የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና የኢፌዴሪ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
ሁለቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት የተስማሙት በአመራር ልማት ፕሮግራም፤ በአፍሌክስ ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ ላይ ሲሆን የሲቪል ማህበረሰቡን አቅም ለመገንባት የሚያግዝ ትብብር እንደሆነም ተገልጿል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ሀሳብን እያመነጩ ለመመራመር እና ጥናት ለማድረግ የተሟላ መሰረተ ልማት ያለው የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመሆን የአፍሪካ ሲቪል ሶሳይቲ ልሕቀት ማዕከል ለመገንባት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል።
በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዘርፍ ያሉትን ከፍተኛ አመራሮች አቅም ለመገንባትም በአፍሌክስ ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራም ውስጥ በማስገባት የሚጠበቅባቸውን ሀገራዊ እና ማህበራዊ ሃላፊነት እንዲወጡ የሚያግዙ ፕሮግራሞች መኖራቸውን ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው በዚህም ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።
የተሻለ አፈጸጸም ያስመዘገቡ እና በአርአያነታቸው ለሌሎች ተምሳሌት የሚሆኑ የዘርፉን አመራሮች ለመሸለም የሚያስችል ስምምነት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር መኖሩንም አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናግረዋል።
ሁለቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት የተስማሙት በአመራር ልማት ፕሮግራም፤ በአፍሌክስ ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ ላይ ሲሆን የሲቪል ማህበረሰቡን አቅም ለመገንባት የሚያግዝ ትብብር እንደሆነም ተገልጿል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ሀሳብን እያመነጩ ለመመራመር እና ጥናት ለማድረግ የተሟላ መሰረተ ልማት ያለው የሀሳብ ማመንጫ ማዕከል እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በመሆን የአፍሪካ ሲቪል ሶሳይቲ ልሕቀት ማዕከል ለመገንባት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል።
በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ዘርፍ ያሉትን ከፍተኛ አመራሮች አቅም ለመገንባትም በአፍሌክስ ጠቅላላ እና ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራም ውስጥ በማስገባት የሚጠበቅባቸውን ሀገራዊ እና ማህበራዊ ሃላፊነት እንዲወጡ የሚያግዙ ፕሮግራሞች መኖራቸውን ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው በዚህም ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።
የተሻለ አፈጸጸም ያስመዘገቡ እና በአርአያነታቸው ለሌሎች ተምሳሌት የሚሆኑ የዘርፉን አመራሮች ለመሸለም የሚያስችል ስምምነት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር መኖሩንም አቶ ዛዲግ አብርሃ ተናግረዋል።
"እድል እና ትግል ሲገናኙ መከናወን ይሆናል፤ ኢትዮጵያዊነት የታደልነው ነው፤ ይህ መታሰቢያ ደግሞ ታግለን የሠራነው ነው"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የዓድዋ ድል መታሰቢያን በይፋ መርቀው ከፍተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በመርሃግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "እድል እና ትግል ሲገናኙ መከናወን ይሆናል። ኢትዮጵያዊነት የታደልነው ነው፤ ይህ መታሰቢያ ደግሞ ታግለን የሠራነው ነው ብለዋል።
መታሰቢያው ኢትዮጵያዊ በመሆናችን ታድለን የመስራት ጥረት ታክሎበት የተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከ128 ዓመት በኋላ ተከውኖ ለልጆች ማለፍ በሚችልበት መልኩ ከነግርማ ሞገሱ ኢትዮጵያን መስሎ ኢትዮጵያን አክሎ የታየበት መሆኑንም ገልጸዋል።
