African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.52K photos
96 videos
6 files
118 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚና ኢጋድ በጋራ ለመስራት ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 16፣ 2017 (አፍሌክስ) የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን በመወከል የአካዳሚው ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ እና የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ወርቅነህ ገበየሁን (ዶ/ር) ወክለው በኢትዮጵያ የኢጋድ ተጠሪ አበባው ቢሆነኝ ፈርመውታል።

በስምምነት ፊርማው ላይ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደገለጹት አካዳሚው ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ትብብር በማድረግ የአመራር ልማት ስራውን ለማስፋት እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው፤ በቀጠናው ሰላም ለማስጠብቅና ሀገራቱን ለማስተሳስር ስምምነቱ ያግዛል ብለዋል።

ፕሬዚደንቱ አያይዘውም ከኢጋድ ጋር የተደረገው ስምምነት በአመራር ልማት፤ በጋራ ጥናትና ምርምር ፤ ዓለምአቀፍ ጉባኤዎችንና ወርክሾፖችን በጋራ ለማካሄድ፤ እንዲሁም በተለያዩ የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት ያለመ እንደሆነ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የኢጋድ ተጠሪ አበባው ቢሆነኝ ኢጋድ በቀጠናው ሰላም ለማስፈን፣ በጤና፣በማህበራዊ አገልግሎት ፣በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና በአመራር ላይ የሚሰራውን ስራን በማንሳት የጋራ ስምምነቱ የአመራር እቅም ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

የትብብር ስምምነቱ ከ2025 ጀምሮ ወደ ትግበራው እንደሚገባ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።
👍13
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚና ኢጋድ በጋራ ለመስራት የተፈራረሙትን ስምምነት ፋና ሚዲያ እንዲህ ዘግቦታል፡-
👍9
የአፍሌክስ ፕሬዝደንት አቶ ዛዲግ አብርሃ ከኢጋድ ጋር የትብብር ምምነት በተፈራረሙበት ወቅት ከተናገሩት :-

👉የአፍሌክስ የትብብር አድማስ ኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ ቀንድ፣ አፍሪካ፣ ከዚያም አለም አቀፍ እያለ እየሰፋ የሚሄድ ነው።

👉ከአፍሪካ ህብረት ጋር አብረን መስራት ጀምረናል።

👉ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ከተለያዩ የእስያ ተቋማት ጋር አብሮ ለመስራት ያደረግነው እንቅስቃሴ ውጤት ማምጣት ጀምሯል።

👉አሜሪካ ውስጥ ከሚገኙ በአመራር ልማት ዘርፍ ስመጥር ከሆኑ ተቋማት ጋር አብረን እየሰራን ነው።

👉ከበርካታ የአውሮፓ ተቋማት ጋርም ትብብር ለመፍጠር ጥረት እያደረግን እንገኛለን።

👉ከኢጋድ ጋር ትብብር ለመመስረት ያደርግነው ጥረት ፍሬ አፍርቶ ለስምምነት በመብቃቱ ደስተኞች ነን።

👉ከኢጋድ ጋር አጋርነት ለመፍጠር መስማማታችን ለአፍሌክስም ለኢትዮጵያ መንግስትም ልዩ ትርጉም አለው።

👉ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነጻነት እና እድገት የቀደመ አስተዋጽዖ የነበራት ጥንታዊት ሃገር ናት።

👉ይህ የሃገራችን አስተዋጽዖ በእኛም ትውልድ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።

👉የቀጠናችን የአፍሪካን ቀንድ ውስብስብ ችግሮች ለመፍታት አቅም ያላቸውን መሪዎች ለማፍራት አፍሌክስ በትጋት ይሰራል።
👍10
“የቻይና መንግስት፤ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን የሰው ሀብት ልማት እና የመሰረተ ልማት ግንባታ ለማገዝ ዝግጁ ነው” Guan Zhiyong የCIDAC ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የልዑክ ቡድኑ መሪ

“የቻይና መንግስት ለአካዳሚው ዘርፈ ብዙ ድጋፍ እና እገዛ በማድረግ ላይ ይገኛል” ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) የአፍሌክስ የአስተዳደር እና የቢዝነስ ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ

ታሕሣሥ 16፣ 2017 (አፍሌክስ-ሱሉሉታ)- የቻይና መንግስት የአፍሌክስን የሰው ሀብት ልማት እና የመሰረተ ልማት ግንባታ ለማገዝ ዝግጁ እንደሆነ ተገለጸ።

ይህ የተገለጸው ዛሬ በአካዳሚው የአመራር ልማት ውስጥ በተደረገ ውይይት ላይ ነው። የቻይናን መንግስት ወክለው ከአካዳሚው ጋር ውይይት ያደረጉት ከአራት የቻይና መንግስት ተቋማት የተውጣጡ የልዑክ ቡድን አባላት ናቸው።

