የርዕሰ አካዳሚ ጽ/ቤት ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ጫኔ በበኩላቸው የተቋሙን የመቶ ቀናት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ተቋማዊ የማስፈፀም አቅም የሀብት አጠቃቀምና አገለልግሎት አሰጣጥ ፣በቁልፍ የውጤት አመላካቾች ላይ የተመሰረተ የዕቅድ አፈፃፀም ትንተና፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች ላይ ገለፃ አቅርበዋል፡፡
በቀረቡት ገለፃዎች ላይ ከአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው በምክትል ርዕሰ አካዳሚዎቹ ለጥያቄዎቹ ምላሽ ፣ ለአስተያየቶቹም ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያቶች ጥሩ መሆናቸውን የተጠቀሰ ሲሆን እንደግብአትም እንደሚያገለግሉ ተጠቁሟል፡፡
የአካዳሚው የአመራር ልማት ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ሆነው ለተሾሙት ወ/ሮ መሰረት ደስታ የእንኳን ደህና መጡ የመልካም ምኞት መልዕክትም ከአመራሩና ከሰራተኛው ተላልፏል::
በቀረቡት ገለፃዎች ላይ ከአካዳሚው አመራሮችና ሰራተኞች ጥያቄዎችና አስተያየቶች ተነስተው በምክትል ርዕሰ አካዳሚዎቹ ለጥያቄዎቹ ምላሽ ፣ ለአስተያየቶቹም ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያቶች ጥሩ መሆናቸውን የተጠቀሰ ሲሆን እንደግብአትም እንደሚያገለግሉ ተጠቁሟል፡፡
የአካዳሚው የአመራር ልማት ዘርፍ ም/ርዕሰ አካዳሚ ሆነው ለተሾሙት ወ/ሮ መሰረት ደስታ የእንኳን ደህና መጡ የመልካም ምኞት መልዕክትም ከአመራሩና ከሰራተኛው ተላልፏል::
👍22
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ እድገት !!
ክቡር የኢፌዴሪ #ጠቅላይ_ሚኒስትር_ዐቢይ_አሕመድ (ዶ/ር) ስለ #አፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ምን አሉ?
የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ እድገት !! በሚል በቀረበው የከፍተኛ አመራር ስልጠና ላይ የስራ ቦታ፤ ኤርጎኖሚክስ፤ የተቋማት ግንባታና የመፈጸም ባህል በሚለው ገለጻ ስር ስለ ተሻጋሪ ተቋማት ይህን ብለዋል።
እንደ #አፍሌክስ ያሉ ተቋማት ለትውልድ የሚሻገሩ ናቸው። ጥርት ብለው፤ ትልቅ ሆነው፤ ኢትዮጵያን በሚመጥን መልኩ የተሰሩ ናቸው።
ክቡር የኢፌዴሪ #ጠቅላይ_ሚኒስትር_ዐቢይ_አሕመድ (ዶ/ር) ስለ #አፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ምን አሉ?
