የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ማልታ ሀገር ከሚገኝ ሜዲትራኔያን አካዳሚ ኦፍ ዲፐሎማቲክ ስተዲስ (The Mediterranean Academy of Diplomatic Studies at the University of Malta) ጋር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡
የጋራ ስምምነቱ ዓላማ ሁለቱ ተቋማት በትብብር እንዲሰሩ የሚያስችል ሲሆን በተለይም በጥናትና ምርምር ተግባራት፤ በስልጠና ፕሮግራሞች፤ በጥናት ሰነዶች ልውውጥ እና በባለሙያዎች ስልጠና ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡
በጋራ መግባቢያ ስምምነቱ ላይ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) እና የማልታ ዩኒቨርስቲ ዲፕሎማቲክ አካዳሚ ዳይሬክተር prof. Stefen Calleya ተፈራርመው የስምምነት መርሀ ግብሩ ተጠናቋል፡፡
የጋራ ስምምነቱ ዓላማ ሁለቱ ተቋማት በትብብር እንዲሰሩ የሚያስችል ሲሆን በተለይም በጥናትና ምርምር ተግባራት፤ በስልጠና ፕሮግራሞች፤ በጥናት ሰነዶች ልውውጥ እና በባለሙያዎች ስልጠና ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡
በጋራ መግባቢያ ስምምነቱ ላይ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) እና የማልታ ዩኒቨርስቲ ዲፕሎማቲክ አካዳሚ ዳይሬክተር prof. Stefen Calleya ተፈራርመው የስምምነት መርሀ ግብሩ ተጠናቋል፡፡
አካዳሚው በአቅመ ደካሞች ቤት ዕድሳት፤ በአረንጓደ አሻራ መርሃ ግብር እንዲሁም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረግ ተግባራትን አጠንክሮ መቀጠሉ ተገለፀ
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጨምሮ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤትና ተጠሪ ተቋማት በሻሸመኔ ከተማ 35 ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት መርሃ ግብር አስጀምረዋል፡፡
ከተቋማቱ የተወጣጡ አመራሮችና ሰራተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጋራ በመሆን በምዕራብ አርሲ ዞን ሲራሮ ወረዳ በአረንጓደ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡
በዞኑ ሁለት ወረዳዎች 11ሺህ ለሚሆኑ ለዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍል ተማሪዎች የ7 ሚሊዮን ብር የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍም ተደርጓል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጨምሮ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤትና ተጠሪ ተቋማት በሻሸመኔ ከተማ 35 ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የቤት ዕድሳት መርሃ ግብር አስጀምረዋል፡፡
ከተቋማቱ የተወጣጡ አመራሮችና ሰራተኞች ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጋራ በመሆን በምዕራብ አርሲ ዞን ሲራሮ ወረዳ በአረንጓደ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡
በዞኑ ሁለት ወረዳዎች 11ሺህ ለሚሆኑ ለዝቅተኛ የህብረተሰብ ክፍል ተማሪዎች የ7 ሚሊዮን ብር የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍም ተደርጓል፡፡
አካዳሚው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አከናወነ
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሱሉልታ ኢፋ ቦሩ ለገ ደቦ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ጊቢ ውስጥ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አከናውኗል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ተቋሙ አገራዊ አጀንዳዎችን ለመፈፀም የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ አስታውሰው በት/ቤት ውስጥ ችግኝ መተከሉ የነገ ሃገር ተረካቢዎችን ተስፋ እንደሚያለመልም ገልፀዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ም/ከንቲባ አቶ አቡ ብርኪ በበኩላቸው አካዳሚው ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመሆን የሚሰራቸውን ስራዎች አድንቀው የችግኝ ተከላው መርሃ ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ የተያዘውን የአረንጓዴ አሻራ ማሳረፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ፋይዳ አብራርተዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የአካዳሚው አመራርና ሰራተኞች እንዲሁም የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር አመራሮችና የትምህርት ቤቱ ሃላፊዎች ተሳትፈውበታል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሱሉልታ ኢፋ ቦሩ ለገ ደቦ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ጊቢ ውስጥ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አከናውኗል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) እንደተናገሩት ተቋሙ አገራዊ አጀንዳዎችን ለመፈፀም የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ አስታውሰው በት/ቤት ውስጥ ችግኝ መተከሉ የነገ ሃገር ተረካቢዎችን ተስፋ እንደሚያለመልም ገልፀዋል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ም/ከንቲባ አቶ አቡ ብርኪ በበኩላቸው አካዳሚው ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመሆን የሚሰራቸውን ስራዎች አድንቀው የችግኝ ተከላው መርሃ ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ የተያዘውን የአረንጓዴ አሻራ ማሳረፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ፋይዳ አብራርተዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የአካዳሚው አመራርና ሰራተኞች እንዲሁም የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር አመራሮችና የትምህርት ቤቱ ሃላፊዎች ተሳትፈውበታል፡፡
አካዳሚው የምስጋና መርሃ ግብር አከናወነ
በሃገር አቀፍ ደረጃ የተላለፈውን የምስጋና መርሃ ግብር ጥሪን ተከትሎ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራሮችና ሰራተኞች የምስጋና መርሃ ግብር አከናውነዋል፡፡
በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) ማመስገን ለሚደረግልንና ለተደረገልን የምንሰጠው ምላሽ መሆኑን በማንሳት በእኛ ጉብዝና ብቻ ሳይሆን በፈጣሪ ድጋፍ ጭምር ለዚህ ደርሰናል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ከጨለማ ይልቅ ብርሃንን መምረጥ መልካም ጎኑ የሚጎላ በመሆኑ ሃገራችንና ህዝባችንን የጠበቀ ፈጣሪን በማመስገን በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ምስጋና እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡
የአካዳሚው ፕሮግራም ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ህይወት አለማየሁ በበኩላቸው መመሰጋገን እንደ ባህል መወሰድ አለበት ለሃገር የለፉ፣ የደከሙና ውጤታማ የሆኑ አመራሮችን ማመስገን ተገቢ ነው ብለዋል፡፡
የግል ዝና እና ሃብታቸውን ትተው ሃገር በማገልገል ላይ ያሉ አመራሮችን ማመስገን ለላቀ ውጤት ስለሚያበቃ ባህሉ ሊጎለብት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ሰራተኞች ለበላይ ኃላፊዎቻቸው እንዲሁም ኃላፊዎች ለሰራተኞች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ሃገራችንን በመወከል ከፍተኛ ድል ያስመሰገቡ አትሌቶቻችንንም የማመስገን ስነስርዓትም ተካሂዷል፡፡
በሃገር አቀፍ ደረጃ የተላለፈውን የምስጋና መርሃ ግብር ጥሪን ተከትሎ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራሮችና ሰራተኞች የምስጋና መርሃ ግብር አከናውነዋል፡፡
በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) ማመስገን ለሚደረግልንና ለተደረገልን የምንሰጠው ምላሽ መሆኑን በማንሳት በእኛ ጉብዝና ብቻ ሳይሆን በፈጣሪ ድጋፍ ጭምር ለዚህ ደርሰናል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ከጨለማ ይልቅ ብርሃንን መምረጥ መልካም ጎኑ የሚጎላ በመሆኑ ሃገራችንና ህዝባችንን የጠበቀ ፈጣሪን በማመስገን በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችም ምስጋና እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡
የአካዳሚው ፕሮግራም ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ ህይወት አለማየሁ በበኩላቸው መመሰጋገን እንደ ባህል መወሰድ አለበት ለሃገር የለፉ፣ የደከሙና ውጤታማ የሆኑ አመራሮችን ማመስገን ተገቢ ነው ብለዋል፡፡
የግል ዝና እና ሃብታቸውን ትተው ሃገር በማገልገል ላይ ያሉ አመራሮችን ማመስገን ለላቀ ውጤት ስለሚያበቃ ባህሉ ሊጎለብት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ሰራተኞች ለበላይ ኃላፊዎቻቸው እንዲሁም ኃላፊዎች ለሰራተኞች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ሃገራችንን በመወከል ከፍተኛ ድል ያስመሰገቡ አትሌቶቻችንንም የማመስገን ስነስርዓትም ተካሂዷል፡፡