ከCIDAC፤ ከChinese Embassy in Ethiopia፤ ከChinese Mission to the African Union እና ከNational Academy of Governance የመጡ ልዑካን ከአፍሌክስ የአስተዳደር እና የቢዝነስ ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።
👍11
በውይይቱ ላይ የCIDAC ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የልዑክ ቡድኑ መሪ ጉዋን ዢዮንግ Guan Zhiyong የቻይና መንግስት፤ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን የሰው ሀብት ልማት እና የመሰረተ ልማት ግንባታ ለማገዝ ዝግጁ እንደሆነ ጠቁመው፤ ለዚህም የሚረዳ የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን እና ወደ ስራ ለመግባት ቅድመ ዝግጅቱ መጠናቀቁን ተናግረዋል።

የልዑክ ቡድኑ መሪ ጉዋን ዢዮንግ Guan Zhiyong አያይዘውም የአካዳሚውን የሰው ሀይል አቅም ለመገንባት በትምህርት እና ስልጠና መስክ እንዲሁም በልምድ ልውውጥ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአፍሌክስ የአስተዳደር እና የቢዝነስ ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው የቻይና መንግስት ለአካዳሚው ዘርፈ ብዙ ድጋፍ እና እገዛ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረው፤ የአካዳሚውን እና የሀገራችንን አመራር አቅም ለመገንባት በርካታ መዋዕለ ንዋይን መድበው እየሰሩ በመሆኑ አመስግነዋል።

ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) አያይዘውም የቻይና መንግስት በብሪክስ ጥላ ስር ለሀገራች እና ለአካዳሚው የሰው ሀብት ልማት እና መሰረተ ልማት ግንባታ ሰፋፊ ስራዎች በመስራቱ ሀገራችን የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ የሚያግዝ እንደሆነም ተናግረዋል።

የልዑክ ቡድኑ በቻይና መንግሰት ቻይና ኤይድ የተሰራውን የአካዳሚውን መሰረተ ልማትም ጎብኝቷል።
👍10
በመጪው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ ለመገንባት የተቀናጀ የኮሚኒኬሽን ሥራ ያስፈልጋል-ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ !

ከወራት በኋላ በአዲስ አበባ በሚካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ ለመገንባት የተቀናጀ የኮሚኒኬሽን ሥራ እንደሚያስፈልግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ በሚሰጠው ስልጠና ላይ ገልፀዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው ይህንን የገለፁት በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለሚሳተፉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነባር ዲፕሎማቶችና በጎ ፍቃደኛ ካዴቶች #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ተገኝተው በውጤታማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ላይ ያተኮረ ስልጠና በሰጡበት ወቅት ነው።

በስልጠናው የተቀናጀ፣ የተደራጀ፣ ስትራቴጅክ እና አጀንዳ ሰጪ የኮሙኒኬሽን ስልትን በመከተል ውጤታማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን እንዲኖር ሁሉም ዜጎች በብሄራዊ ስሜትና አገራዊ ሀላፊነት እንዲሰሩ ሚኒስትር ዴኤታው አበክረው ተናግረዋል።

በመጪው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ኢትዮጵያን በሚገባ ለማስተዋወቅ ምቹ አጋጣሚ መሆኑን ያስታወሱት ሚኒስትር ዴኤታው ሰልጣኞቹ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ በተገቢው በመረዳት በሁሉም ዘርፍ እየታዩ ያሉ እምርታዎችን ለእንግዶቹ በማስገንዘብ አገራዊ ሀላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ገልፀዋል።
👍10
የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ የሚያጠለሹና ብሄራዊ ክብርን ዝቅ የሚያደርጉ ሀሰተኛ መረጃዎችን በሚገባ በመለየት ብሔራዊ ጥቅምን ሊያስጠብቁ የሚችሉ የተግባቦት ስራዎችን መስራት ያስፈልጋል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው
ከዚህ በተጨማሪም አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ መልዕክቶችን በመቅረጽ ተሳታፊዎች ስለኢትዮጵያ በጎ መረጃ ይዘው እንዲመለሱ የሚያስችል የመረጃ ስራ በቅንጅት እንደሚዘጋጅ አሳውቀዋል።

በመድረኩ የተሳተፉ ሰልጣኞች በቀጣይ የአፍሪካ ህብረት በሁሉም የኮሙኒኬሽን ስልቶች አገራቸውን ለማስተዋወቅ ያላቸውን ዝግጁነት ያሳወቁ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ ላነሱት ጥያቄም ሚኒስትር ዴኤታው ምላሽ ሰጥተውበታል።
👍10
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚና ኢጋድ በጋራ ለመስራት የተፈራረሙትን ስምምነት NBC ETHIOPIA እንዲህ ዘግቦታል፡-
👍9
Consultative Discussion between AFLEX and Chinese Delegates

Dec 25, 2025 / ADDIS ABABA / AFLEX / A consultative discussion was held between AFLEX President, Mr. Zadig Abreha, and the Chinese delegates from CIDAC, the China Embassy in Ethiopia, the Chinese Mission to the African Union, and the National Academy of Governance at the AFLEX Head Office.
👍9