አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት የተሰጠው ሹመት የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ሲመክሩበት ቆይተው የወሰኑት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ሹመቶችን ባጸደቀበት ወቅት ነው፡፡
ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ፓርቲው ከበርካታ እጩዎች ውስጥ ባላቸው ልምድ ኢትዮጵያን ማገልገል የሚችሉ እጩዎችን ወደ ፊት ለማምጣት የወሰነበት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
በተለይም ከተሿሚዎች ውስጥ ሁለቱ ከብልጽግና ፓርቲ አባል ውጪ መሆናቸው ለኢትዮጵያ ቅድሚያ የተሰጠበት እና ልምድ እና እውቀት ብቻ መስፈርት የሆነበት መሆኑን አውስተዋል፡፡
ከየትኛውም ፓርቲ ቢሆን ልምድና እውቀት ያላቸውን ወደፊት ማምጣቱ እንደሚቀጥልም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ባለው የመተካካት ባህል የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከሥራ አስፈፃሚነታቸው በክብር መሸኘታቸውን ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲሁም ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበለትን ሹመት መርምሮ አጽድቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ሹመቶችን ባጸደቀበት ወቅት ነው፡፡
ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)÷ ፓርቲው ከበርካታ እጩዎች ውስጥ ባላቸው ልምድ ኢትዮጵያን ማገልገል የሚችሉ እጩዎችን ወደ ፊት ለማምጣት የወሰነበት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
በተለይም ከተሿሚዎች ውስጥ ሁለቱ ከብልጽግና ፓርቲ አባል ውጪ መሆናቸው ለኢትዮጵያ ቅድሚያ የተሰጠበት እና ልምድ እና እውቀት ብቻ መስፈርት የሆነበት መሆኑን አውስተዋል፡፡
ከየትኛውም ፓርቲ ቢሆን ልምድና እውቀት ያላቸውን ወደፊት ማምጣቱ እንደሚቀጥልም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ባለው የመተካካት ባህል የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከሥራ አስፈፃሚነታቸው በክብር መሸኘታቸውን ተናግረዋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንዲሁም ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበለትን ሹመት መርምሮ አጽድቋል፡፡
ከ UN Women ለመጡ የስራ ሀላፊዎች ስለ አፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሪፎርም፤ ማስፋትና ሽግግር ሰፊ ገለጻ ተደረገላቸው።
ገለጻውን ያደረጉት የአፍሌክስ ፕሮግራም ዘርፍ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ተወካይ አቶ ጥላሁን አረጋ ሲሆኑ አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ቀርጾ እየሰራ ነው ብለዋል።
አካዳሚው የአፍሪካን እና የኢትዮጵያን አመራር ለማብቃት በሀገር ውስጥ ካሉ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር እየሰራ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ጥላሁን የሴቶችን አቅም በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማጎልበትም ከሜሊንዳ እና ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ከ UN Women ጋር በመስራትም የአካዳሚውን ስትራቴጂያዊ የግንኙነት አድማስ ማስፋት እንደሚያስፈልግ እና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ትብብር ለመመስረት እንደሚፈልጉ የጠቆሙት አቶ ጥላሁን በቴክኒካል፤ በፕሮግራም እና በመሰረተ ልማት አብረው እንዲሰሩ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከ UN Women የመጡት የልፍኝ አበጋዝ በበኩላቸው አፍሌክስ በሶስት ዓመት ውስጥ ሊተገብራቸው ያቀዳቸውን ፕሮጀክቶች አድንቀው በገለጻው ያገኙትን ግንዛቤ ለ UN Women ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በማጋራት እና በመነጋገር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር የሚቻልበትን ሁኔታ እንደሚያመቻቹ ተናግረዋል።
ከ UN Women የመጡት የስራ ሀላፊዎችም ለአፍሌክስ ግምታቸው ከሰባ ሺህ ብር በላይ የሆኑ መጽሀፍት በስጦታ ያበረከቱ ሲሆን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ፋሲሊቲም ጎብኝተዋል።
ገለጻውን ያደረጉት የአፍሌክስ ፕሮግራም ዘርፍ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ተወካይ አቶ ጥላሁን አረጋ ሲሆኑ አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ እና በሀገራችን የነበረውን የስልጠና ስርአት ወደ አመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳደግ የሶስት ዓመት ስትራቴጂ ቀርጾ እየሰራ ነው ብለዋል።