የህልም ጉልበት፤ ለእመርታዊ እድገት !! በሚል በቀረበው የከፍተኛ አመራር ስልጠና ላይ የስራ ቦታ፤ ኤርጎኖሚክስ፤ የተቋማት ግንባታና የመፈጸም ባህል በሚለው ገለጻ ስር ስለ ተሻጋሪ ተቋማት ይህን ብለዋል።
እንደ #አፍሌክስ ያሉ ተቋማት ለትውልድ የሚሻገሩ ናቸው። ጥርት ብለው፤ ትልቅ ሆነው፤ ኢትዮጵያን በሚመጥን መልኩ የተሰሩ ናቸው።
👍21
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ነው
*****************
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በስብሰባው ላይ የምክር ቤት አባላት ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡
ምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጥያቄዎቹ ላይ የሚሰጡትን የመንግሥትን አቋም በማዳመጥ የድጋፍ ሞሽኑን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
*****************
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በስብሰባው ላይ የምክር ቤት አባላት ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡
ምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጥያቄዎቹ ላይ የሚሰጡትን የመንግሥትን አቋም በማዳመጥ የድጋፍ ሞሽኑን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
👍11
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-
👉በ2016 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፤
👉 ይህ በዓለም አቀፍ ደረጃም ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በዘንድሮው በጀት ዓመትም 8 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል፤
👉 ከዚህም ውስጥ ግብርና 6 ነጥብ 1 በመቶ እንደሚያደግ የሚጠበቅ ሲሆን፤ 30 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል፤
👉 በተለያዩ ዘርፎች ሲከናወኑ የነበሩ ሪፎርሞችን አጠናቀን ሀገራዊ ማንሰራራት የምንጀምርበት ዘመን የመጀመሪያ ምእራፍ ላይ ተገኝተናል፤
👉 በመሆኑም በ2017 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ የምናስመዘግብ ይሆናል፤
👉 ከዚህ አኳያ ከትናንት እሳቤ ወጥተን በጋራ ወደ ነገ መሻገር አለብን፡፡
👉በ2016 በጀት ዓመት በኢትዮጵያ 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት ተመዝግቧል፤
👉 ይህ በዓለም አቀፍ ደረጃም ትልቅ ስኬት ነው፡፡ በዘንድሮው በጀት ዓመትም 8 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል፤
👉 ከዚህም ውስጥ ግብርና 6 ነጥብ 1 በመቶ እንደሚያደግ የሚጠበቅ ሲሆን፤ 30 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል፤
👉 በተለያዩ ዘርፎች ሲከናወኑ የነበሩ ሪፎርሞችን አጠናቀን ሀገራዊ ማንሰራራት የምንጀምርበት ዘመን የመጀመሪያ ምእራፍ ላይ ተገኝተናል፤
👉 በመሆኑም በ2017 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ የምናስመዘግብ ይሆናል፤
👉 ከዚህ አኳያ ከትናንት እሳቤ ወጥተን በጋራ ወደ ነገ መሻገር አለብን፡፡
👍14
በዚህ ዓመት የግብርናው ዘርፍ 6 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጥቅምት 21/2017 (አዲስ ዋልታ) በተያዘው በጀት ዓመት የግብርናው ዘርፍ 6 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እየተካሄደ ባለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል።
በማብራሪያቸውም በ2017 በጀት ዓመት 8 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት ለማስመዝገብ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በግብርናው ዘርፍ ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ገልጸው በዚህ ዓመት በተሰራው ሰፊ ስራ 6 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
