀት እየተሰራ ያለ ቤት ቤቱ ተጠናቆ ካርታ እስኪወጣለት ድረስ የማህበሩ አባል የሆነ ሰው ይህን ቤት ቢያስተላልፍ ቤት የመስራት መብቱን ወይም እጣውን እንዳስተላለፈ እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረትን እንዳስተላለፈ አይቆጠርም። የማህበሩ አባል በስሙ ካርታና የባለቤትነት ማስረጃ እስካልተሰጠው ድረስ ቤቱ ወይም እየተሰራ ያለው ቤት በማህበሩ አጠቃላይ ይዞታ ስር የሚገኝ በመሆኑ የማህበሩ አባል ለ 3ኛ ወገን ሊያስተላልፍ የሚችለው እጣውን ወይም ጥቅሙን እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለውን መብት አይደለም። እንዲህ አይነት ውሎች የግድ ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ሊረጋገጡ አይገባም።
🔴 ኛ ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (ሰ/መ/ቁጥር 32222 ቅፅ 7)
✏️ ብዙን ግዜ እንዲህ አይነት ውል ከ Real Estate ቤቶች ግንባታ ጋር የተያያ ነው። ምንም እንኳን ውላቸው ላይ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ቢሉም ዉሉ በሚደረግበት ግዜ ቤቱ ያልነበረ በመሆኑ የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብትነት ከአንዱ ወደ ሌላው ተላልፏል ሊባል አይችልም። ያልነበረን ቤት ሰርቶ ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል የግንባታ ውል እንጂ የማይንቀሳቀስ ንብረት ሽያጭ ውል ሊባል የሚችል ባለመሆኑ ውሉ በፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት መረጋገጥ አይኖርበትም።
4⃣ ኛ አዋዋይ ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች ለተወሰነ ግዜ ሳይፈፀምበት የቆየ የመንደር ውል (የሰ/መ/ቁጥር 36740 ቅጽ 8)
✏️ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ በሰጠው ውሳኔ መሠረት በግራ ቀኙ መሀከል የተደረገው የመንደር ውል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ቀርቦ ነገር ግን አስተዳደራዊ ወይም የፕሮቶኮል ጉዳዮች የተሟሉት የተወሰነ ግዜ ከቆየ በኋላ ቢሆንም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰው አካል ፊት ያልተደረገ ነው በሚል ውድቅ ሊደረግ አይገባም የሚል ነው።
✏️ ችሎቱ በዚህ መዝገብ ላይ እንዳለው ቤቱን የሚመለከቱ እዳና እገዳ ለማጣራትና ክፍያ ለመፈፀም የውልና ማስረጃ ምዝገባ ጽ/ቤት በውል ላይ ማህተም ሣያሣርፍበትና የፕሮቶኮል ቁጥር ሰጥቶ ሣያረጋግጥበት የተወሰነ ጊዜ ያለፈ ቢሆንም እነዚህ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እስኪከናወኑ ድረስ በውል ላይ ማህተም ሣያርፍበት መቆየቱ ወይም የፕሮቶኮል ቁጥር ሣይሰጠው መዘግየቱ ውል እንዳልተደረገ የሚያስቆጥረው ነው ለማለት አያስችልም፡፡
5⃣ ኛ የሊዝ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል (የሰ/መ/ቁጥር 191095 & 225796)
#በአለሕግ_ጠበቃና_ሕግ_አማካሪ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
የማንይቀሳቀስ ንብረትን ለማስተላለፍ ወይም የማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ያለ መብትን ለማስተላለፍ የሚደረግ ውል በ ፍርድ ቤት ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት ካልተደረገ ተቀባይነት የለውም። ነገር ግን ከተወሰኑ የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በመነሳት የመንደር ውል ህጋዊ ተብለው የሚቆጠሩበት ሁኔታዎች አሉ። እነዚህ 5 ሁኔታዎች የሚከተሉት ናቸው።
#በአለሕግ_ጠበቃና_ሕግ_አማካሪ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
April 10
April 11
Forwarded from አለሕግAleHig ️
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
April 11
April 11
April 12
April 12
April 12
April 13
April 13
April 13
April 13
በፌደራል_ጠበቆች_እና_የጥብቅና_ሙያ_አገልግሎት_ድርጅቶች_ስለሚሰጥ_ነጻ_የሕግ_ድጋፍ_አገልግሎት_ሥርዓት.pdf
261.1 KB
የፍትሕ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት በፌደራል ጠበቆች እና የጥብቅና ሙያ አገልግሎት ድርጅቶች ስለሚሰጥ ነጻ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ሥርዓት ለመወሰን የወጣ ረቂቅ መመሪያ
April 13
April 13
የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸው ሰነዶች
ሚያዚያ 06/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
በቴምብር ቀረጥ አዋጅ ቁጥር 110/90 በአንቀጽ-3 መሰረት በሚከተሉት 12 ሰነዶች የቴምብር ቀረጥ እንዲከፈልባቸው ያዛል፡-
1. የማህበር መመስረቻ ፅሁፍና መተዳደሪያ ደንብ
2. ግልግል ሰነድ
3. ማገቻ
4. የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ
5. ውል፣ ስምምነትና የእነዚህ መግለጫ
6. የመያዣ ሰነዶች
7. የሕብረት ስምምነት
8. የስራ ቅጥር ውል
9. የኪራይ፣ የተከራይ አከራይ ማረጋገጫ
10. ማረጋገጫ
11. የውክልና ስልጠና
12. የንብረት ባለቤትነት ማስመዝገቢያ ሰነድ
ሚያዚያ 06/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
በቴምብር ቀረጥ አዋጅ ቁጥር 110/90 በአንቀጽ-3 መሰረት በሚከተሉት 12 ሰነዶች የቴምብር ቀረጥ እንዲከፈልባቸው ያዛል፡-
1. የማህበር መመስረቻ ፅሁፍና መተዳደሪያ ደንብ
2. ግልግል ሰነድ
3. ማገቻ
4. የዕቃ ማከማቻ ማረጋገጫ ሰነድ
5. ውል፣ ስምምነትና የእነዚህ መግለጫ
6. የመያዣ ሰነዶች
7. የሕብረት ስምምነት
8. የስራ ቅጥር ውል
9. የኪራይ፣ የተከራይ አከራይ ማረጋገጫ
10. ማረጋገጫ
11. የውክልና ስልጠና
12. የንብረት ባለቤትነት ማስመዝገቢያ ሰነድ
April 14