ጥቅምት 28፣ 2015 ዓ.ም (አአልአ) አካዳሚው ለኢትዮጵያ ጉልህ ጠቀሜታ የሚሰጡ የተለያዩ ስልጠናዎችን እየሰጠ መሆኑ ተገለፀ። ይሕ የተገለፀው በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ውስጥ ለመካከለኛና ለከፍተኛ ዲፕሎማቶች በተዘጋጀ ስልጠና መክፈቻ ላይ ነው፡፡
የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት አካዳሚው ለሀገር ግንባታ ትልቅ ሚና የሚኖራቸውን ስልጠናዎች እየሰጠ እንደሆነና የዛሬውም ስልጠና የዚሁ አንድ አካል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው እንደገለፁት በስልጠናው ዲፕሎማቶች ብቃት ያለው ስብዓና እንዲላበሱ እና የላቀ የዲፕሎማሲ ሰራ ለመፈፀም የሚያስችል ከፍተኛ ስልጠና በአካዳሚው እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል ። ዶ/ር ምህረት አያይዘውም ዲፕሎማቶች ኢትዮጵያ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ ለብሔራዊ ጥቅሟ መከበር አበክረው ሊሰሩ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በበኩላቸው ሥልጠናው በዲፕሎማሲ ባህልና ታሪክ ፣ በዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ሥርዓት ውስጥ ያሉ ወቅታዊ የዲፕሎማሲ ተግባራት ላይ ያተኮረ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የተለያዩ የዲፕሎማሲ ጫናዎች ውስጥ መሆኗን ጠቅሰው ፥ ዲፕሎማቶች ወቅቱን ያገናዘበ የዲፕሎማሲ ሥራ ሊያከናውኑ ይገባል ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የዲጅታል ዲፕሎማሲ ስራን ማጠናከር ፣ እውነትን እና ሀቅን በመያዝ የተለያዩ አካላት ተፅዕኖ በመቋቋም ተልዕኮውን በአግባቡ የሚወጣ ዲፕሎማት እንደሚያስፈልግ ነው የገለጹት፡፡
አምባሳደር ብርቱካን ፥ የዲፕሎማቶችን ብቃት ለማሳደግ የሰው ኃይል ልማት ሥራ፣ የውጭ አገልግሎት አዋጅ ማሻሻያና ብዝሃነትን ያገናዘበ ምርጫ በማድረግ አቅምና ብቃት በመጨመር የበለጠ የመፈፀም አቅማችን እያጠናከርን ነው ብለዋል ።
የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት አካዳሚው ለሀገር ግንባታ ትልቅ ሚና የሚኖራቸውን ስልጠናዎች እየሰጠ እንደሆነና የዛሬውም ስልጠና የዚሁ አንድ አካል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ርዕሰ አካዳሚው እንደገለፁት በስልጠናው ዲፕሎማቶች ብቃት ያለው ስብዓና እንዲላበሱ እና የላቀ የዲፕሎማሲ ሰራ ለመፈፀም የሚያስችል ከፍተኛ ስልጠና በአካዳሚው እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል ። ዶ/ር ምህረት አያይዘውም ዲፕሎማቶች ኢትዮጵያ ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ ለብሔራዊ ጥቅሟ መከበር አበክረው ሊሰሩ እንደሚገባም ጠቁመዋል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በበኩላቸው ሥልጠናው በዲፕሎማሲ ባህልና ታሪክ ፣ በዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ሥርዓት ውስጥ ያሉ ወቅታዊ የዲፕሎማሲ ተግባራት ላይ ያተኮረ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የተለያዩ የዲፕሎማሲ ጫናዎች ውስጥ መሆኗን ጠቅሰው ፥ ዲፕሎማቶች ወቅቱን ያገናዘበ የዲፕሎማሲ ሥራ ሊያከናውኑ ይገባል ብለዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የዲጅታል ዲፕሎማሲ ስራን ማጠናከር ፣ እውነትን እና ሀቅን በመያዝ የተለያዩ አካላት ተፅዕኖ በመቋቋም ተልዕኮውን በአግባቡ የሚወጣ ዲፕሎማት እንደሚያስፈልግ ነው የገለጹት፡፡
አምባሳደር ብርቱካን ፥ የዲፕሎማቶችን ብቃት ለማሳደግ የሰው ኃይል ልማት ሥራ፣ የውጭ አገልግሎት አዋጅ ማሻሻያና ብዝሃነትን ያገናዘበ ምርጫ በማድረግ አቅምና ብቃት በመጨመር የበለጠ የመፈፀም አቅማችን እያጠናከርን ነው ብለዋል ።
