African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.52K photos
96 videos
6 files
118 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
#UPCOMINGEVENT

WHAT: Signing of Letter of Intent for Cooperation between Africa Leadership Excellence Academy (AFLEX) and Ministry of Culture and Sport

Participant: AFLEX Management and Ministry of Culture and Sport Management team

When: Thursday 2 January 2025 at 2:00 pm

WHERE: Sululuta, AFLEX

#Partnership #LeadershipDevelopmentProgram #Collaboration

#AFLEX

#Ministry_of_Culture_and_Sport
👍5
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የራሳችን ተረቶች የሉንም። ካሉም የሚነግሩን ስለ ዝናብና ስለ ግብርና ነው።

ተረት መናገርን ካለመሰልጠን ጋር አገናኝተነዋል።

ለአገር በቀል ዕውቀቶች የሰጠነው ቦታ አነስተኛ ነው።

ከራሳችን ጋር ተጣልተናል። እንዴት እንታረቅ?

"ከውጭ ለመኮረጅ ብዙ ሞክረናል ብዙም አልተሳካልንም። ወደራሳችን እንመልከት ሃገር በቀል እውቀት ጠቃሚ ነው ይሉናል።" አቶ ዛዲግ አብርሃ :-
👍2
Exciting Publications Ahead!
In the upcoming year, we will have new publications on leadership by experts at our Leadership Excellence Academy. 📗
These publications will feature engaging insights, practical tools, and innovative strategies designed to empower both current and emerging leaders across Africa. 🌍
Our goal is to create resources that inspire and equip leaders to tackle the unique challenges facing our continent!
📘Each publication will:
• delve into key issues
• offer fresh perspectives
• provide actionable solutions
• foster effective leadership &
• drive positive change.
What do you think is the most important thing in leadership?
Please share your opinions in the comments below!
#AFLEX #AFLEXPublications
👍7
Stepping Forward Toward Our Vision in 2025!

As we step into 2025, AFLEX is making bold moves toward realizing its vision of becoming the premier leadership excellence center in Africa! 🚀

This 2025, we are committed to advancing leadership development through a range of transformative initiatives designed to empower our community.

Each initiative is crafted to equip leaders with the knowledge and tools necessary to navigate the unique challenges our continent faces.🌍

At AFLEX, we believe that every step we take brings us closer to cultivating a culture of excellence in leadership!
#AFLEX #Leadership Excellence
👍7
"Be Part of the Experience: Discover Pioneering Technology at AFLEX Conference Hall."
every idea is shared seamlessly
At AFLEX, we are committed to providing a world-class experience with our state-of-the-art conference hall technology. Equipped with the latest audio-visual systems, high-speed internet access, and interactive presentation tools, our facilities are designed to enhance collaboration and engagement. Whether you’re participating in workshops, panel discussions, or keynote presentations, our technology ensures that every voice is heard and every idea is shared seamlessly.
👍3
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
👉የኢትዮጵያ ጀግና ማነው?

👉ጀግኖቻችን የት ነው ያሉት?

👉የጋራ ጀግና መፍጠር ያቃተን ለምንድነው?

👉በብሄር እና በሃይማኖት የታጠሩ ጀግኖችን ሃገራዊ ለማድረግ ምን እንስራ?

👉የሌሎች ሃገራት ጀግኖች መነሻዎችስ ምንድናቸው?

