የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይሬክተር ጀኔራሎች ጋር ተወያዩ።
ርዕሰ አካዳሚው ተቋሙ በሪፎርምና በሽግግር ስራዎቹ ውስጥ ሊሰራቸው ስላቀዳቸው የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ገለጻ አድርገዋል። አካዳሚው በሪፎርም ስራዎቹ ውስጥ አስራ ሶስት የትኩረት መስኮችን ለይቶ እየሰራ እንደሆነና ከእነዚህ ውስጥ ለስምንቱ ቅድሚያ በመስጠት ወደ ስራ እንደገባ አቶ ዛዲግ አብራርተዋል።
ተቋሙ እንደ ስሙ አፍሪካዊ እንዲሆን የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎች እንደተሰሩ የገለጹት አቶ ዛዲግ፤ በዋናነትም በምክትል ፕሬዚደንት የሚመራ የአፍሪካ ጉዳዮች ዘርፍ ለማቋቋምና ወደ ስራ ለመግባት ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።
በሱሉልታ የሚገኘው የአመራር ልማት እና የስልጠና ማዕከል አፍሪካዊ ቅርጽና ይዘት እንዲኖረው እየተሰራ እንደሆነና አፍሪካውያን ወንድሞችንና እህቶችን በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ለማስተማር ካሪኩለም መቀረጹን ርዕሰ አካዳሚው አስታውሰው፤ ለፓን አፍሪካኒዝም አስተሳሰብ መስረጽ አካዳሚው የድርሻውን ለማበርከት እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል። የሀገራችንን እና የአፍሪካ አመራሮችን በስልጠና ለማብቃትም አራት ጠቅላላ ፕሮግራሞችና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እንደተቀረጹ አቶ ዛዲግ ተናግረዋል።
በሌሎች ስምንት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችና የሪፎርምና ስራዎች ላይ ገለጻ የተደረገላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይሬክተር ጀኔራሎች አስተያየትና ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን በርዕሰ አካዳሚው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
ርዕሰ አካዳሚው ተቋሙ በሪፎርምና በሽግግር ስራዎቹ ውስጥ ሊሰራቸው ስላቀዳቸው የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ገለጻ አድርገዋል። አካዳሚው በሪፎርም ስራዎቹ ውስጥ አስራ ሶስት የትኩረት መስኮችን ለይቶ እየሰራ እንደሆነና ከእነዚህ ውስጥ ለስምንቱ ቅድሚያ በመስጠት ወደ ስራ እንደገባ አቶ ዛዲግ አብራርተዋል።
ተቋሙ እንደ ስሙ አፍሪካዊ እንዲሆን የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎች እንደተሰሩ የገለጹት አቶ ዛዲግ፤ በዋናነትም በምክትል ፕሬዚደንት የሚመራ የአፍሪካ ጉዳዮች ዘርፍ ለማቋቋምና ወደ ስራ ለመግባት ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።
በሱሉልታ የሚገኘው የአመራር ልማት እና የስልጠና ማዕከል አፍሪካዊ ቅርጽና ይዘት እንዲኖረው እየተሰራ እንደሆነና አፍሪካውያን ወንድሞችንና እህቶችን በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ለማስተማር ካሪኩለም መቀረጹን ርዕሰ አካዳሚው አስታውሰው፤ ለፓን አፍሪካኒዝም አስተሳሰብ መስረጽ አካዳሚው የድርሻውን ለማበርከት እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል። የሀገራችንን እና የአፍሪካ አመራሮችን በስልጠና ለማብቃትም አራት ጠቅላላ ፕሮግራሞችና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እንደተቀረጹ አቶ ዛዲግ ተናግረዋል።
በሌሎች ስምንት የአመራር ልማት ፕሮግራሞችና የሪፎርምና ስራዎች ላይ ገለጻ የተደረገላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይሬክተር ጀኔራሎች አስተያየትና ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን በርዕሰ አካዳሚው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በኢንዱስትሪ አመራር ልማት ፕሮግራም ላይ ለመስራት ያቀደው ሪፎርም እና ሽግግር የዘርፉን ክፍተት ለመድፈን ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ክቡር መላኩ አለበል ገለፁ::
የአካዳሚውን ሪፎርም ሽግግር እና ማስፋት በተመለከተ ለክቡር ሚኒስትሩ እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ገለፃ ተደርጓል::
የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደገለፁት ከሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ውስጥ የኢንዱስትሪ አመራር ልማት አንዱ በመሆኑ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል::
አቶ ዛዲግ አያይዘውም አካዳሚው በሪፎርም እና ማስፋፋት እቅዶቹ ውስጥ ከያዛቸው ስራዎች መካከል አስራ ሁለት የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ስራ ላይ እንደሚውሉ እና ከኢንዱስትሪ ጋር የሚገናኘውን በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል::
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ክቡር መላኩ አለበል በበኩላቸው አፍሌክስ የጀመረው ሪፎርም እና ማስፋፋት የኢንዱስትሪ ዘርፉን የአመራር ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ ጠቅሰው ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የልማት አጋሮች እና ባለሀብቶች ጋር በመሆን የአካዳሚውን ተልእኮ ለማሳካት እንደሚሰሩ እና አፍሌክስን ለባለ ድርሻ አካላት በማስተዋወቅ አለም አቀፍ ጉባኤዎች በአካዳሚው እንዲደረጉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይሰራል ብለዋል::
ሁለቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል::
የአካዳሚውን ሪፎርም ሽግግር እና ማስፋት በተመለከተ ለክቡር ሚኒስትሩ እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ገለፃ ተደርጓል::
የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደገለፁት ከሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ውስጥ የኢንዱስትሪ አመራር ልማት አንዱ በመሆኑ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባ ጠቅሰዋል::
አቶ ዛዲግ አያይዘውም አካዳሚው በሪፎርም እና ማስፋፋት እቅዶቹ ውስጥ ከያዛቸው ስራዎች መካከል አስራ ሁለት የሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ስራ ላይ እንደሚውሉ እና ከኢንዱስትሪ ጋር የሚገናኘውን በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል::
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ክቡር መላኩ አለበል በበኩላቸው አፍሌክስ የጀመረው ሪፎርም እና ማስፋፋት የኢንዱስትሪ ዘርፉን የአመራር ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ ጠቅሰው ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የልማት አጋሮች እና ባለሀብቶች ጋር በመሆን የአካዳሚውን ተልእኮ ለማሳካት እንደሚሰሩ እና አፍሌክስን ለባለ ድርሻ አካላት በማስተዋወቅ አለም አቀፍ ጉባኤዎች በአካዳሚው እንዲደረጉ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይሰራል ብለዋል::
ሁለቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚና የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደረጉ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በተቋሙ የሪፎርም፤ የሽግግርና የማስፋት ስራዎች ዙሪያ ለክቡር ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እና ለከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ገለጻ አድርገዋል።
አፍሌክስ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ አብርሃ፤ በውሀና ኢነርጂ ዘርፍ ውስጥ ያሉ የስልጠና፤ የጥናት እና የምርምር ስራዎች ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በመሆን ለመስራት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ካለው ሰፊ ልምድና አቅም አንጻር በተመረጡ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቀረጻ እና ለፕሮግራሞቹ የሚያስፈልገውን ሀብት መሸፈን ላይ ትኩረት አድርጎ ቢሰራ የተቋሙን የመፈጸም አቅም ማሳደግ እንደሚቻል የጠቀሱት አቶ ዛዲግ አፍሌክስም ለዚሁ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
የውሀና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው ከፍተኛ የስልጠና ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሪፎርም፤ በሽግግር እና በማስፋት የያዛቸውን ስራዎች ለማገዝ አብረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አያይዘውም አካዳሚው በጥናትና ምርምር ማዕከሉ አህጉር አቀፍ የውሀ እና ኢነርጂ ጉዳዮችን አካቶ ለመስራት ማቀዱ በዘርፉ ያለውን ክፍተት እና ውስንነት ለማረምና ለማስተካከል እንደሚያግዝ ጠቅሰው ለዚሁ እንዲረዳ በአጭር እና በረጅም ጊዜ የሚከናወኑ ተግባራትን የሚያመላክት የመግባቢያ እና የተግባር ማስፈጸሚያ መነሻ እንዲዘጋጅ ሀሳብ አቅርበዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በተቋሙ የሪፎርም፤ የሽግግርና የማስፋት ስራዎች ዙሪያ ለክቡር ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እና ለከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ገለጻ አድርገዋል።
አፍሌክስ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ዛዲግ አብርሃ፤ በውሀና ኢነርጂ ዘርፍ ውስጥ ያሉ የስልጠና፤ የጥናት እና የምርምር ስራዎች ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በመሆን ለመስራት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ካለው ሰፊ ልምድና አቅም አንጻር በተመረጡ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቀረጻ እና ለፕሮግራሞቹ የሚያስፈልገውን ሀብት መሸፈን ላይ ትኩረት አድርጎ ቢሰራ የተቋሙን የመፈጸም አቅም ማሳደግ እንደሚቻል የጠቀሱት አቶ ዛዲግ አፍሌክስም ለዚሁ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
የውሀና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው ከፍተኛ የስልጠና ፍላጎት እንዳለው ጠቅሰው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሪፎርም፤ በሽግግር እና በማስፋት የያዛቸውን ስራዎች ለማገዝ አብረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አያይዘውም አካዳሚው በጥናትና ምርምር ማዕከሉ አህጉር አቀፍ የውሀ እና ኢነርጂ ጉዳዮችን አካቶ ለመስራት ማቀዱ በዘርፉ ያለውን ክፍተት እና ውስንነት ለማረምና ለማስተካከል እንደሚያግዝ ጠቅሰው ለዚሁ እንዲረዳ በአጭር እና በረጅም ጊዜ የሚከናወኑ ተግባራትን የሚያመላክት የመግባቢያ እና የተግባር ማስፈጸሚያ መነሻ እንዲዘጋጅ ሀሳብ አቅርበዋል።