ሴቶችን ወደ ውሳኔ ሰጭነት ለማምጣትና አቅማቸውን ለመገንባት እየተሰራ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ በሴቶች አመራር ልማትና ማብቃት ፕሮጀክት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደርጓል ፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ በምክክር መድረኩ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት አካዳሚው ከቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን (Bill and Melinda Gates Foundation) ጋር በመተባበር ሴቶችን ለማሳደግ የሚረዳ የሴቶችን የውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ የሚረዳ የሴቶች የአመራር ልማት ፕሮጀክት (WLDP) ቀርፆ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል፡፡
ወ/ሮ ሕይወት አያይዘውም ፕሮጀክቱ ሊያሳካ ያቀዳቸውን ውጥኖች የጠቆሙ ሲሆን መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመተባበር ሴት አመራሮችን ለማብቃትና በቁልፍ የመካከለኛ አመራር ቦታዎች ላይ ከፍተኛ ሚና እንዲኖራቸው ይሰራል ብለዋል ፡፡
የምክክር መድረኩም በፕሮጀክቱ ላይ የሚሳተፉ ሴት አመራሮችን ለመምረጥና በቀጣይ በጋራ መሰራት በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እንደሆነ ም/ርዕሰ አካዳሚዋ ተናግረዋል ፡፡
የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ መስፍን በሃይሉ ስለ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ከመንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት የሚመረጡ የሴት አመራሮችን መስፈርት አብራርተዋል፡፡ በቀረበው ገለፃ ላይም ጥሪ የተደረገላቸው የተቋማት አመራሮች ጥያቄና አሰስተያየት ያቀረቡ ሲሆን በመድረኩ በቂ ምላሽም ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ ከ10 በላይ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ በምክክር መድረኩ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት አካዳሚው ከቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን (Bill and Melinda Gates Foundation) ጋር በመተባበር ሴቶችን ለማሳደግ የሚረዳ የሴቶችን የውሳኔ ሰጭነት ሚና ለማሳደግ የሚረዳ የሴቶች የአመራር ልማት ፕሮጀክት (WLDP) ቀርፆ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል፡፡
ወ/ሮ ሕይወት አያይዘውም ፕሮጀክቱ ሊያሳካ ያቀዳቸውን ውጥኖች የጠቆሙ ሲሆን መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመተባበር ሴት አመራሮችን ለማብቃትና በቁልፍ የመካከለኛ አመራር ቦታዎች ላይ ከፍተኛ ሚና እንዲኖራቸው ይሰራል ብለዋል ፡፡
የምክክር መድረኩም በፕሮጀክቱ ላይ የሚሳተፉ ሴት አመራሮችን ለመምረጥና በቀጣይ በጋራ መሰራት በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እንደሆነ ም/ርዕሰ አካዳሚዋ ተናግረዋል ፡፡
የፕሮጀክቱ ማናጀር አቶ መስፍን በሃይሉ ስለ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ከመንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት የሚመረጡ የሴት አመራሮችን መስፈርት አብራርተዋል፡፡ በቀረበው ገለፃ ላይም ጥሪ የተደረገላቸው የተቋማት አመራሮች ጥያቄና አሰስተያየት ያቀረቡ ሲሆን በመድረኩ በቂ ምላሽም ተሰጥቶባቸዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ ከ10 በላይ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
አለም አቀፍ የኤድስ ቀን
"ፍትሃዊና ተደራሽ የኤች አይ ቪ/ኤድስ አገልግሎት!
እንዲሁም አለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን"ሴትን አከብራለሁ፤ ጥቃቷንም እከላከላለሁ!" በሚል መሪ ቃል በእግር ጉዞ እና በውይይት እንደሚከበር በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የሴቶች፣ ወጣቶች እና ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ ገልጸዋል::
"ፍትሃዊና ተደራሽ የኤች አይ ቪ/ኤድስ አገልግሎት!