ጥቅምት 21/2017 (አዲስ ዋልታ) በተያዘው በጀት ዓመት የግብርናው ዘርፍ 6 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እየተካሄደ ባለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛል።
በማብራሪያቸውም በ2017 በጀት ዓመት 8 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት ለማስመዝገብ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በግብርናው ዘርፍ ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ገልጸው በዚህ ዓመት በተሰራው ሰፊ ስራ 6 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
👍14
በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ 72 ትላልቅ ፋብሪካዎች ሥራ ይጀምራሉ -ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው በጀት ዓመት በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ 72 ትላልቅ ፋብሪካዎች ሥራ እንደሚጀምሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢንዱስትሪ ዘርፍን በሚመለከት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ÷በዘርፉ በተያዘው በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እድገት ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ማኑፋክቸሪንግ ላይ 12 በመቶ እድገት እንደሚጠበቅ ጠቅሰው÷ኮንስትራክሽን ላይ ደግሞ 12 ነጥብ 3 በመቶ ገደማ እድገት ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ኢንዱስትሪ በዚህ ዓመት ከፍተኛ እድገት እንደሚያመጣ የተጠበቀበት ዋናው ምክንያትም ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ታምርት በሚል ንቅናቄ የጀመርነው ሥራ የሚጨበጥ ፍሬ እንደሚያመጣ ስለሚጠበቅ ነው ብለዋል፡፡
እንዲሁም ኢንዱስትሪን ባለፈው ዓመትና በዚህ ዓመት መጀመሪያ በእቅድ ደረጃ እያንዳንዱ ፋብሪካ ምን ችግር እንዳለው፤ ምን ብናግዘው ምርታማነቱ እንደሚያድግ በጋራ ለመስራት ጥረት ተደርጓልም ነው ያሉት፡፡
ከፋብሪካዎች ጋር የሚያያዝ መብራት ከሞላ ጎደል ተፈትቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ከቴሌና ከባንክ ጋር የሚያያዝ ችግርም ከሞላ ጎደል መፈታቱን አንስተዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመትም በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ 72 ትላልቅ ፋብሪካዎች ሥራ ይጀምራሉ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፡፡
ከመሬት አቅርቦትና ከእኛ አሰራር ጋር የሚያያዙ በርካታ ችግሮች መፍትሔ እያገኙ መጥተዋል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ተጨማሪ ስራ የሚያስፈልገውና ኢንዱስትሪዎች ድጋፍ የሚፈልጉት ከጉምሩክ ጋር የሚያያዝ ስራ እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው በጀት ዓመት በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ 72 ትላልቅ ፋብሪካዎች ሥራ እንደሚጀምሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢንዱስትሪ ዘርፍን በሚመለከት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያ÷በዘርፉ በተያዘው በጀት ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እድገት ይጠበቃል ብለዋል፡፡
ማኑፋክቸሪንግ ላይ 12 በመቶ እድገት እንደሚጠበቅ ጠቅሰው÷ኮንስትራክሽን ላይ ደግሞ 12 ነጥብ 3 በመቶ ገደማ እድገት ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ኢንዱስትሪ በዚህ ዓመት ከፍተኛ እድገት እንደሚያመጣ የተጠበቀበት ዋናው ምክንያትም ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ታምርት በሚል ንቅናቄ የጀመርነው ሥራ የሚጨበጥ ፍሬ እንደሚያመጣ ስለሚጠበቅ ነው ብለዋል፡፡
እንዲሁም ኢንዱስትሪን ባለፈው ዓመትና በዚህ ዓመት መጀመሪያ በእቅድ ደረጃ እያንዳንዱ ፋብሪካ ምን ችግር እንዳለው፤ ምን ብናግዘው ምርታማነቱ እንደሚያድግ በጋራ ለመስራት ጥረት ተደርጓልም ነው ያሉት፡፡
