African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.51K photos
96 videos
6 files
118 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
🌍 A New Day for the World, Africa, and AFLEX! 🌍

As we prepare to step into 2025, the African Leadership Excellence Academy (AFLEX) is ready to make a difference like never before. Through our transformative Leadership Development Program, we aim to shape the future leaders of Africa and beyond.

Welcome, 2025! 🚀 We are excited to serve you with new ideas and renewed energy. Together, let’s create an impact and build a brighter tomorrow.

#AFLEX #ShapingFutureLeaders #Welcome2025 #LeadershipExcellence
👍8
Empowering Women Leaders!

At AFLEX, we take pride in our dedication to advancing women in leadership. Our #Women_Leadership_Development_Program is thoughtfully designed to address the unique challenges faced by women in leadership roles.

This program goes beyond traditional training by fostering confidence, building resilience, and cultivating a strong sense of self-worth. Through this initiative, we aim to empower women to lead with purpose, authenticity, and impact, shaping a future where diversity and inclusion are at the forefront of leadership.

#AFLEX # WomenIn Leadership #Leadership In Africa # Purposeful Leadership #Empowerment #Leadership Development #Diversity In Leadership #Equality In Leadership #Resilient Leadership #Advancing Women
👍7
የባህልና ስፖርት ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያለው ሚና፣ ተግዳሮቶችና መልካም አጋጣሚዎች በሚል ርዕስ በአፍሌክስ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

ታኅሳስ 22፣ 2017ዓ.ም (ሱሉልታ- አፍሌክስ)- በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እየተሰጠ የሚገኘው አመራሮችን በማብቃት የባህል፣ የስፖርት እና የኪነ ጥበብ ዘርፍ ለሀገር አንድነትና ብልፅግና ያለውን ሚና አጠናክሮ የማስቀጠል ስልጠና በሁለተኛው ቀን ውሎ የባህልና ስፖርት ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያለው ሚና፣ ተግዳሮቶች እና መልካም አጋጣሚዎች በሚል ርዕስ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የስልጠናውን ሰነድ አዳነ ካሴ (ዶ/ር ) ባቀረቡበት ወቅት ኢትዮጵያ የብዝሀ ባህል እና ቋንቋ ባለቤት፤ የልዩ ልዩ ዕይታዊ፣ ትዕይንታዊ እና ሥነ-ፅሁፋዊ እሴቶችም ባለቤት እንደመሆኗ መጠን ለሀገር ኢኮኖሚ ልማት ያለው እምቅ አቅም ከፍተኛ ድርሻ ያለው እና ያልተነካ እምቅ ሀብት ያለበት ዘርፍ ነው። በቀጣይም መንግስት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በሰጠው ትኩረት ልክ ዘርፉ ለዚህ ዕቅድ ስኬት የዕቅዱ አካል አድርጎ ሊሠራ ይገባል ብለዋል።

አክለውም በስፖርት ዘርፉም ልዩ የሆኑ ባህላዊ ስፖርቶች መገኛ ከመሆኗም ባሻገር ዘመናዊ ስፖርቶች የሚከናወኑባት እና ስፖርት ወዳድ የሆነ ህዝብ ያለባት ሀገር እንደመሆኗ ይህንን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም የኢኮኖሚ ምንጭ ማድረግ ይገባል።

ሙሉጌታ ጌጡ (ዶ/ር) በበኩላቸው ብሔራዊ የህግ ማዕቀፎችና ዘርፉ ለኢኮኖሚ ያለው አስተዋፅኦ ከሀገሪቱ የልማት ዕቅድ አኳያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የባህል፣ የስፖርት እና የኪነ ጥበብ ዘርፍን በህግ ማቀፍ ከህገ መንግስት፣ ከስትራቴጂክ ፖሊሲ፣ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ የየዘርፉ ፖሊሲዎችንና ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች አንፃር ገለፃ አድርገዋል።
👍9
ሙሉጌታ ጌጡ (ዶ/ር) የስልጠናውን ዓላማ ሲያብራሩ፦ ህጎች የተቋማት ግብ ተገማች ለማድረግ፤ ለባለድርሻ አካላት መተማመኛን ለመፍጠር፤ ለሚፈለገው ግብ መዳረሻ መሳሪያ እንዲሆን፤ ቅንጅታዊ አሰራርን ለማሳለጥ፤ ለተለያዩ አካላት ሚናና ኃላፊነት ለመደልደል የሚያግዝ መሣሪያ ነው ብለዋል።

የባህል፣ ስፖርት እና የኪነ ጥበብ ዘርፍ የሀገሪቱን ህጎች የተቋሙን ፖሊሲዎች መመሪያዎችን እና ዓለማ አቀፋዊ ተሞክሮዎችን በመቀመር ለ17ቱ የሀገሪቱ የዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት ጠንክሮ መስራት ይገባል ብለዋል።
👍7
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጥቂት ሰዎች ሃገር ይቀይራሉ!

"ሁላችንም በአንዴ ሃብታም ልንሆን አንችልም። ነገር ግን ከህዝባችን መካከል ጥቂቱ እንኳን ስኬታማ ስራ ፈጣሪ መሆን ከቻለ ኢትዮጵያ የመለወጥ እድሏ ሰፊ ነው።
ችግሩ ጥቂቶች እንኳን ስኬታማ የሚሆኑበትን እድል የሚፈጥር ሃገራዊ ስነ-ምህዳር አለን ወይ ነው?"

አቶ ዛዲግ አብርሃ የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
#AFLEX
👍14
#የአካል_ብቃት_እንቅስቃሴ_በአፍሌክስ

ታህሳስ 23፣ 2017ዓ.ም (ሱሉልታ- ኤፍሌክስ)

ብቁ፣ ንቁ እና አሸናፊ ትውልድን ለመፍጠር የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ልማድ ማድረግ አስፈላጊ ነው።

ዛሬ ማለዳ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተከናውኗል።

የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ባህል በማድረግ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች እራሳችንን እንጠብቅ።
👍7