African Leadership Excellence Academy
2.13K subscribers
2.38K photos
89 videos
6 files
104 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
የገጠር መንገድ ትስስርን ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ማረጋገጠ አለብን ሲሉ የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሄለን ደበበ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ውስጥ በተደረገው መርሀ ግብር ላይ ተናገሩ፡፡

ሚኒስትር ዲኤታዋ ይህን ያሉት ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ የመንገድና ትራንሰፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሚኒስቴር መ/ቤቱ አስተባባሪነትና በአለም ባንክ ድጋፍ በ407 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገጠር ትስስርን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን አዲሱን ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ ውስጥ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ስንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ጥቅምት 4ቀን 2017 ዓ.ም ለ17ኛ ጊዜ #በአፍሪካ_አመራር_ልህቀት_አካዳሚ የአመራር ልማት ማዕከል ተከብሯል፡፡

በዕለቱ የአካዳሚው ም/ል ርዕሰ አካዳሚ #ወንድዬ _ለገሰ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት #ሰንደቅ_ዓላማችን የኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን የጋራ ዓርማ በመሆኑ ልንጠብቅውና በክብር ለትውልድ ልናስተላልፈው ይገባል ብለዋል::

ም/ል ርዕሰ አካዳሚው አያይዘውም ሰንደቅ ዓላማችን ክብሩና ዝናዉ ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገር የአካዳሚው ማህብረሰብ ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባው ጠቅሰው ሁሉም አመራር እና ሰራተኛ በተሰማራበት የስራ መስክ ጠንክሮ በመስራት ለሀገሩ ብልፅግና የድርሻውን እንዲያበርክት ጥሪ አቅርበዋል::

የአካዳሚው ማህበረሰብም ከፌዴራል ፖሊስ አባላት ጋር በመሆን በሰንደቅ ዓላማው ስር ቃል በመግባት የበዓሉ ፍፃሜ ሆኗል::