የዓድዋን ድል ማርከስ ማለት የአባቶቻችንን አጥንትና ደም ማርከስ መሆኑንም ገልጸዋል።
አባቶቻችን ዋጋ የከፈሉበት ነጻነትና ክብር እሴት መሆኑን ገልጸው ነጻነትን ለማግኘት የሄዱበት መንገድ እሳት መሆኑን ገልጸዋል።
ከአባቶቻችን ልንወርስ የሚገባው ነጻነቱን ክብሩንና አንድነቱን እንጂ እሳቱን መሆን አይጠበቅብንም ብለዋል።
በምረቃ መርሃግብ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የሁለቱም ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ተገኝተዋል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ ለአሁኑ ትውልድ ኩራትና መማሪያ እንዲሆን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት በአዲስ አበባ አተማ አስተዳደር መገንባቱ ተገልጿል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
****
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የዓድዋ ድል መታሰቢያን በይፋ መርቀው ከፍተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በመርሃግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "እድል እና ትግል ሲገናኙ መከናወን ይሆናል። ኢትዮጵያዊነት የታደልነው ነው፤ ይህ መታሰቢያ ደግሞ ታግለን የሠራነው ነው ብለዋል።
መታሰቢያው ኢትዮጵያዊ በመሆናችን ታድለን የመስራት ጥረት ታክሎበት የተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከ128 ዓመት በኋላ ተከውኖ ለልጆች ማለፍ በሚችልበት መልኩ ከነግርማ ሞገሱ ኢትዮጵያን መስሎ ኢትዮጵያን አክሎ የታየበት መሆኑንም ገልጸዋል።
የዓድዋን ድል ማርከስ ማለት የአባቶቻችንን አጥንትና ደም ማርከስ መሆኑንም ገልጸዋል።
አባቶቻችን ዋጋ የከፈሉበት ነጻነትና ክብር እሴት መሆኑን ገልጸው ነጻነትን ለማግኘት የሄዱበት መንገድ እሳት መሆኑን ገልጸዋል።
ከአባቶቻችን ልንወርስ የሚገባው ነጻነቱን ክብሩንና አንድነቱን እንጂ እሳቱን መሆን አይጠበቅብንም ብለዋል።
በምረቃ መርሃግብ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ የሁለቱም ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ተገኝተዋል።
የዓድዋ ድል መታሰቢያ ለአሁኑ ትውልድ ኩራትና መማሪያ እንዲሆን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጪነት በአዲስ አበባ አተማ አስተዳደር መገንባቱ ተገልጿል።
ከ 21 በላይ ተቋማት ለተውጣጡ 40 ሴት አመራሮች ሲሰጥ የነበረው አራተኛ ዙር የሴት አመራር ልማት ፕሮግራም ተጠናቀቀ።
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የሴት አመራር ፕሮጀክት ማናጀር አቶ መስፍን በሐይሉ እንደገለጹት በስልጠናው ለተሳተፉት ሴት አመራሮች ለውጥን መተንበይ እና መተንተን እንዲሁም የፖሊሲ ተፅዕኖ ማድረግ እንዲችሉ የሚያግዝ ስልጠና ለተከታታይ አምስት ቀናት እንደተሰጠ ጠቅሰው ሴት አመራሮቹ በቀጣይ ለሚሰሩት ፕሮጀክት እንደ ትልቅ ግብዓት ይሆናቸዋል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
አቶ መስፍን አያይዘውም ስልጠናው የተሰጠው ሀገር ውስጥ ባሉ ከፍተኛ ልምድ እና የትምህርት ዝግጅት ባላቸው አሰልጣኞች እንደሆነ አስታውሰው በ Digital leadership, influencing policy making, Change Management & organizational Transformation, System thinking skills for leaders, እና Capstone project seminar ስልጠናው መሰጠቱን ተናግረዋል።
ይህን የሴቶች የአመራር ልማት ፕሮግራም በገንዘብ የሚደግፈው የሚሊንዳ እና ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን እንደሆነም ተገልጿል።
በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የሴት አመራር ፕሮጀክት ማናጀር አቶ መስፍን በሐይሉ እንደገለጹት በስልጠናው ለተሳተፉት ሴት አመራሮች ለውጥን መተንበይ እና መተንተን እንዲሁም የፖሊሲ ተፅዕኖ ማድረግ እንዲችሉ የሚያግዝ ስልጠና ለተከታታይ አምስት ቀናት እንደተሰጠ ጠቅሰው ሴት አመራሮቹ በቀጣይ ለሚሰሩት ፕሮጀክት እንደ ትልቅ ግብዓት ይሆናቸዋል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