ከፋብሪካዎች ጋር የሚያያዝ መብራት ከሞላ ጎደል ተፈትቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ከቴሌና ከባንክ ጋር የሚያያዝ ችግርም ከሞላ ጎደል መፈታቱን አንስተዋል፡፡
በተያዘው በጀት ዓመትም በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ 72 ትላልቅ ፋብሪካዎች ሥራ ይጀምራሉ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፡፡
ከመሬት አቅርቦትና ከእኛ አሰራር ጋር የሚያያዙ በርካታ ችግሮች መፍትሔ እያገኙ መጥተዋል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ተጨማሪ ስራ የሚያስፈልገውና ኢንዱስትሪዎች ድጋፍ የሚፈልጉት ከጉምሩክ ጋር የሚያያዝ ስራ እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
👍14
በተያዘው በጀት ዓመት፡-
👉የኢንዱስትሪ ዘርፉ 12 ነጥብ 8 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል
👉 የሌማት ትሩፋት ምርቶች የ5 ነጥብ 4 በመቶ እድገት ያስመዘግባሉ
👉 በዓመቱ 12 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ይጠበቃል
👉 8 ቢሊዮን የዶሮ እንቁላል ለማግኘት ታቅዷል
👉 218 ሺሕ ቶን ስጋ እና 297 ሺሕ ቶን የማር ምርት ለማምረት እቅድ ተይዟል
👉 በዘንድሮው በጀት ዓመት 8 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል
👉 30 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል
👉72 ትልልቅ ፕሮጀክቶች ስራ ይጀምራሉ
👉 በኢንዱስትሪ ሴክተር 12 ነጥብ 8 በመቶ እድገት ይጠበቃል
👉 በማኑፋክቸሪንግ 12 በመቶ በኮንስትራክሽን ደግሞ 12 ነጥብ 3 በመቶ እድገት ለማስመዝገብ ታቅዷል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ከሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የተወሰደ።
👉የኢንዱስትሪ ዘርፉ 12 ነጥብ 8 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል
👉 የሌማት ትሩፋት ምርቶች የ5 ነጥብ 4 በመቶ እድገት ያስመዘግባሉ
👉 በዓመቱ 12 ቢሊዮን ሊትር የወተት ምርት ይጠበቃል
👉 8 ቢሊዮን የዶሮ እንቁላል ለማግኘት ታቅዷል
👉 218 ሺሕ ቶን ስጋ እና 297 ሺሕ ቶን የማር ምርት ለማምረት እቅድ ተይዟል
👉 በዘንድሮው በጀት ዓመት 8 ነጥብ 4 በመቶ እድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል
👉 30 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በማረስ 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል
👉72 ትልልቅ ፕሮጀክቶች ስራ ይጀምራሉ
👉 በኢንዱስትሪ ሴክተር 12 ነጥብ 8 በመቶ እድገት ይጠበቃል
👉 በማኑፋክቸሪንግ 12 በመቶ በኮንስትራክሽን ደግሞ 12 ነጥብ 3 በመቶ እድገት ለማስመዝገብ ታቅዷል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ከሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የተወሰደ።
👍14
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-
👉 ባለፉት ሦስት ወራት 180 ቢሊየን ብር ገቢ ሰብስበናል፡፡ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 109 ቢሊየን ብር ነበር የተሰበሰበው፡፡ የልዩነቱ ስፋት ለውጥ እንዳለ እና መንገዳችን ትክክል እንደሆነ አመላክች ነው፡፡
👉 በፌደራል መንግሥት 900 ቢሊየን ብር በክልሎች ደግሞ 600 ቢሊየን ብር ገቢ መሠብሰብ ከተቻለ በአጠቃላይ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ገደማ እንሰበስባለን ማት ነው፡፡ ይህም በቂ ባይሆንም ትልቅ እመርታ ነው፡፡
👉 ሪዘርቭን በተመለከተ ደግሞ የብሔራዊ ባንክ ሪዘርቭ 161 በመቶ አድጓል፡፡
👉 የግል ባንኮች ሪዘርቭ 29 በመቶ አድጓል፡፡
👉 ሬሚታንስን በተመለከተም ባለፉት ሦስት ወራት 24 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡
👉 ባንኮች 652 ሚሊየን ዶላር ገዝተው 1 ቢሊየን ገደማ ዶላር ሸጠዋል፡፡
👉 ባለፉት ሦስት ወራት ከኤክስፖርት ምርቶች 1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ለማግኘት አቅደን፤ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር አግኝተናል፡፡ ይህ ትልቅ ስኬት ነው፡፡
