አለሕግAleHig ️
16.2K subscribers
2.85K photos
25 videos
1.86K files
3.57K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
ባለፉት 6 ወራት ብቻ 89 ዳኞች ስራ መልቀቃቸው ተሰማ::
‼️💎📊
👉🏽የደህንንት እና ፀጥታ ስጋት እንዲሁም የክፍያ ማነስ ለዳኞቹ ከስራ መልቀቅ ምክንያት ነው ተብሏል፡፡

👉🏽 “የዳኞች እስር ለፍትህ ስርዓቱ እንቅፋት ሆኗል”

#Ethiopia | ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ይህን ያለው የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ሪፖርቱን ለክልሉ ምክር ቤት ባቀረበበት ወቅት ነው።

የስድስት ወሩን የስራ ክንውን ሪፖርት በንባብ ያቀረቡት የአማራ ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አለምአንተ አግድው ናቸው፡፡

ፕሬዝደንቱ በክልሉ ያለው የሰላም እጦት ለፍትህ ስርዓቱ እንቅፋት መሆኑን በሪፖርታቸው አስረድተዋል፡፡

ይህም በእቅዳችን ለመከውን እንዳንችል አድረጎናል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡

በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት በክልሉ በየደረጃው ከሚገኙ 221 ፍርድቤቶች መካከል 28 የወረዳ ፍርድቤት ምድብ ችሎቶች አገልግሎት እየሰጡ አደሉም ተብሏል ፡፡

በዚህም ምክንያት የዜጎች ፍትህ የማግኝት መብት ላይ አሉታዊ ተጽኖ ማሳደሩን ጠቁመዋል፡፡

በግጭቱ አንዳንድ ፍርድቤቶች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ያሉት የአማራ ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አለምአንተ አግድው ከእነዚህ ፍርድ ቤቶችም ዳኞች አመራሮች እና የጉባዔው ተሿሚዎች ከስራ ውጭ ሆነዋል ብለዋል፡፡

በክልሉ ያለው የዳኞች እስራትም ለፍትህ ስርዓቱ እንቅፋት እንደሆነባቸው ተናግረዋል፡፡

ችግር ያለባቸውን ዳኞች በህገመንግስቱ በተቀመጠው ስርዓት መሰረት በዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ለማየት ከዛም ያለፈ ሲሆን በመደበኛው ስርዓት ተጠያቂ ለማድረግ ቁርጠኛ ነን ብለዋል፡፡

ነገር ግን በአንዳንድ ክትትሎቻችን የተወሰኑ የዳኞች እስራት ከሰጠዋቸው ወሳኔዎች ጋር የሚገናኝ ሆኖ ስላገኘናቸው የተከበረው ምክርቤት ማስተካከያ እንዲደረግበት በአፅኖት እንዲታይልን እንፈልጋለን ሲሉ ፕሬዚዳንቱ ምክር ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

በክልሉ 9ኝ ዳኞች በአሁኑ ወቅት በእስር ላይ መሆናቸውንም የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ አሳሳ የዛሬ ወር መናገራቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

መሃበሩ ዳኞችን ከችሎት እያነሱ ማሰር ኢትዮጵያ ፈርማ ባጸደቀቻቸው አለም አቀፍ ህጎችም ሆነ በህገመንግስቷ ሲታይ ተቀባይነት ስለሌለው ሊቆም ይገባል ሲል በተደጋጋሚ ሲጠይቅ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

ከወራቶች በፊት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ለክልሉ ፕሬዝዳንት እና ለክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ በፃፈው ደብዳቤ ችግሩ መኖሩን አረጋግጫለው ብሏል፡፡

ከድብዳቤው ላይ እንደተመለከትነው በፍርድ ቤት ስራ ላይ የአስፈፃሚው አካል ጣልቃ ገብነት መኖሩን ኢሰመኮ አረጋግጧል እንዲቆምም ጠይቋል፡፡
via sheger FM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
February 15
February 15
February 16
February 16
February 16
#የቤት_ኪራይ ውል ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ ተከራይ ቤቱን ለቆ እንዲያስረክበው ለቆ የማያስረክብ ከሆነ ግን የኪራይ ተመኑ በማስጠንቀቂያው ላይ በተመለከተው ተመን እንደሚሆን በመግለጽ አከራይ ማስጠንቀቂያ ሰጥቶት ተከራዩ ቤቱን ለቆ ካላስረከበ ተከራይ በኪራይ በቤቱ መገልገሉን እንዲቀጥል አከራዩ አለመፍቀዱን በማያሻማ ሁኔታ የሚያሳይ ቢሆንም ተከራይ ሊከፍል የሚገባውን የኪራይ ተመን በተመለከተ ውሉ ላለመራዘሙ ዋናው ምክንያት የኪራይ ተመን አለመግባባት ከሆነና ተከራይ የኪራይ ተመን መጨመርን በግልጽ ከተቃወመ ሊከፍል የሚገባው በማስጠንቀቂያው ላይ በተገለጸው የኪራይ ተመን ሳይሆን በቀድሞው ተመን ነው።
በዚህ መዝገብ ተከራይ ቤቱን ለ4 ዓመታት ተከራይቶ የውሉ ዘመን ሲያልቅ ቤቱን ለቆ እንዲያስረክብ የማያስረክብ ከሆነ የኪራይ ተመኑ ብር 80,000 እንደሚሆን በመግለጽ ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ሊከፍል የሚገባው በ 20,000 ነው በሚል በሰበር ችሎቱ ውሳኔ ተሰጥቷል።
ሰ/መ/ቁ. 220884 ቀን ጥቅምት 04 ቀን 2015 ዓ/ም
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ📱
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website 📱 alehig.com
https://linktr.ee/alehig
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
February 18
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
February 21