የመንግስት ግዥ እና ንብረት ባለስልጣን በአፍሌክስ የአመራር ልማት ስልጠና መውሰድ ጀመረ
ሱሉልታ መጋቢት 11/2017 (አፍሌክስ) - የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን አመራሮች ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሌክስ የአመራር ልማት ማዕከል የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል።
መርሃ ግብሩ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን የቡድን መሪዎች፣ ስራ አስፈፃሚዎችና የጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችን ጨምሮ 30 ተሳታፊዎችን ይዟል።
ጅማሮውን ዛሬ ያደረገውና ለተከታታይ 4 ቀናት የሚቆየው ስልጠናው እንደ ትራንስፎርሜሽን እና አገልጋይ አመራር፣ የለውጥ አስተዳደርና የሰራተኞች ልማትን የመሳሰሉ ለተቋም አመራር ወሳኝ የሆኑ ርዕሶችን አካቷል።
የስልጠናው ርዕሶች የተመረጡት ተሳታፊዎች በተቋማቸው ውስጥ ውጤታማ አመራር እንዲኖራቸው አስፈላጊ የሆኑት ክህሎቶችን ለማስታጠቅ ታስቦ እንደሆነ ተገልጿል።
ስልጠናው መሪዎቹ በስራ ላይ የሚገጥሙ ውስብስብ ፈተናዎችን በመፈተሽ እና አወንታዊ የስራ አካባቢን በመፍጠር ውጤታማ የለውጥ አመራርን መተግበር እንዲችሉ ማገዝን አላማው አድርጓል።
የአመራር መርሆዎችን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያስችሉ ገለጻዎች እና ውይይቶች የስልጠናው አካላት ናቸው።
ሱሉልታ መጋቢት 11/2017 (አፍሌክስ) - የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን አመራሮች ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሌክስ የአመራር ልማት ማዕከል የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና መውሰድ ጀምረዋል።
መርሃ ግብሩ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን የቡድን መሪዎች፣ ስራ አስፈፃሚዎችና የጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችን ጨምሮ 30 ተሳታፊዎችን ይዟል።
ጅማሮውን ዛሬ ያደረገውና ለተከታታይ 4 ቀናት የሚቆየው ስልጠናው እንደ ትራንስፎርሜሽን እና አገልጋይ አመራር፣ የለውጥ አስተዳደርና የሰራተኞች ልማትን የመሳሰሉ ለተቋም አመራር ወሳኝ የሆኑ ርዕሶችን አካቷል።
የስልጠናው ርዕሶች የተመረጡት ተሳታፊዎች በተቋማቸው ውስጥ ውጤታማ አመራር እንዲኖራቸው አስፈላጊ የሆኑት ክህሎቶችን ለማስታጠቅ ታስቦ እንደሆነ ተገልጿል።
ስልጠናው መሪዎቹ በስራ ላይ የሚገጥሙ ውስብስብ ፈተናዎችን በመፈተሽ እና አወንታዊ የስራ አካባቢን በመፍጠር ውጤታማ የለውጥ አመራርን መተግበር እንዲችሉ ማገዝን አላማው አድርጓል።
የአመራር መርሆዎችን ግንዛቤ ለማሳደግ የሚያስችሉ ገለጻዎች እና ውይይቶች የስልጠናው አካላት ናቸው።
የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር በአፍሌክስ የፈተና ንድፍ በማዘጋጀት ላይ ነው
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እያካሄደ ያለውን ሪፎርም ተከትሎ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ለራሱና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች የሙያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ንድፍ በአፍሌክስ በማዘጋጀት ላይ ይገኛል።
ንድፉ በዋናነት እቅድ፣ የአየር ንብረት፣ ፖሊሲ እና ስታቲስቲክስ ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን፡ የማውጣት ሂደቱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ ከፍተኛ ባለሞያዎች፣ መካከለኛ አመራሮች እና አማካሪዎች የተሳተፉበት ነው።