👉 ባለፉት ሦስት ወራት 180 ቢሊየን ብር ገቢ ሰብስበናል፡፡ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 109 ቢሊየን ብር ነበር የተሰበሰበው፡፡ የልዩነቱ ስፋት ለውጥ እንዳለ እና መንገዳችን ትክክል እንደሆነ አመላክች ነው፡፡
👉 በፌደራል መንግሥት 900 ቢሊየን ብር በክልሎች ደግሞ 600 ቢሊየን ብር ገቢ መሠብሰብ ከተቻለ በአጠቃላይ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ገደማ እንሰበስባለን ማት ነው፡፡ ይህም በቂ ባይሆንም ትልቅ እመርታ ነው፡፡
👉 ሪዘርቭን በተመለከተ ደግሞ የብሔራዊ ባንክ ሪዘርቭ 161 በመቶ አድጓል፡፡
👉 የግል ባንኮች ሪዘርቭ 29 በመቶ አድጓል፡፡
👉 ሬሚታንስን በተመለከተም ባለፉት ሦስት ወራት 24 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡
👉 ባንኮች 652 ሚሊየን ዶላር ገዝተው 1 ቢሊየን ገደማ ዶላር ሸጠዋል፡፡
👉 ባለፉት ሦስት ወራት ከኤክስፖርት ምርቶች 1 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ለማግኘት አቅደን፤ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር አግኝተናል፡፡ ይህ ትልቅ ስኬት ነው፡፡
👍12
በዚህ ዓመት 72 ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ስራ እንደሚጀምሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ፤ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ከኢንዱስትሪው በዚህ ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እድገት ይጠበቃል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ እያንዳንዱ ፋብሪካ ችግሩ እንዲፈታ ከፍተኛ ስራ መከናወኑን ገልጸዋል።
በዚህም የኤሌክትሪክ፣ የቴሌኮም፣ የባንክና ሌሎች አገልግሎቶች መቀረፋቸውን ተናግረዋል።
ከመሬት አቅርቦት፣ ከመንግሥታዊ አገልግሎትና ከጉምሩክ ጋር የተያያዙ በርካታ ችግሮች እየተፈቱ ነው ብለዋል።
በዚህ ዓመትም 72 አዳዲስ ከፋብሪካ በላይ የሆኑ ኢንዱስትሪዎች ሥራ እንደሚጀምሩ ጠቅሰዋል።
ሥራ የሚጀምሩትም 9 የጨርቃጨርቅ፣ 41 የምግብና መጠጥ፣ አራት የኮንስትራክሽንና ኬሚካል፣ 15 የቴክኖሎጂ ና ሦስት የሚሊተሪ ኢንዱስትሪዎች ናቸው ብለዋል።
ከመከላከያ ጋር ተያይዞ ከውጭ ይመጡ የነበሩ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለአፍሪካ ገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።
እነዚህ 72 ፋብሪካዎችች ሥራ ሲጀምሩ ቀድመው ከነበሩት ተጨማሪ ኃብት ያመጣሉ ነው ያሉት።
በአገራዊ ለውጡ 50 በመቶ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በሀገር ውስጥ ባለኃብቶች እንዲያዙ በማድረግ በተኪ ምርትም ከፍተኛ እመርታ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በጥቅሉ በዚህ ዓመት የኢንዱስትሪዎች የምርት አቅም ከ59 በመቶ ወደ 67 በመቶ ዕድገት ይጠበቃል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮችና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ፤ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ከኢንዱስትሪው በዚህ ዓመት 12 ነጥብ 8 በመቶ እድገት ይጠበቃል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ እያንዳንዱ ፋብሪካ ችግሩ እንዲፈታ ከፍተኛ ስራ መከናወኑን ገልጸዋል።
በዚህም የኤሌክትሪክ፣ የቴሌኮም፣ የባንክና ሌሎች አገልግሎቶች መቀረፋቸውን ተናግረዋል።
ከመሬት አቅርቦት፣ ከመንግሥታዊ አገልግሎትና ከጉምሩክ ጋር የተያያዙ በርካታ ችግሮች እየተፈቱ ነው ብለዋል።
በዚህ ዓመትም 72 አዳዲስ ከፋብሪካ በላይ የሆኑ ኢንዱስትሪዎች ሥራ እንደሚጀምሩ ጠቅሰዋል።
ሥራ የሚጀምሩትም 9 የጨርቃጨርቅ፣ 41 የምግብና መጠጥ፣ አራት የኮንስትራክሽንና ኬሚካል፣ 15 የቴክኖሎጂ ና ሦስት የሚሊተሪ ኢንዱስትሪዎች ናቸው ብለዋል።
ከመከላከያ ጋር ተያይዞ ከውጭ ይመጡ የነበሩ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ ለአፍሪካ ገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።
እነዚህ 72 ፋብሪካዎችች ሥራ ሲጀምሩ ቀድመው ከነበሩት ተጨማሪ ኃብት ያመጣሉ ነው ያሉት።