እንዲሁም አለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን"ሴትን አከብራለሁ፤ ጥቃቷንም እከላከላለሁ!" በሚል መሪ ቃል በእግር ጉዞ እና በውይይት እንደሚከበር በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የሴቶች፣ ወጣቶች እና ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ ገልጸዋል::
ሙስና የአገር ነቀርሳ በመሆኑ መንግስት ይህንን ትኩረት አድርጎ እየወሰደ ያለው እርምጃ የሚበረታታ ነው ሲሉ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ምክትል ርእሰ አካዳሚ ዶክተር ወንድዬ ለገሰ ተናገሩ።
አካዳሚው ግንዛቤ በመፍጠር የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣም ገልጸዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በዓለም አቀፍ ለ19ኛ ጊዜ እና በአገር አቀፍ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ ሙስና ቀንን "ሙስናን መታገል በተግባር" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሁነቶች በማክበር ላይ ነው፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ምክትል ርእሰ አካዳሚ ዶክተር ወንድዬ ለገሰ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፣ ሙስና የአገር ነቀርሳ መሆኑን በመጥቀስ መንግስት ይህንን ትኩረት አድርጐ እየወሰደ ያለው እርምጃ የሚበረታታ ነው ብለዋል።
የአካዳሚው የስነምግባርና ፀረ ሙስና ዳዳይሬክተር ወይዘሮ አልማዝ መኮንን ባቀረቡት ጽሁፍ፣ ሙስና የአገርን ኢኮኖሚ የሚገታ፣ የአለም ስጋት፣ አደገኛና ድንበር ዘለል ወንጀል በመሆኑ በጋራ መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
ሁሉን አቀፍ እድገትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ሙስናን በተግባር መታገል ትኩረት የሚሻ ጉዳይ እንደሆነም ተናግረዋል።
መርሐግብሩ በፓናል ውይይት፣ ስነ ጽሁፍ፣ ጥያቄና መልስና መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሁነቶች ተከናውኗል፡፡።
አካዳሚው ግንዛቤ በመፍጠር የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣም ገልጸዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በዓለም አቀፍ ለ19ኛ ጊዜ እና በአገር አቀፍ ለ18ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ ሙስና ቀንን "ሙስናን መታገል በተግባር" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሁነቶች በማክበር ላይ ነው፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ምክትል ርእሰ አካዳሚ ዶክተር ወንድዬ ለገሰ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፣ ሙስና የአገር ነቀርሳ መሆኑን በመጥቀስ መንግስት ይህንን ትኩረት አድርጐ እየወሰደ ያለው እርምጃ የሚበረታታ ነው ብለዋል።
የአካዳሚው የስነምግባርና ፀረ ሙስና ዳዳይሬክተር ወይዘሮ አልማዝ መኮንን ባቀረቡት ጽሁፍ፣ ሙስና የአገርን ኢኮኖሚ የሚገታ፣ የአለም ስጋት፣ አደገኛና ድንበር ዘለል ወንጀል በመሆኑ በጋራ መታገል እንደሚገባ አመላክተዋል።
ሁሉን አቀፍ እድገትና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ሙስናን በተግባር መታገል ትኩረት የሚሻ ጉዳይ እንደሆነም ተናግረዋል።
መርሐግብሩ በፓናል ውይይት፣ ስነ ጽሁፍ፣ ጥያቄና መልስና መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሁነቶች ተከናውኗል፡፡።
ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃት የሚያስከትለውን ማህበራዊ፤ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንደሚያስፈልጉና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ተግባራዊ ለውጥ ላይ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለፀ፡፡
ይኽ የተገለፀው ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀን በአካዳሚ ደረጃ ሲከበር ነው፡፡ አለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን "ሴትን አከብራለሁ፤ ጥቃቷንም እከላከላለሁ!" እንዲሁም አለም አቀፍ የኤድስ ቀን "ፍትሃዊና ተደራሽ የኤች አይ ቪ/ኤድስ አገልግሎት! በሚል መሪ ቃል በእግር ጉዞ እና በውይይት በተከበረበት ወቅት ነው፡፡
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት ፆታዊ ጥቃትንም ሆነ ኤድስን ለመከላከል ተግባራዊ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ሁሉም የአካዳሚው ማህበረሰብ ከመድረኩ የሚያገኘውን ግንዛቤ ወደ ተግባር በመለወጥ ለሴቶች ያለውን ድጋፍና አጋርነት በተግባር ማሳየት ይገባል ሲሉም አክለዋል፡፡
በአካዳሚው የሴቶች፣ ወጣቶች እና ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ በበኩላቸው ተቋሙ የፆታ ጥቃትን ለመከላከልና ወላጆቻቸውን በኤድስ ያጡ ህጻናትን ለመደገፍ ያለውን ጥረት አመላክተው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀንን በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብሮች ሱሉሉታ በሚገኘው የስልጠና ማዕከል ውስጥ አክብረዋል፡፡
ይኽ የተገለፀው ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀን በአካዳሚ ደረጃ ሲከበር ነው፡፡ አለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን "ሴትን አከብራለሁ፤ ጥቃቷንም እከላከላለሁ!" እንዲሁም አለም አቀፍ የኤድስ ቀን "ፍትሃዊና ተደራሽ የኤች አይ ቪ/ኤድስ አገልግሎት! በሚል መሪ ቃል በእግር ጉዞ እና በውይይት በተከበረበት ወቅት ነው፡፡
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት ፆታዊ ጥቃትንም ሆነ ኤድስን ለመከላከል ተግባራዊ የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ሁሉም የአካዳሚው ማህበረሰብ ከመድረኩ የሚያገኘውን ግንዛቤ ወደ ተግባር በመለወጥ ለሴቶች ያለውን ድጋፍና አጋርነት በተግባር ማሳየት ይገባል ሲሉም አክለዋል፡፡
በአካዳሚው የሴቶች፣ ወጣቶች እና ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ቡድን መሪ አቶ ምህረት አስጨ በበኩላቸው ተቋሙ የፆታ ጥቃትን ለመከላከልና ወላጆቻቸውን በኤድስ ያጡ ህጻናትን ለመደገፍ ያለውን ጥረት አመላክተው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ፆታዊ ጥቃት እና የኤድስ ቀንን በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብሮች ሱሉሉታ በሚገኘው የስልጠና ማዕከል ውስጥ አክብረዋል፡፡