African Leadership Excellence Academy
2.13K subscribers
2.38K photos
89 videos
6 files
104 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም (አፍሌክስ)
#ከአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ #የለውጥ_Reform #የማስፋት_Scaling_Up እና #የመሰረታዊ_እመርታ_Transformation ስራዎች መካከል አንዱ የሆነው የቀድሞ ህንፃዎችን በማደስ ለአገልግሎት ዝግጁ የማድረግ ተግባር ስራ ተጀምሯል::

በሱሉልታ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት የቀድሞ ህንጻዎች የአስተዳደር ቢሮውን በአዲስ መልክ የማደስ ተግባር ተጀምሯል።

ለእድሳቱም #የኢትዮጵያ_መንገዶች_ባለስልጣን #ERA አጠቃላይ ወጭውን የሚሸፍን ሲሆን ለዕድሳት ደግሞ #የኢትዮጵያ_ኢንጂነሪንግ_ኮርፖሬሽን #ECC ውል ገብቶ ስራ ጀምሯል።

የህንጻው እድሳት እንደተጠናቀቀም የአካዳሚው ሰራተኞች ወደ አዲሱ ህንጻ ተዛውረው ስራ ይጀምራሉ።

በዚህም አካዳሚው ለቢሮ ኪራይ የሚያወጣውን ገንዘብ ከማስቀረቱም በላይ ለአመራር ልማት እና ለጥናትና ምርምር ስራዎች ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ተብሏል።

የህንፃ እድሳቱ ሲጠናቀቅ የሚኖረውን ገፅታ የሚያመላክተው የ3D ቪዲዮ እንደሚያሳየው ሁሉንም አይነት መሰረተ ልማት ያካተተው ይህ የህንፃ እድሳት በወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅም ተገልጿል::