በአገራዊ ለውጡ 50 በመቶ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በሀገር ውስጥ ባለኃብቶች እንዲያዙ በማድረግ በተኪ ምርትም ከፍተኛ እመርታ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በጥቅሉ በዚህ ዓመት የኢንዱስትሪዎች የምርት አቅም ከ59 በመቶ ወደ 67 በመቶ ዕድገት ይጠበቃል ብለዋል።
👍12
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-
👉 የዋጋ ግሽበት ባለፉት ዓመታት በርካታ ሀገራትን ፈትኗል ፤ ኢትዮጵያም የዋጋ ግሽበትን ለመቅረፍ በርካታ ስራዎችን እያከናወነች ነው፤ በተለይም ምርት ማምረት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
👉 በሀገሪቱ የሚስተዋለውን የዋጋ ግሽበት ለመቅረፍም ከ300 እስከ 400 ቢሊየን ዶላር ለድጎማ ተይዟል፡፡
👉 ባለፉት 3 ወራት ለነዳጅ ዘርፍ 35 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ተደጉሟል፤ በበጀት ዓመቱ ለሴፍቲነት 80 ቢሊየን ብር፣ ለዘይት 9 ቢሊየን ብር፣ ለማዳበሪያ 53 ቢሊየን ብር ለድጎማ ተመድቧል፡፡
👉 የደመወዝ ጭማሪውን በተመለከተ ከፍተኛ የዳታ ችግር ተፈጥሯል፤ ይህን ዳታ ለማጥራት ከፍተኛ ሥራ ሲሰራ ቆይቷል፡፡
👉 ለደመወዝ ጭማሪ 91 ቢሊየን ብር ተመድቧል፤ ጭማሪውም በተያዘው ጥቅምትር ወር ጀምሮ ተግባረዊ ይደረጋል፡፡
👉 በተያዘው በጀት ዓመት የዋጋ ግሽበት 17 በመቶ ሆኗል፤ ይህም ካለፉት ዓመታት አንጻር የተሻለ ሥራ መሰራቱን ያመላክታል፡፡
👉 ኢንዱስት ፓርኮች 50 በመቶ በሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ተይዘዋል፡፡
👉 ከነበሩበት 59 በመቶ የማምረት ዐቅም በዚህ ዓመት 67 በመቶ የምርት ዕድገት ይጠበቅባቸዋል ኢንዱስትሪ ፓርኮች፡፡
👉 124 አዳዲስ አውሮፕላኖች አዝዘናል፡፡ በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነውን አውሮፕላን በእጥፍ ለመብለጥ እየተሠራ ነው፡፡
👉 በአፍሪካ ትልቁን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እየሠራን ነው፡፡
👉 ከነበሩበት 59 በመቶ የማምረት ዐቅም በዚህ ዓመት 67 በመቶ የምርት ዕድገት ይጠበቅባቸዋል ኢንዱስትሪ ፓርኮች፡፡
👉 124 አዳዲስ አውሮፕላኖች አዝዘናል፡፡ በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነውን አውሮፕላን በእጥፍ ለመብለጥ እየተሠራ ነው፡፡
👉 የዋጋ ግሽበት ባለፉት ዓመታት በርካታ ሀገራትን ፈትኗል ፤ ኢትዮጵያም የዋጋ ግሽበትን ለመቅረፍ በርካታ ስራዎችን እያከናወነች ነው፤ በተለይም ምርት ማምረት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
👉 በሀገሪቱ የሚስተዋለውን የዋጋ ግሽበት ለመቅረፍም ከ300 እስከ 400 ቢሊየን ዶላር ለድጎማ ተይዟል፡፡
👉 ባለፉት 3 ወራት ለነዳጅ ዘርፍ 35 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ተደጉሟል፤ በበጀት ዓመቱ ለሴፍቲነት 80 ቢሊየን ብር፣ ለዘይት 9 ቢሊየን ብር፣ ለማዳበሪያ 53 ቢሊየን ብር ለድጎማ ተመድቧል፡፡
👉 የደመወዝ ጭማሪውን በተመለከተ ከፍተኛ የዳታ ችግር ተፈጥሯል፤ ይህን ዳታ ለማጥራት ከፍተኛ ሥራ ሲሰራ ቆይቷል፡፡
👉 ለደመወዝ ጭማሪ 91 ቢሊየን ብር ተመድቧል፤ ጭማሪውም በተያዘው ጥቅምትር ወር ጀምሮ ተግባረዊ ይደረጋል፡፡
👉 በተያዘው በጀት ዓመት የዋጋ ግሽበት 17 በመቶ ሆኗል፤ ይህም ካለፉት ዓመታት አንጻር የተሻለ ሥራ መሰራቱን ያመላክታል፡፡
👉 ኢንዱስት ፓርኮች 50 በመቶ በሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ተይዘዋል፡፡
👉 ከነበሩበት 59 በመቶ የማምረት ዐቅም በዚህ ዓመት 67 በመቶ የምርት ዕድገት ይጠበቅባቸዋል ኢንዱስትሪ ፓርኮች፡፡
👉 124 አዳዲስ አውሮፕላኖች አዝዘናል፡፡ በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነውን አውሮፕላን በእጥፍ ለመብለጥ እየተሠራ ነው፡፡
👉 በአፍሪካ ትልቁን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እየሠራን ነው፡፡
👉 ከነበሩበት 59 በመቶ የማምረት ዐቅም በዚህ ዓመት 67 በመቶ የምርት ዕድገት ይጠበቅባቸዋል ኢንዱስትሪ ፓርኮች፡፡
👉 124 አዳዲስ አውሮፕላኖች አዝዘናል፡፡ በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነውን አውሮፕላን በእጥፍ ለመብለጥ እየተሠራ ነው፡፡
👍13