ከሰኞ ጀምሮ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አዘጋጅነት እየተከወነ ያለው የማዘጋጀት ሂደት በተለያዩ ባለሞያዎች፣ በተለያዩ ዙሮች የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።
ዝግጅቱ ንድፉን ማጠናቀቅ፣ ማስገምገም፣ የፈተና ረቂቅ ማዘጋጀት .....እያለ በርካታ ሂደቶችን የሚያልፍ ይሆናል።
አፍሌክስ ከተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት ጋር በጋራ በመስራት ተቋማቱ ስልጠና፣ ኮንፈረንስና የብቃት ምዘና ስርዐት ማዘጋጀትን ጨምሮ የተለያዩ የአመራር ብቃትን እና የስራ አፈጻጸማቸውን ለማሳደግ የሚረዱ ተግባራትን እንዲከውኑ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ላይ ይገኛል።
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እያካሄደ ያለውን ሪፎርም ተከትሎ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ለራሱና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች የሙያ ብቃት መመዘኛ ፈተና ንድፍ በአፍሌክስ በማዘጋጀት ላይ ይገኛል።
ንድፉ በዋናነት እቅድ፣ የአየር ንብረት፣ ፖሊሲ እና ስታቲስቲክስ ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን፡ የማውጣት ሂደቱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ ከፍተኛ ባለሞያዎች፣ መካከለኛ አመራሮች እና አማካሪዎች የተሳተፉበት ነው።
ከሰኞ ጀምሮ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አዘጋጅነት እየተከወነ ያለው የማዘጋጀት ሂደት በተለያዩ ባለሞያዎች፣ በተለያዩ ዙሮች የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል።
ዝግጅቱ ንድፉን ማጠናቀቅ፣ ማስገምገም፣ የፈተና ረቂቅ ማዘጋጀት .....እያለ በርካታ ሂደቶችን የሚያልፍ ይሆናል።
አፍሌክስ ከተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት ጋር በጋራ በመስራት ተቋማቱ ስልጠና፣ ኮንፈረንስና የብቃት ምዘና ስርዐት ማዘጋጀትን ጨምሮ የተለያዩ የአመራር ብቃትን እና የስራ አፈጻጸማቸውን ለማሳደግ የሚረዱ ተግባራትን እንዲከውኑ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ላይ ይገኛል።
ተለዋዋጭ በሆነው አለም አፍሌክስን ተወዳዳሪ ለማድረግ ተቋሙን ከአዳዲስ ሃሳቦች እና ግኝቶች ጋር ማስተሳሰር ይገባል ተባለ።
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - በአፍሌክስ የአስተዳደር እና ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ተቋማዊ ልህቀትን በተመለከተ ስልጠና ሲሰጡ እንደጠቀሱት፤ ብቁ እና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት የላቀ አፈጻጸም ያስፈልጋል ብለዋል። በስልጠናው ላይ በተነሱ ሃሳቦች ዙሪያም ውይይቶች ተደርገዋል።
በስልጠናው ላይ የተነሱ ሃሳቦችን ከአፍሌክስ ተልዕኮ ጋር በማስተሳሰር ተቋሙን ወደስኬት ማድረስ በሚቻልባቸው ጉዳዮች በውይይቶቹ ተዳሰዋል።
ውይይቶቹ የቀሪውን በጀት ዓመት ወሳኝ የትኩረት አቅጣጫዎችን በመለየት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የአመራር ልማትን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና የአካዳሚውን ተልዕኮ ከግብ በማድረስ ወደ ስኬት መጓዝ ላይ ትኩረት አድርገዋል።
ተለዋዋጭ በሆነው አለም አፍሌክስን ተወዳዳሪ ለማድረግ ከአዳዲስ ሃሳቦች እና ግኝቶች ጋር ተቋሙን ማስተሳሰር እንደሚገባ በውውይቶቹ ላይ ተጠቁሟል።
የአፍሌክስ አመራር እና ሰራተኞች እየወሰዱ ያሉት ስልጠና በመድረክ ከሚቀርቡ ማብራሪያዎች በተጨማሪ ተሳታፊው ሃሳብ የሚያነሳባቸውን አሳታፊ ውይይቶች ያካተተ ነው።
