African Leadership Excellence Academy
2.3K subscribers
2.49K photos
96 videos
6 files
116 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
Research Validation workshop at AFLEX
AFLEX holds a workshop on the Pan African Now: Pan Africanism for a changing world
Today, January 20, 2023, the African Leadership Excellence Academy, AFLEX, holds a discussion on Pan Africanism Now: Pan Africanism for a changing world here at Skylight Hotel Addis Ababa.
According to Dr.Shimles, the purpose of the workshop is research output validation.
Dr. Shimles Offered the Source, The argument, the background, significance, objectives, research questions, and what can be done as part of the broadsheet.
After the presentation, a discussion was apprehended on the topic. Participants outstretched their questions and perceptions and the questions were responded.

Finally, the head of the African Leadership Excellence Academy, Dr. Mehret Debebe, gave an explanation of the presentation given on the topic and told the inputs given by the participants are vital.

The presentation was moderated by professor Brook Hailu Senior Advisor of AFLEX.
በትውውቅ መርሀ ግብሩ ላይ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክ፤ ከመከላከያ፤ ከትምህርት፤ ከኢንዱስትሪ፤ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ፤ ከግብርና ሚ/ር መስሪያ ቤቶች፤ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል፤ ከኢትዮ ኢንጂነሪንግ፤ ከስፔስ ሳይንስ፤ ከምድር ባቡር፤ ከፌዴራል ፖሊስ እና ሌሎችም ተቋማት የመጡ ተሳታፊዎች የተካፈሉ ሲሆን ሱሉሉታ የሚገኘውን የአካዳሚውን የስልጠና ማዕከልም ጎብኝተዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከሜሊንዳ እና ቢልጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን ለሚሰጠው የሴቶች አመራር ልማት ስልጠና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ ግብር ተከናወነ፡፡ ሰልጣኞችም የእርስ በእርስ ትውውቅ አድርገዋል፡፡
የትውውቅ መርሀ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የአካዳሚው የፕሮግራም ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ እንደተናገሩት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እንደ አዲስ በህግ ከተቋቋመ ጀምሮ በስልጠና እና በምርምር የሰራቸውን ስራዎች የገለፁ ሲሆን የከፍተኛ አመራር ስልጠናን በመስጠት ላይ እንደሆነና ለፖሊሲ አውጭውና ለስልጠና ፕሮግራሙ ግብዓት የሚውሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የስልጠናውን መስፈርት አሟልተው ከተለያዩ ተቋማት የመጡ ሴት የስልጠና ተሳታፊዎችን አቅም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አካዳሚው የራሱን ሚና እንደሚጫወትና ስልጠናውን ተከታትለው በቁርጠኝነት የሚያጠናቅቁ ተሳታፊዎችም በሀገር ግንባታ ውስጥ የራሳቸውን የአመራር ድርሻ እንዲያበረክቱ ድጋፍና እገዛ እንደሚደረግና ሰልጣኞችም ስልጠናውን በተገቢው መንገድ እንዲከታተሉና ለውጤት እንዲበቁ ም/ል ርዕሰ አካዳሚዋ በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ ገልፀዋል፡፡
የሴቶች አመራር ልማት ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ መስፍን በሀይሉ የፕሮጀክቱን ዓላማ በስፋት የገለፁ ሲሆን ሰልጣኞች ወደ ፊት ስለሚሰለጥኑባቸው ርዕሰ ጉዳዮችና ከስልጠናው የሚጠበቀውን ውጤትም አብራርተዋል፡ ስልታዊ አስተሳሰብን ማበልፀግ፤ ችግርን ተረድቶ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መፍታት፤ ውጤታማ የተግባቦት ክህሎትን ማሳደግ፤ የቡድን ስራ ግንባታና የባለድርሻ አካላት ስራ አመራር ከስልጠናው የሚጠበቁ ውጤቶች መሆናቸውንም አቶ መስፍን ጠቅሰዋል፡፡
በኢትዮጵያ የሚገኙ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎበኙ፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