አቶ መስፍን አያይዘውም ስልጠናው የተሰጠው ሀገር ውስጥ ባሉ ከፍተኛ ልምድ እና የትምህርት ዝግጅት ባላቸው አሰልጣኞች እንደሆነ አስታውሰው በ Digital leadership, influencing policy making, Change Management & organizational Transformation, System thinking skills for leaders, እና Capstone project seminar ስልጠናው መሰጠቱን ተናግረዋል።
ይህን የሴቶች የአመራር ልማት ፕሮግራም በገንዘብ የሚደግፈው የሚሊንዳ እና ቢል ጌትስ ፋውንዴሽን እንደሆነም ተገልጿል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከፓን አፍሪካን ወጣቶች ህብረት ዋና ጸሀፊ ቤንኢንግ አህመድ BENING AHMED WIISICHONG SECRETARY-GENERAL, PAN AFRICA YOUTH UNION(PYU) ጋር ተወያዩ።
አፍሌክስ የአህጉሪቱን እና የሀገራችንን አመራሮች ለማብቃት ስልጠና ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በማመኑ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰምንት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ ርዕሰ አካዳሚው ለዋና ጸሀፊው ገልጸዋል።
በተለይም በወጣቶች የአመራር ልማት ፕሮግራም የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ወጣቶች አቅም ለመገንባት ፕሮጀክት መቀረጹን የጠቀሱት አቶ ዛዲግ፤ በአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎች ውስጥም ወጣት አመራሮች አቅማቸውን እንዲገነቡ እና ሀሳብ እያፈለቁ የምርምር ስራዎችን እንደዲያበረክቱ አፍሌክስ እየሰራ ነው ብለዋል።
ሀያ ሁለተኛው ክፍለ ዘመን የአፍሪካውያን ብልጽግና የሚረጋገጥበት እንደሆነ ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ቀደምት የአፍሪካ ወጣቶች አህጉሪቷን ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዳወጧት ሁሉ የዚህ ዘመን ትውልድም ከድህነት የምትላቀቅበትን መንገድ እንዲቀይስ የሚያግዙ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እንደተቀረጹ አቶ ዛዲግ ተናግረዋል።
አፍሌክስ የአህጉሪቱን እና የሀገራችንን አመራሮች ለማብቃት ስልጠና ብቻውን በቂ እንዳልሆነ በማመኑ አራት ጠቅላላ እና ሰላሳ ሰምንት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ነድፎ ወደ ስራ እየገባ እንደሆነ ርዕሰ አካዳሚው ለዋና ጸሀፊው ገልጸዋል።
በተለይም በወጣቶች የአመራር ልማት ፕሮግራም የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ወጣቶች አቅም ለመገንባት ፕሮጀክት መቀረጹን የጠቀሱት አቶ ዛዲግ፤ በአመራር ልማት ፕሮግራም ማዕቀፎች ውስጥም ወጣት አመራሮች አቅማቸውን እንዲገነቡ እና ሀሳብ እያፈለቁ የምርምር ስራዎችን እንደዲያበረክቱ አፍሌክስ እየሰራ ነው ብለዋል።
ሀያ ሁለተኛው ክፍለ ዘመን የአፍሪካውያን ብልጽግና የሚረጋገጥበት እንደሆነ ያስታወሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ቀደምት የአፍሪካ ወጣቶች አህጉሪቷን ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዳወጧት ሁሉ የዚህ ዘመን ትውልድም ከድህነት የምትላቀቅበትን መንገድ እንዲቀይስ የሚያግዙ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች እንደተቀረጹ አቶ ዛዲግ ተናግረዋል።
አፍሪካን ከአጀንዳ ተቀባይነት ወደ አጀንዳ ባለቤትነት የሚያሸጋግሩ ፕሮጀክቶችም በአፍሌክስ ውስጥ እየተዘጋጁ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ዛዲግ፤ የአፍሪካ ወጣቶችም የአፍሪካውያንን አጀንዳ በመቅረጽ እና በማስፈጸም ረገድ በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ አፍሌክስ ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ርዕሰ አካዳሚው አያይዘውም የፓን አፍሪካን ወጣቶች ህብረት ከአፍሌክስ ጋር በወጣቶች አመራር ልማት ፕሮግራም፤ በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ እና በአፍሌክስ አመራር ሽልማት ላይ አብረው እንዲሰሩ ግብዣ አቅርበዋል።