አትዮ ቴሌኮም ለኢትዮጵያ የኤክትሮኒክ ግብይት ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*************************
አትዮ ቴሌኮም ለኢትዮጵያ የኤክትሮኒክ ግብይት ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አትዮ ቴሌኮም ሰዎችን በስልክ ከማገናኘት አልፎ ኢ-ኮሜርስ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲያድግ ከፍተኛ ድርሻ እየተጫወተ ይገኛል“ ብለዋል
ተቋሙ የኤክትሮኒክ ግብይት ላይ በትኩረት በመሥራቱ በሀገሪቱ በሞባይል ስልክ የሚፈጸም የግብይት መጠን በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን አንስተዋል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እያስፋፋው የሚገኘው የ5ጂ ቴክኖሎጂም ለዘርፉ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ በቅርቡ ያካሄደው የ10 በመቶ የአክስዮን ሽያጭ የተቋሙን አቅም ይበልጥ እንደሚሳድገውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመላክተዋል፡፡
*************************
አትዮ ቴሌኮም ለኢትዮጵያ የኤክትሮኒክ ግብይት ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አትዮ ቴሌኮም ሰዎችን በስልክ ከማገናኘት አልፎ ኢ-ኮሜርስ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲያድግ ከፍተኛ ድርሻ እየተጫወተ ይገኛል“ ብለዋል
ተቋሙ የኤክትሮኒክ ግብይት ላይ በትኩረት በመሥራቱ በሀገሪቱ በሞባይል ስልክ የሚፈጸም የግብይት መጠን በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን አንስተዋል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እያስፋፋው የሚገኘው የ5ጂ ቴክኖሎጂም ለዘርፉ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ጠቁመዋል፡፡
ተቋሙ በቅርቡ ያካሄደው የ10 በመቶ የአክስዮን ሽያጭ የተቋሙን አቅም ይበልጥ እንደሚሳድገውም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አመላክተዋል፡፡
👍13
የኢትዮጵያን ዕዳ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ ይሰራል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*********************
በሚቀጥሉት ዓመታት የኢትዮጵያን ዕዳ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ የብድር ጫና ከአጠቃላይ ሀገራዊ ጥቅል ምርት አንጻር ከነበረበት ከ30 ነጥብ 6 በመቶ ወደ 13 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡
በሚቀጥሉት ዓመታት ይህን አሃዝ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ እንደሚሰራም አስታውቀዋል፡፡
ባለፉት ስድስት ዓመታት መንግስት ምንም አይነት የንግድ ብድር አለመውሰዱን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተጠቀሰው ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የኢትዮ ቴሌኮምን ሳይጨምር 13 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ መክፈሉን ገልጸዋል፡፡
“ይህም ለትውልዱ ዕዳን ሳይሆን ምንዳን ለማውረስ የምናደርገውን ሥራ የሚያግዝ ነው” ብለዋል፡፡
*********************
በሚቀጥሉት ዓመታት የኢትዮጵያን ዕዳ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ የብድር ጫና ከአጠቃላይ ሀገራዊ ጥቅል ምርት አንጻር ከነበረበት ከ30 ነጥብ 6 በመቶ ወደ 13 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡
በሚቀጥሉት ዓመታት ይህን አሃዝ ከ10 በመቶ በታች ለማድረግ እንደሚሰራም አስታውቀዋል፡፡
ባለፉት ስድስት ዓመታት መንግስት ምንም አይነት የንግድ ብድር አለመውሰዱን ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተጠቀሰው ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የኢትዮ ቴሌኮምን ሳይጨምር 13 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ መክፈሉን ገልጸዋል፡፡
“ይህም ለትውልዱ ዕዳን ሳይሆን ምንዳን ለማውረስ የምናደርገውን ሥራ የሚያግዝ ነው” ብለዋል፡፡
👍13