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - በአፍሌክስ የአስተዳደር እና ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዚደንት ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ተቋማዊ ልህቀትን በተመለከተ ስልጠና ሲሰጡ እንደጠቀሱት፤ ብቁ እና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት የላቀ አፈጻጸም ያስፈልጋል ብለዋል። በስልጠናው ላይ በተነሱ ሃሳቦች ዙሪያም ውይይቶች ተደርገዋል።
በስልጠናው ላይ የተነሱ ሃሳቦችን ከአፍሌክስ ተልዕኮ ጋር በማስተሳሰር ተቋሙን ወደስኬት ማድረስ በሚቻልባቸው ጉዳዮች በውይይቶቹ ተዳሰዋል።
ውይይቶቹ የቀሪውን በጀት ዓመት ወሳኝ የትኩረት አቅጣጫዎችን በመለየት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የአመራር ልማትን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና የአካዳሚውን ተልዕኮ ከግብ በማድረስ ወደ ስኬት መጓዝ ላይ ትኩረት አድርገዋል።
ተለዋዋጭ በሆነው አለም አፍሌክስን ተወዳዳሪ ለማድረግ ከአዳዲስ ሃሳቦች እና ግኝቶች ጋር ተቋሙን ማስተሳሰር እንደሚገባ በውውይቶቹ ላይ ተጠቁሟል።
የአፍሌክስ አመራር እና ሰራተኞች እየወሰዱ ያሉት ስልጠና በመድረክ ከሚቀርቡ ማብራሪያዎች በተጨማሪ ተሳታፊው ሃሳብ የሚያነሳባቸውን አሳታፊ ውይይቶች ያካተተ ነው።
"ተቀባይነት ማጣት ለሰነፍ ተስፋ መቁረጫ፡ ለብርቱ ደግሞ የቁጭት እና የብርታት ምንጭ ነው!" ዛዲግ አብርሃ፡ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
የአፍሌክስ ስልጠና 5ተኛ ቀን ውሎ
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - ዛሬ 5ተኛ ቀኑን ባሳቆጠረው ስልጠና አቶ ዛዲግ አብርሃ አትችልም ተብሎ ተቀባይነት ማጣትን ወደ ትልቅ እድል መቀየር ይቻላል ሲሉ ተናገሩ።
ተስፋ ያለመቁረጥን እና የሁለተኛ እድልን ላይ ትኩረት ሰጥተው በሰፊው የዳሰሱት አቶ ዛዲግ፡ በአለማችን በተደጋጋሚ ተቀባይነት አጥተው ተስፋ ባለመቁረጥ ታትረው ከስኬት የደረሱ ግለሰቦችን፤ ተቋማትን እና ሀገራትን እንደምሳሌ በማንሳት ተቀባይነት ማጣት ወድቆ መቅረት አለመሆኑን አስረድተዋል።
በንግግራቸው "ተቀባይነት ማጣት ለሰነፍ ተስፋ መቁረጫ፡ ለብርቱ ደግሞ የቁጭት እና የብርታት ምንጭ ነው!" ብለዋል።
"አፍሌክስ ሁለተኛ እድል ያገኘ ተቋም ነው!" ብለው፡ "ይህንን ሁለተኛ እድል ተጠቅሞ አካዳሚው ያነገበውን ታላቅ ራዕይ ከግብ በማድረስ ታላቅ አፍሪካዊ ተቋም ለማድረግ የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል" ሲሉ አሳስበዋል።
"ኢትዮጵያ የአፍሪካን መሪዎች የማሰልጠን አኩሪ ታሪኳን በአፍሌክስ አጠናክራ እንድታስቀጥል እኛ ሃላፊነት አለብን!" ብለዋል።
የአፍሌክስ ስልጠና 5ተኛ ቀን ውሎ
ሱሉልታ መጋቢት 13/2017 (አፍሌክስ) - ዛሬ 5ተኛ ቀኑን ባሳቆጠረው ስልጠና አቶ ዛዲግ አብርሃ አትችልም ተብሎ ተቀባይነት ማጣትን ወደ ትልቅ እድል መቀየር ይቻላል ሲሉ ተናገሩ።
ተስፋ ያለመቁረጥን እና የሁለተኛ እድልን ላይ ትኩረት ሰጥተው በሰፊው የዳሰሱት አቶ ዛዲግ፡ በአለማችን በተደጋጋሚ ተቀባይነት አጥተው ተስፋ ባለመቁረጥ ታትረው ከስኬት የደረሱ ግለሰቦችን፤ ተቋማትን እና ሀገራትን እንደምሳሌ በማንሳት ተቀባይነት ማጣት ወድቆ መቅረት አለመሆኑን አስረድተዋል።
በንግግራቸው "ተቀባይነት ማጣት ለሰነፍ ተስፋ መቁረጫ፡ ለብርቱ ደግሞ የቁጭት እና የብርታት ምንጭ ነው!" ብለዋል።
"አፍሌክስ ሁለተኛ እድል ያገኘ ተቋም ነው!" ብለው፡ "ይህንን ሁለተኛ እድል ተጠቅሞ አካዳሚው ያነገበውን ታላቅ ራዕይ ከግብ በማድረስ ታላቅ አፍሪካዊ ተቋም ለማድረግ የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል" ሲሉ አሳስበዋል።
