African Leadership Excellence Academy
2.29K subscribers
2.48K photos
96 videos
6 files
116 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
አካዳሚው የምስጋና መርሃ ግብር አከናወነ
በሃገር አቀፍ ደረጃ የተላለፈውን የምስጋና መርሃ ግብር ጥሪን ተከትሎ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራሮችና ሰራተኞች የምስጋና መርሃ ግብር አከናውነዋል፡፡
በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) ማመስገን ለሚደረግልንና ለተደረገልን የምንሰጠው ምላሽ መሆኑን በማንሳት በእኛ ጉብዝና ብቻ ሳይሆን በፈጣሪ ድጋፍ ጭምር ለዚህ ደርሰናል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ከጨለማ ይልቅ ብርሃንን መምረጥ መልካም ጎኑ የሚጎላ በመሆኑ ሃገራችንና ህዝባችንን የጠበቀ ፈጣሪን በማመስገን በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ምስጋና እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡
የአካዳሚው ፕሮግራም ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ህይወት አለማየሁ በበኩላቸው መመሰጋገን እንደ ባህል መወሰድ አለበት ለሃገር የለፉ፣ የደከሙና ውጤታማ የሆኑ አመራሮችን ማመስገን ተገቢ ነው ብለዋል፡፡
የግል ዝና እና ሃብታቸውን ትተው ሃገር በማገልገል ላይ ያሉ አመራሮችን ማመስገን ለላቀ ውጤት ስለሚያበቃ ባህሉ ሊጎለብት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ሰራተኞች ለበላይ ኃላፊዎቻቸው እንዲሁም ኃላፊዎች ለሰራተኞች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ሃገራችንን በመወከል ከፍተኛ ድል ያስመሰገቡ አትሌቶቻችንንም የማመስገን ስነስርዓትም ተካሂዷል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት (ECSOC) በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ፡፡
ውይይቱን የመሩት የአካዳሚው የፕሮግራም ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ሕይወት አለማየሁ አካዳሚው እንደ አዲስ ከተቋቋመ ጀምሮ ያከናወናቸውን ተግባራትና የጀመረውን ተቋማዊ ሪፎርም ሲጨርስ ሊሰሩ ስለታሰቡ ስራዎች ያብራሩ ሲሆን ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በጋራ በመስራት በዘርፉ ያለውን የአመራር የክህሎትና የዕውቀት ክፍተት በመሙላት ብቁ አመራር ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ውስጥ አካዳሚው የድርሻውን ለመወጣት እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የተወጣጡ አመራሮችና ባለሙያዎች በበኩላቸው አካዳሚው እያከናወናቸው ያሉ ስራዎችን በማድነቅ ተቋሙ የሰነቀው ራዕይ ከሃገራችን አልፎ በአፍሪካ ደረጃ ትልቅ ተቋም መሆኑን የሚያመላክት በመሆኑ በቀጣይ ከአካዳሚው ጋር በመስራት የዘርፉን አመራር አቅም ማብቃት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡
አብሮ ለመስራት በሚቻልባቸው ዝርዝር ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በቀጣይ በወርክሾፕና በስልጠና ግንኙነቱን ወደ ላቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት ማሳደግ እንደሚገባ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት በስሩ 3700 የሚሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ይገኛሉ፡፡
የደቡብ ሱዳን የደህንነትና የሲቪል ሹማምንት ከፍተኛ ልዑክ ከአካዳሚው ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጉት እንዳለው ገለፀ
የደቡብ ሱዳን የደህንነትና የሲቪል ልዑክ አባላት እና የኢትዮጵያ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮች በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን የደቡብ ሱዳን ልዑክ አባላት የአካዳሚውን መሰረተ ልማት ከጎበኙ በኃላ እንደተናገሩት ከአካዳሚው ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡
የአካዳሚው የስራ አመራር ኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሠ (ዶ/ር) የልዑካን ቡድኑ አባላት ወደ አካዳሚው በመምጣታቸው ደስተኛ እንደሆኑና ተቋሙ አፍሪካዊ ተልዕኮን ያነገበ በመሆኑ ከአፍሪካ አገራት ጋር አብሮ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን በመግለፅ በቀጣይ በኢትዮጵያዊና በአፍሪካዊ መስተንግዶ የሚቀበሏቸው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት በበኩላቸው አካዳሚው እያከናወናቸው ያሉ ስራዎችን በማድነቅ በቀጣይ በተለይም በስልጠና ስራዎች አብሮ ለመስራት ከፍተኛ ፍላጉት እንዳላቸውና በቅርቡ የቴክኒክ ልዑክ በመላክ በቀጣይ ሊሰሩ ስለሚገቡ ስራዎች ዝርዝር ውይይት እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡
የኡጋንዳ የልዑካን ቡድን በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጉብኝት አደረገ፡፡
በኡጋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ኦኬሎ ኦሪየም የተመራው ልዑክ ነሐሴ 15 ቀን 2014 ዓ.ም በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በመገኘት የስልጠና ማዕከሉን ጎብኝቷል፡፡
የኡጋንዳ የምድር ኃይል ዋና አዛዥና የፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ የልዩ ዘመቻ ከፍተኛ አማካሪ ሌተናል ጀነራል ሙሆዚ ኪኑሩጋባን ጨምሮ ሌሎች የደኅንነትና ወታደራዊ ከፍተኛ አመራሮችን ያካተተው የልዑካን ቡድን ሱሉልታ በሚገኘው የአካዳሚው የስልጠና ማዕከል ሲደርስ አቀባበል ያደረጉለት የአካዳሚው ስራ አመራር ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) እና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ናቸው፡፡
ምክትል ርዕሰ አካዳሚው ለልዑካን ቡድኑ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ ስለ አካዳሚው ተልዕኮና ተግባራት ሰፊ ገለፃ አድርገዋል፡፡ ተቋሙ የአፍሪካውያንን የመሪዎች ሚና ለማሳደግና ለማበልፀግ እንደሚሰራና ይህንን ግቡን ለማሳካት ሰፊ የሪፎርም ስራ ላይ እንደሚገኝም ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ መሪ የኡጋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ኦኬሎ ኦሪየም በበኩላቸው አካዳሚው የአፍሪካውያንን የአመራር ክፍተት ለመሙላትና የመሪዎችን አቅም በስልጠና ለመገንባት የሚያደርገውን ጥረት አድንቀው የኡጋንዳ መሪዎችን በተቁሙ ውስጥ ለማሰልጠን ፍላጎት እንዳለቸው ተናግረዋል፡፡
ሌሎች የልዑካን ቡድኑ አባላትም በአካዳሚው ውስጥ ባዩት የስልጠና ፋሲሊቲ እና በተደረገላቸው አቀባበል ደስተኛ መሆናቸውን በመግለፅ በቀጣይ ከአካዳሚው ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
አካዳሚው ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
የስልጠናውን ሂዴት በተመለከተ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ ሃገር የምትለወጠው በስራ እንደሆነ እና ስራ ደግሞ የሚመራው በክህሎት መሆኑን በማንሳት በቆይታቸው ስኬታማ ጊዜን እንደሚያሳልፉ እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል በበኩላቸው አካዳሚው የስልጠና ፍላጎት ጥያቄያቸውን ተቀብሎ ስልጠናውን ስላመቻቸ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በተሟላ የስልጠና ማዕከል ስልጠና መውሰዳቸው ለቀጣይ ተልዕኳቸው እንደሚያግዛቸው ገልፀዋል፡፡