በኢትዮጵያ የሚገኙ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች እና ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን ጎበኙ፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት ተቋሙ በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ ከፍተኛ አመራሮችን እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም በአፍሪካ ደረጃ በማሳደግ የአህጉሩን መሪዎች አቅም በማጎልበት የአፍሪካን ብልፅግና ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
አካዳሚው ከስልጠና በተጨማሪ በምርምርና ማማከር አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን በቅርቡም የፓን አፍሪካኒዝም ፎረም እንደሚያዘጋጅ ተጠቅሷል፡፡
በጉብኝቱ ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍስሀ ሻውልን ጨምሮ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በኢትዮጵያ የራሺያ ፌዴሬሽን አምባሳደር Yevgeny Tarekhin ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይቱ ላይ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት አካዳሚው እንደ አዲስ በሚኒስትሮች ም/ቤት ከተቋቋመ ጀምሮ የመንግስትንና የግል ተቋማትን አመራሮች በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ተቋማዊ ሪፎርም እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
ተቋማዊ ሪፎርሙ ሲጠናቀቅም አካዳሚው ሊያከናውናቸው ያቀዳቸው በርካታ አገር አቀፍና አህጉር አቀፍ ፕሮግራሞች መኖራቸውን የጠቀሱት ዶ/ር ምህረት ይህንንም ለማሳካት ተቋሙ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ስትራቴጂያዊ አጋርነትን በመመስረትም የአካዳሚውን ተልዕኮ ለማሳካት እየተሰራ እንደሆነ የተናገሩት ርዕሰ አካዳሚው ከራሺያ ፌዴሬሽን ጋር በስልጠና እና በምርምር መስኮች በመስራትም የተቋሙን የመፈፀም አቅም ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸውም ገልፀዋል፡፡
አምባሳደር Evgeny Tarekhin በበኩላቸው ከአካዳሚው ጋር በጋራ ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት ገልፀው በቀጣይ በሚደረጉ ውይይቶች የሚዳብር ሀሳብ እንዳላቸው አስታውሰው አካዳሚው ላደረገላቸው መልካም አቀባበልና ግብዣ አመስግነዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት አካዳሚው እንደ አዲስ በሚኒስትሮች ም/ቤት ከተቋቋመ ጀምሮ የመንግስትንና የግል ተቋማትን አመራሮች በተሟላ የስልጠና ማዕከል ውስጥ እያሰለጠነ እንደሆነና ይህንንም ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ተቋማዊ ሪፎርም እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡
ተቋማዊ ሪፎርሙ ሲጠናቀቅም አካዳሚው ሊያከናውናቸው ያቀዳቸው በርካታ አገር አቀፍና አህጉር አቀፍ ፕሮግራሞች መኖራቸውን የጠቀሱት ዶ/ር ምህረት ይህንንም ለማሳካት ተቋሙ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
ስትራቴጂያዊ አጋርነትን በመመስረትም የአካዳሚውን ተልዕኮ ለማሳካት እየተሰራ እንደሆነ የተናገሩት ርዕሰ አካዳሚው ከራሺያ ፌዴሬሽን ጋር በስልጠና እና በምርምር መስኮች በመስራትም የተቋሙን የመፈፀም አቅም ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላቸውም ገልፀዋል፡፡
አምባሳደር Evgeny Tarekhin በበኩላቸው ከአካዳሚው ጋር በጋራ ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት ገልፀው በቀጣይ በሚደረጉ ውይይቶች የሚዳብር ሀሳብ እንዳላቸው አስታውሰው አካዳሚው ላደረገላቸው መልካም አቀባበልና ግብዣ አመስግነዋል፡፡
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ አመራሮችና ሰራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አደረጉ፡፡
ውይይቱን የመሩት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት የሚደረገው በሁሉም የመንግስትቋማት ውስጥ መሆኑን ገልፀው ሰሞኑን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎ ከሀይማኖት አባቶች የሚተላለፉ መልእክቶች በመንግስት ስራ ውስጥ ክፍተት እንዳይፈጥሩ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ሁሉም የአካዳሚው አመራርና ሰራተኛ የበኩሉን ሚና እንዲጫወትም ጠይቀዋል፡፡
የስራ አመራር ዘርፍ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው በሀይማኖት አባቶች መካከል የተፈጠረውን ችግር ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው የሚሰሩ ሀይሎች እንዳሉ ጠቅሰው የአካዳሚው አመራርና ሰራተኞች የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ በሰከነ መንገድ ሰላም እንዲሰፍን የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የአካዳሚው አመራርና ሰራተኞችም የተፈጠረው ችግር በሰላም እንዲፈታ መንግስት እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡
ውይይቱን የመሩት የአካዳሚው ርዕሰ አካዳሚ ዶ/ር ምህረት ደበበ እንደተናገሩት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት የሚደረገው በሁሉም የመንግስትቋማት ውስጥ መሆኑን ገልፀው ሰሞኑን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ተከትሎ ከሀይማኖት አባቶች የሚተላለፉ መልእክቶች በመንግስት ስራ ውስጥ ክፍተት እንዳይፈጥሩ መጠንቀቅ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ሁሉም የአካዳሚው አመራርና ሰራተኛ የበኩሉን ሚና እንዲጫወትም ጠይቀዋል፡፡
የስራ አመራር ዘርፍ ም/ል ርዕሰ አካዳሚ ወንድዬ ለገሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው በሀይማኖት አባቶች መካከል የተፈጠረውን ችግር ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው የሚሰሩ ሀይሎች እንዳሉ ጠቅሰው የአካዳሚው አመራርና ሰራተኞች የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ በሰከነ መንገድ ሰላም እንዲሰፍን የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የአካዳሚው አመራርና ሰራተኞችም የተፈጠረው ችግር በሰላም እንዲፈታ መንግስት እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡
የፓን አፍሪካዊነት እሳቤ ዳግም እንዲያንሰራራ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እየተካሄደ በሚገኘው የፓን አፍሪካዊነት ፎረም ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው።
ኢትዮጵያ የገነባችው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የአፍሪካ ወጣት መሪዎችን ለማፍራት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካ መጠናከር የነበራትን ታሪካዊ የመሪነት ሚና አሁንም አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል።
የፓን አፍሪካ ፎረምን በ2063 የአፍሪካ የልማት አጀንዳ 10 ዓመት እንዲሁም የአፍሪካ ሕብረት ምስረታ ለ60ኛ ዓመት ክብረ በዓል ወቅት ማዘጋጀቷም ለጉዳዩ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፎረሙ ለፓን አፍሪካዊነት መንፈስ እና የአፍሪካ አንድነት እንደ አዲስ ትንሳዔውን እንደሚያበስር ተናገረዋል። የፓን አፍሪካ እንቅስቃሴውን ዕውን ለማድረግ አዲስ አስተሳሰብ፣ አካሄድ እና ጥበብ እንደሚጠይቅም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ሀገራት ከሰው ሰራሽ መልክዓ ምድራዊ የወሰን ሃሳብ መስመሮች እና ከርዕዮተ ዓለም አጥሮች ወጥተው የተባበረች እና የበገለፀገች አፍሪካን ዕውን ለማድረግ መስራት አለባቸውም ነው ያሉት። በተለይም መሪዎች አጀንዳ የሚቀርጽ፣ ተሻጋሪ ሃሳብ የሚያፈልቅ ችግር ፈች አፍሪካዊ ትውልድ ለመገንባት በአርዓያነት ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የፓን አፍሪካዊነት ዳግም ትንሳኤ እንዲያብብ በቁርጠኝነት እንደምትሰራም አረጋግጠዋል።
የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ያዘጋጀው የመጀመሪያው የፓን አፍሪካዊነት ፎረም በአካዳሚው ተከናውኗል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እየተካሄደ በሚገኘው የፓን አፍሪካዊነት ፎረም ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ነው።
ኢትዮጵያ የገነባችው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የአፍሪካ ወጣት መሪዎችን ለማፍራት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለፓን አፍሪካ መጠናከር የነበራትን ታሪካዊ የመሪነት ሚና አሁንም አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ አረጋግጠዋል።
የፓን አፍሪካ ፎረምን በ2063 የአፍሪካ የልማት አጀንዳ 10 ዓመት እንዲሁም የአፍሪካ ሕብረት ምስረታ ለ60ኛ ዓመት ክብረ በዓል ወቅት ማዘጋጀቷም ለጉዳዩ ያላትን ቁርጠኝነት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፎረሙ ለፓን አፍሪካዊነት መንፈስ እና የአፍሪካ አንድነት እንደ አዲስ ትንሳዔውን እንደሚያበስር ተናገረዋል። የፓን አፍሪካ እንቅስቃሴውን ዕውን ለማድረግ አዲስ አስተሳሰብ፣ አካሄድ እና ጥበብ እንደሚጠይቅም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ሀገራት ከሰው ሰራሽ መልክዓ ምድራዊ የወሰን ሃሳብ መስመሮች እና ከርዕዮተ ዓለም አጥሮች ወጥተው የተባበረች እና የበገለፀገች አፍሪካን ዕውን ለማድረግ መስራት አለባቸውም ነው ያሉት። በተለይም መሪዎች አጀንዳ የሚቀርጽ፣ ተሻጋሪ ሃሳብ የሚያፈልቅ ችግር ፈች አፍሪካዊ ትውልድ ለመገንባት በአርዓያነት ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የፓን አፍሪካዊነት ዳግም ትንሳኤ እንዲያብብ በቁርጠኝነት እንደምትሰራም አረጋግጠዋል።
የአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ ያዘጋጀው የመጀመሪያው የፓን አፍሪካዊነት ፎረም በአካዳሚው ተከናውኗል፡፡