የፓን አፍሪካን ወጣቶች ህብረት ዋና ጸሀፊ ቤንኢንግ አህመድ BENING AHMED WIISICHONG SECRETARY-GENERAL, PAN AFRICA YOUTH UNION (PYU) በበኩላቸው አፍሌክስ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን አመራሮች አቅም ግንባታ የሚሰራውን ስራ አድንቀው ህብረቱ በቀረበለት ግብዣ መሰረት ከአካዳሚው ጋር ለመስራት ዝግጁ እንደሆነ እና የጋራ መግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ወደ ተግባር ለመግባት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
ርዕሰ አካዳሚው አያይዘውም የፓን አፍሪካን ወጣቶች ህብረት ከአፍሌክስ ጋር በወጣቶች አመራር ልማት ፕሮግራም፤ በሀሳብ ማመንጫ ማዕከል ግንባታ እና በአፍሌክስ አመራር ሽልማት ላይ አብረው እንዲሰሩ ግብዣ አቅርበዋል።
የፓን አፍሪካን ወጣቶች ህብረት ዋና ጸሀፊ ቤንኢንግ አህመድ BENING AHMED WIISICHONG SECRETARY-GENERAL, PAN AFRICA YOUTH UNION (PYU) በበኩላቸው አፍሌክስ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን አመራሮች አቅም ግንባታ የሚሰራውን ስራ አድንቀው ህብረቱ በቀረበለት ግብዣ መሰረት ከአካዳሚው ጋር ለመስራት ዝግጁ እንደሆነ እና የጋራ መግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ወደ ተግባር ለመግባት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
አፍሪካ እና የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 484/2013 እንደ አዲስ የተቋቋመው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የተሰጠውን ሀገራዊ እና አህጉራዊ ተልዕኮ ለመወጣት እንዲችል፤ በቅርጽም ሆነ በይዘት አፍሪካዊ እንዲሆን የሚያስችሉ የሪፎርም፤ የማስፋት እና የሽግግር ሂደቶች ውስጥ ይገኛል።
አፍሪካዊ ተቋም እንዳይሆን ያደረጉትን ውስንነቶች በጥናት በመለየት፤ ችግሮቹን በመፍታት፤ ከአፍሪካውያን ወንድሞች እና እህቶች ጋር በአመራር ልማት ፕሮግራም እና በትምህርት መስክ ለመስራት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ፤ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ስራ ገብቷል።
ሱሉልታ የሚገኘው የተቋሙ የአመራር ልማት ማዕከል በቻይና መንግስት ድጋፍ እንደመሰራቱ፤ ሕንጻው እና በውስጡ የሚገኙ መገልገያዎች በሙሉ የቻይናን የስነ ህንጻ ጥበብ የሚያጎሉ እና የቻይናን የስልጠና ማዕከላት ቅርጽ የሚያንጸባርቁ ናቸው።
ይህ ደግሞ የአፍሪካን ስያሜ እና ተልዕኮ ይዞ ለሚሰራ አካዳሚ አፍሪካዊ ባህልን እና እሴትን አለማካተቱ በተልዕኮው አፈጻጸም ላይ የራሱን አሉታዊ ጫና እንደሚኖረው በጥናት ተለይቷል።
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 484/2013 እንደ አዲስ የተቋቋመው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የተሰጠውን ሀገራዊ እና አህጉራዊ ተልዕኮ ለመወጣት እንዲችል፤ በቅርጽም ሆነ በይዘት አፍሪካዊ እንዲሆን የሚያስችሉ የሪፎርም፤ የማስፋት እና የሽግግር ሂደቶች ውስጥ ይገኛል።
አፍሪካዊ ተቋም እንዳይሆን ያደረጉትን ውስንነቶች በጥናት በመለየት፤ ችግሮቹን በመፍታት፤ ከአፍሪካውያን ወንድሞች እና እህቶች ጋር በአመራር ልማት ፕሮግራም እና በትምህርት መስክ ለመስራት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ፤ ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ስራ ገብቷል።
ሱሉልታ የሚገኘው የተቋሙ የአመራር ልማት ማዕከል በቻይና መንግስት ድጋፍ እንደመሰራቱ፤ ሕንጻው እና በውስጡ የሚገኙ መገልገያዎች በሙሉ የቻይናን የስነ ህንጻ ጥበብ የሚያጎሉ እና የቻይናን የስልጠና ማዕከላት ቅርጽ የሚያንጸባርቁ ናቸው።
ይህ ደግሞ የአፍሪካን ስያሜ እና ተልዕኮ ይዞ ለሚሰራ አካዳሚ አፍሪካዊ ባህልን እና እሴትን አለማካተቱ በተልዕኮው አፈጻጸም ላይ የራሱን አሉታዊ ጫና እንደሚኖረው በጥናት ተለይቷል።