አካዳሚው የአፍሪካን እና የኢትዮጵያን አመራር ለማብቃት በሀገር ውስጥ ካሉ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር እየሰራ እንደሆነ የጠቀሱት አቶ ጥላሁን የሴቶችን አቅም በአመራር ልማት ፕሮግራም ለማጎልበትም ከሜሊንዳ እና ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በመሆን እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።
ከ UN Women ጋር በመስራትም የአካዳሚውን ስትራቴጂያዊ የግንኙነት አድማስ ማስፋት እንደሚያስፈልግ እና በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ትብብር ለመመስረት እንደሚፈልጉ የጠቆሙት አቶ ጥላሁን በቴክኒካል፤ በፕሮግራም እና በመሰረተ ልማት አብረው እንዲሰሩ ጥያቄ አቅርበዋል።
ከ UN Women የመጡት የልፍኝ አበጋዝ በበኩላቸው አፍሌክስ በሶስት ዓመት ውስጥ ሊተገብራቸው ያቀዳቸውን ፕሮጀክቶች አድንቀው በገለጻው ያገኙትን ግንዛቤ ለ UN Women ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በማጋራት እና በመነጋገር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር የሚቻልበትን ሁኔታ እንደሚያመቻቹ ተናግረዋል።
ከ UN Women የመጡት የስራ ሀላፊዎችም ለአፍሌክስ ግምታቸው ከሰባ ሺህ ብር በላይ የሆኑ መጽሀፍት በስጦታ ያበረከቱ ሲሆን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ፋሲሊቲም ጎብኝተዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከሲቪል ሶሳይቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያዩ።
አቶ ዛዲግ አብርሃ በአፍሌክስ ሪፎርም(Reform)፤ ማስፋት (Scaling Up) እና ሽግግር (Transformation) ለሲቪል ሶሳይቲ ከፍተኛ አመራሮች ገለጻ አድርገዋል።
አፍሌክስ የጀመረውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳካት የሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ርዕሰ አካዳሚው ተናግረዋል።
አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም በመስራት ላይ እንደሆነም አቶ ዛዲግ ገልጸዋል።
ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመሆንም በአመራር ልማት ፕሮግራም፤ በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ እና በአፍሌክስ ሽልማት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ለመፈራረም መስማማታቸውንም አቶ ዛዲግ አብርሃ ጠቅሰዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳውን ራዕይ ለማሳካት ተቋማቸው ዝግጁ እንደሆነ ጠቁመው፤ ባለስልጣኑ የሚቆጣጠራቸው ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶችም ከአፍሌክስ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
የሲቪል ሶሳይቲ ከፍተኛ አመራሮች ስለ አፍሌክስ ፕሮጀክቶች እና የአመራር ልማት ፕሮግራሞች በተደረገላቸው ማብራሪያ መደሰታቸውን ጠቅሰው፤ ለአካዳሚው የሚጠቅሙ ሀሳቦችን እና አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን እንዲብራሩላቸው ባነሷቸው ጥያቄዎች ላይም ርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ በአፍሌክስ ሪፎርም(Reform)፤ ማስፋት (Scaling Up) እና ሽግግር (Transformation) ለሲቪል ሶሳይቲ ከፍተኛ አመራሮች ገለጻ አድርገዋል።
አፍሌክስ የጀመረውን የአመራር ልማት ፕሮግራም ለማሳካት የሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ርዕሰ አካዳሚው ተናግረዋል።
አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም በመስራት ላይ እንደሆነም አቶ ዛዲግ ገልጸዋል።
ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመሆንም በአመራር ልማት ፕሮግራም፤ በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ እና በአፍሌክስ ሽልማት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ለመፈራረም መስማማታቸውንም አቶ ዛዲግ አብርሃ ጠቅሰዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በበኩላቸው አፍሌክስ ይዞ የተነሳውን ራዕይ ለማሳካት ተቋማቸው ዝግጁ እንደሆነ ጠቁመው፤ ባለስልጣኑ የሚቆጣጠራቸው ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶችም ከአፍሌክስ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
የሲቪል ሶሳይቲ ከፍተኛ አመራሮች ስለ አፍሌክስ ፕሮጀክቶች እና የአመራር ልማት ፕሮግራሞች በተደረገላቸው ማብራሪያ መደሰታቸውን ጠቅሰው፤ ለአካዳሚው የሚጠቅሙ ሀሳቦችን እና አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን እንዲብራሩላቸው ባነሷቸው ጥያቄዎች ላይም ርዕሰ አካዳሚው ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በበኩላቸው ከአፍሌክስ ጋር በሶስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት በመፈራረማቸው ደስተኛ እንደሆኑ ገልጸው፤ በተለይም ከዚህ ቀደም በተቋማቸው ተጀምሮ የነበረውን የአፍሪካ የሲቪል ሶሳይቲ ልህቀት ማዕከል በአፍሌክስ ውስጥ መገንባቱ የዘርፉ አመራሮች የሚሰባሰቡበት፤ ሀሳባቸውን የሚያንሸራሽሩበት፤ የጥናት እና ምርምር ስራዎቻቸውን የሚያጎለብቱበት እንደሚሆን ጠቅሰዋል።