የአፍሌክስ ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ ማብራሪያ
👍10
በባህል፣ በኪነጥበብና ስፖርት ዘርፍ የትውልድ ግንባታ ስራ ይካሄዳል፦ ክብርት ሸዊት ሻንካ
ታህሳስ 24፣ 2017 ዓ.ም (ሱሉልታ-አፍሌክስ) የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሸዊት ሻንካ በስልጠናው የማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የባህል፣ የኪነጥበብና የስፖርት ዘርፍን ተቋማዊ አሰራር በማዘመን የትውልድ ግንባታ የሚካሄድበት ብሎም ሀገራዊ ብለፅግና የሚረጋገጥበት ተቋም ለመፍጠር እንደሚሰራ ገለፁ።
ክብርት ሸዊት ሻንካ በአፍሪካ አመራር ልቀት አካዳሚ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና በቅንጅት፣ በአብሮነት እንዲሁም በትስስር ለመስራት ምቹ ሁኔታን የፈጠረ ከመሆኑም ባሻገር ስልጠናው በተልዕኮ ላይ ምን ውጤት አመጣ የሚለውም እንደሚለካ እና እንደሚመዘን አቅጣጫ ሰጥተዋል።
👍4
አመራሮችን በማብቃት የባህል፣ የስፖርትና የኪነጥበብ ዘርፍ ለሀገር አንድነትና ብልፅግና ያለውን ሚና አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚል መሪ ሀሳብ ሲሰጥ በቆየው ስልጠና የስልጠናው ተሳታፊዎች ከስልጠና በኋላ የሚቆጠር፣ የሚጨበጥ ውጤት ለማምጣት መትጋት እንዳለባቸው ክብርት ሚኒስትሯ አክለው አስገንዝበዋል።
በስልጠናው የተገኙ እውቀቶችን በመጠቀም በተቋም ደረጃ ተግባራዊ በማድረግ የተገልጋዮችን እርካታ ማሳለጥ እንደሚገባ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የኪነጥበብ ስነጥበብና ፈጠራ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ነፊሳ አልማህዲ በበኩላቸው ተናግረዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር መክዩ መሀመድ እንደገለፁት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተስፋ የሚሰጥ፣ ሀይል ያለው፣ ለለውጥ የሚያዘጋጅ እና ተልዕኮዎችን በትክክለኛው መንገድ ለመምራት የሚያስችል ግቡን የመታ ስልጠና መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከስልጠናው የተገኙ ውጤቶችና እና በቀጣይ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዮች በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ከስልጠናው ተሳታፊዎች አስተያየቶች ተሰጥተዋል።
በንድፈ ሀሳብና በተግባር በመደገፍ ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ በቆየው የአመራሮችና የባለሙያዎች ስልጠናው ላይ ተሳታፊዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ከተሰጡ አስተያየቶች መካከል ስልጠናው እቅድን ከተግባር ጋር በማገናኘት ለመስራት ተነሳሽነትን የሚፈጥር፣ ክፍተቶችን በመለየት የተሻለ ውጤት ለማምጣት የሚያስችል፣ ስልጠናው የዕርስ በዕርስ ትውውቅን የሚያጠናክር ስለመሆኑ፤ ስልጠናው በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ስፖርት መደገፉ ለስልጠናው ምቹ ሁኔታ ስለመፍጠሩ፣ የስልጠናው አውዶች ከአሁኑ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተያያዙ ስለመሆናቸው ከተሳታፊዎች የቀረቡ አስተያየቶች ናቸው።
በተጨማሪም ስልጠናው በአይነቱም በይዘቱም ከባለፉት አመታት ለየት ያለ ከመሆኑም ባሻገር ወቅቱንና ጊዜውን የሚመጥን ስልጠና ሲሆን ስልጠናውን መነሻ በማድረግ የተሻለ ስራ ለመስራት እንደሚያስችል፣ ከጠባቂነት ወደ ተነሳሽነትን የሚያሻግር ስልጠና ስለመሆኑ፣ ስልጠናው ለለውጥ መሰረት የሚጥል እና መተጋገዝን፣ ቅንጅታዊ አሰራርን የሚያዳብር እንደሆነም ተመላክቷል።
የባለቤትነት ስሜትን በማጋራት ለተቋማዊ ስኬት የሚሰጥ እንደዚህ አይነት ስልጠና ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባም የስልጠናው ተሳታፊዎች አስተያየታቸውን ከመስጠት አልዘነጉም።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ስልጠና ላይ ስልጠናውን በልዩ ሁኔታ በማስተባበር ሀላፊነት ለተወጡ አስተባባሪዎች የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት በክብርት ሚኒስትሯ ተበርክቶላቸዋል።
👍7
Together we stand, Pan-African and proud,
AFLEX empowers leaders, speaking strong and loud.
With diverse voices, we weave a rich tapestry,
Uniting our strengths, a shared destiny.
In collaboration, we rise to the call,
For a brighter tomorrow, where all can stand tall
👍4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
🔹አንድን ነገር ብቻ ማወቅ አዋቂ አያሰኝም፡፡

🔹ምሉዕ ለመሆን ተነፃፃሪ ዕውቀት ያስፈልጋል፡፡

🔹የሀሳብ ጥራት መሰረቱ ምንድን ነው

🔹ጊዜው ደርሶ የተወለደን ሀሳብ መመከትና ማስቆም ይቻላል ወይ

🔹የአፍሌክስ ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ ማብራሪያ #ክፍል_5👇👇👇👇
👍4
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
ታህሳስ 24/2017 (አፍሌክስ- ሱሉልታ) የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በአመራር አቅም ግንባታ ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ እና የባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ክብርት ሸዊት ሻንካ ሱሉልታ በሚገኘው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተገኝተው ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር እና አፍሌክስ የአመራር ዕውቀትና ክህሎትን በማስፋት ላይ ያተኮሩ የጋራ የሥልጠና፣ የምርምር እና የማማከር ሥራዎችን ወደ ፊት የሚያሳድጉበት እና በአመራር አቅም ግንባታ ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ በስምምነት ፊርማው ወቅት እንደገለጹት፥ ባህል እና ስፖርት ለሀገር ያለውን ጉልህ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሚና ጠቅሰው ስምምነቱ በኢትዮጵያ ባህል እና ስፖርት ላይ ጉልህ የአመራር ለውጥ እንደሚያመጣ እና ዘርፉ ብቃት ባላቸው አመራሮች እንዲመራ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ክብርት ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው፤ ስምምነቱ በዋናነት የሴክተሩን የማስፈፀም አቅም ለማሳደግና፣ የተሻለ ስልጠና ለመስጠት እና የሰለጠነ የሰው ሃይል ለማፍራት የሚያግዝ ነው፡፡
👍8