"ኢትዮጵያ የአፍሪካን መሪዎች የማሰልጠን አኩሪ ታሪኳን በአፍሌክስ አጠናክራ እንድታስቀጥል እኛ ሃላፊነት አለብን!" ብለዋል።
"የተቋማት ግንባታ ጊዜ የሚወስድ ተግባር በመሆኑ ስራውን ዛሬ መጀመር አለብን!" ዛዲግ አብርሃ፣ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
የአፍሌክስ መለወጥ የግድ ነው ተባለ
ሱሉልታ መጋቢት 14/2017 (አፍሌክስ) -ለአካዳሚው አመራር እና ሰራተኞች ስልጠና በመስጠት ላይ የሚገኙት የአካዳሚው ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለውጥ ለአፍሌክስ ምርጫ ሳይሆን ብልጫ ነው ብለዋል።
የሃገራዊ ሪፎርሙ አካል መሆን፣ የአሰራር ስርዐቱን ማሻሻል፣ ድርጅታዊ ቁመናውን ማሳደግ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም ማድረግ እና መሰረታዊ ከሆነው የአመራር ልማት ለውጥ ጋር መጓዝ የአካዳሚው የለውጥ ጉዞ ዋነኛ ኢላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል።
በተቋማት የለውጥ ሒደት ውስጥ ተግዳሮቶችን ተቋቁመውና አሸንፈው የአሻጋሪነት ሚና የሚወስዱ ተቋማት እንዳሉ ሁሉ፤ በገጠማቸው የህልውና አደጋ ተሸንፈው ህልውናቸውን ያጡ ተቋማት በታሪክ እንደተመዘገቡ ጠቁመው "የአፍሌክስ ስኬት የአመራርና የሰራተኛው ስኬት በመሆኑ፤ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ እንደ ዐይኑ ብሌን ሊጠብቀውና ሊያስቀጥለው ይገባል።" ሲሉ ተናግረዋል።
አያይዘውም "የመጪውን ትውልድ መሪዎች የሚቀርጽ ተቋም ገንብተን ለትውልድ አሻራችንን እናኑር" የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የተቋም ግንባታንና ስልጣኔን ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚሉት አቶ ዛዲግ፤ እውነታውን ከአፍሌክስ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አዛምደው አስቀምጠዋል። "የተቋም ግንባታ ጊዜ የሚወስድ ተግባር በመሆኑ፣ ስራውን ዛሬ መጀመር አለብን!" ብለዋል።
የአፍሌክስ መለወጥ የግድ ነው ተባለ
ሱሉልታ መጋቢት 14/2017 (አፍሌክስ) -ለአካዳሚው አመራር እና ሰራተኞች ስልጠና በመስጠት ላይ የሚገኙት የአካዳሚው ፕሬዚደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ለውጥ ለአፍሌክስ ምርጫ ሳይሆን ብልጫ ነው ብለዋል።
የሃገራዊ ሪፎርሙ አካል መሆን፣ የአሰራር ስርዐቱን ማሻሻል፣ ድርጅታዊ ቁመናውን ማሳደግ፣ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተቋም ማድረግ እና መሰረታዊ ከሆነው የአመራር ልማት ለውጥ ጋር መጓዝ የአካዳሚው የለውጥ ጉዞ ዋነኛ ኢላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል።
በተቋማት የለውጥ ሒደት ውስጥ ተግዳሮቶችን ተቋቁመውና አሸንፈው የአሻጋሪነት ሚና የሚወስዱ ተቋማት እንዳሉ ሁሉ፤ በገጠማቸው የህልውና አደጋ ተሸንፈው ህልውናቸውን ያጡ ተቋማት በታሪክ እንደተመዘገቡ ጠቁመው "የአፍሌክስ ስኬት የአመራርና የሰራተኛው ስኬት በመሆኑ፤ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ እንደ ዐይኑ ብሌን ሊጠብቀውና ሊያስቀጥለው ይገባል።" ሲሉ ተናግረዋል።
አያይዘውም "የመጪውን ትውልድ መሪዎች የሚቀርጽ ተቋም ገንብተን ለትውልድ አሻራችንን እናኑር" የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል።
የተቋም ግንባታንና ስልጣኔን ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚሉት አቶ ዛዲግ፤ እውነታውን ከአፍሌክስ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አዛምደው አስቀምጠዋል። "የተቋም ግንባታ ጊዜ የሚወስድ ተግባር በመሆኑ፣ ስራውን ዛሬ መጀመር አለብን!" ብለዋል።