በትውውቅ መርሀ ግብሩ ላይ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክ፤ ከመከላከያ፤ ከትምህርት፤ ከኢንዱስትሪ፤ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ፤ ከግብርና ሚ/ር መስሪያ ቤቶች፤ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል፤ ከኢትዮ ኢንጂነሪንግ፤ ከስፔስ ሳይንስ፤ ከምድር ባቡር፤ ከፌዴራል ፖሊስ እና ሌሎችም ተቋማት የመጡ ተሳታፊዎች የተካፈሉ ሲሆን ሱሉሉታ የሚገኘውን የአካዳሚውን የስልጠና ማዕከልም ጎብኝተዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከሜሊንዳ እና ቢልጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን ለሚሰጠው የሴቶች አመራር ልማት ስልጠና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብር ተከናወነ፡፡ ሰልጣኞችም የእርስ በእርስ ትውውቅ አድርገዋል፡፡
የትውውቅ መርሀ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የአካዳሚው የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ እንደተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እንደ አዲስ በህግ ከተቋቋመ ጀምሮ በስልጠና እና በምርምር የሰራቸውን ስራዎች የገለፁ ሲሆን የከፍተኛ አመራር ስልጠናን በመስጠት ላይ እንደሆነና ለፖሊሲ አውጭውና ለስልጠና ፕሮግራሙ ግብዓት የሚውሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የስልጠናውን መስፈርት አሟልተው ከተለያዩ ተቋማት የመጡ ሴት የስልጠና ተሳታፊዎችን አቅም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አካዳሚው የራሱን ሚና እንደሚጫወትና ስልጠናውን ተከታትለው በቁርጠኝነት የሚያጠናቅቁ ተሳታፊዎችም በሀገር ግንባታ ውስጥ የራሳቸውን የአመራር ድርሻ እንዲያበረክቱ ድጋፍና እገዛ እንደሚደረግና ሰልጣኞችም ስልጠናውን በተገቢው መንገድ እንዲከታተሉና ለውጤት እንዲበቁ ም/ል ርዕሰ አካዳሚዋ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡
የሴቶች አመራር ልማት ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ መስፍን በሀይሉ የፕሮጀክቱን ዓላማ በስፋት የገለፁ ሲሆን ሰልጣኞች ወደ ፊት ስለሚሰለጥኑባቸው ርዕሰ ጉዳዮችና ከስልጠናው የሚጠበቀውን ውጤትም አብራርተዋል፡ ስልታዊ አስተሳሰብን ማበልፀግ፤ ችግርን ተረድቶ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መፍታት፤ ውጤታማ የተግባቦት ክህሎትን ማሳደግ፤ የቡድን ስራ ግንባታና የባለድርሻ አካላት ስራ አመራር ከስልጠናው የሚጠበቁ ውጤቶች መሆናቸውንም አቶ መስፍን ጠቅሰዋል፡፡
የትውውቅ መርሀ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የአካዳሚው የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ እንደተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እንደ አዲስ በህግ ከተቋቋመ ጀምሮ በስልጠና እና በምርምር የሰራቸውን ስራዎች የገለፁ ሲሆን የከፍተኛ አመራር ስልጠናን በመስጠት ላይ እንደሆነና ለፖሊሲ አውጭውና ለስልጠና ፕሮግራሙ ግብዓት የሚውሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የስልጠናውን መስፈርት አሟልተው ከተለያዩ ተቋማት የመጡ ሴት የስልጠና ተሳታፊዎችን አቅም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አካዳሚው የራሱን ሚና እንደሚጫወትና ስልጠናውን ተከታትለው በቁርጠኝነት የሚያጠናቅቁ ተሳታፊዎችም በሀገር ግንባታ ውስጥ የራሳቸውን የአመራር ድርሻ እንዲያበረክቱ ድጋፍና እገዛ እንደሚደረግና ሰልጣኞችም ስልጠናውን በተገቢው መንገድ እንዲከታተሉና ለውጤት እንዲበቁ ም/ል ርዕሰ አካዳሚዋ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡
የሴቶች አመራር ልማት ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ መስፍን በሀይሉ የፕሮጀክቱን ዓላማ በስፋት የገለፁ ሲሆን ሰልጣኞች ወደ ፊት ስለሚሰለጥኑባቸው ርዕሰ ጉዳዮችና ከስልጠናው የሚጠበቀውን ውጤትም አብራርተዋል፡ ስልታዊ አስተሳሰብን ማበልፀግ፤ ችግርን ተረድቶ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መፍታት፤ ውጤታማ የተግባቦት ክህሎትን ማሳደግ፤ የቡድን ስራ ግንባታና የባለድርሻ አካላት ስራ አመራር ከስልጠናው የሚጠበቁ ውጤቶች መሆናቸውንም አቶ መስፍን ጠቅሰዋል፡፡
በኢትዮጵያ የሚገኙ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎበኙ፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በኢትዮጵያ የራሺያ ፌዴሬሽን አምባሳደር Yevgeny Tarekhin ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይቱ ላይ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት አካዳሚው እንደ አዲስ በሚኒስትሮች ም/ቤት ከተቋቋመ ጀምሮ የመንግስትንና የግል ተቋማትን አመራሮች በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ተቋማዊ ሪፎርም እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
ተቋማዊ ሪፎርሙ ሲጠናቀቅም አካዳሚው ሊያከናውናቸው ያቀዳቸው በርካታ አገር አቀፍና አህጉር አቀፍ ፕሮግራሞች መኖራቸውን የጠቀሱት ዶ/ር ምህረት ይህንንም ለማሳካት ተቋሙ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ስትራቴጂያዊ አጋርነትን በመመስረትም የአካዳሚውን ተልዕኮ ለማሳካት እየተሰራ እንደሆነ የተናገሩት ርዕሰ አካዳሚው ከራሺያ ፌዴሬሽን ጋር በስልጠና እና በምርምር መስኮች በመስራትም የተቋሙን የመፈፀም አቅም ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸውም ገልፀዋል፡፡
አምባሳደር Evgeny Tarekhin በበኩላቸው ከአካዳሚው ጋር በጋራ ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት ገልፀው በቀጣይ በሚደረጉ ውይይቶች የሚዳብር ሀሳብ እንዳላቸው አስታውሰው አካዳሚው ላደረገላቸው መልካም አቀባበልና ግብዣ አመስግነዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት አካዳሚው እንደ አዲስ በሚኒስትሮች ም/ቤት ከተቋቋመ ጀምሮ የመንግስትንና የግል ተቋማትን አመራሮች በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ተቋማዊ ሪፎርም እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
ተቋማዊ ሪፎርሙ ሲጠናቀቅም አካዳሚው ሊያከናውናቸው ያቀዳቸው በርካታ አገር አቀፍና አህጉር አቀፍ ፕሮግራሞች መኖራቸውን የጠቀሱት ዶ/ር ምህረት ይህንንም ለማሳካት ተቋሙ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ስትራቴጂያዊ አጋርነትን በመመስረትም የአካዳሚውን ተልዕኮ ለማሳካት እየተሰራ እንደሆነ የተናገሩት ርዕሰ አካዳሚው ከራሺያ ፌዴሬሽን ጋር በስልጠና እና በምርምር መስኮች በመስራትም የተቋሙን የመፈፀም አቅም ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸውም ገልፀዋል፡፡
አምባሳደር Evgeny Tarekhin በበኩላቸው ከአካዳሚው ጋር በጋራ ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት ገልፀው በቀጣይ በሚደረጉ ውይይቶች የሚዳብር ሀሳብ እንዳላቸው አስታውሰው አካዳሚው ላደረገላቸው መልካም አቀባበልና ግብዣ አመስግነዋል፡፡