African Leadership Excellence Academy
2.33K subscribers
2.52K photos
96 videos
6 files
118 links
የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ሰላም ዲሞክራሲና ልማት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና ካላቸው ወሳኝ አካላት አንዱ አሰተማማኝ አቅም ያለው አመራር መኖር በመሆኑ፤ ተከታታይና ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት በሁለም ደረጃ ማካሄድ አስፈሊጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በንድፈ-ኃ
Download Telegram
የዲፕሎማሲ ስራ ንቃት ዝግጁነትና ብልሃትን የሚጠይቅ መሆኑን በመጠቆም ኢትዮጵያ መርህን መሰረት ያደረገ የዲፕሎማሲ ስልት በመከተል ስኬታማ ስራ ማከናወኗን አስታውቀዋል።
በዚህ ረገድ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ማህበራዊ ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ለዚህም ሰልጣኞች ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ሰልጣኞች የጉባኤውን ትልቅነት ተገንዝበው በፍጹም አገራዊ ስሜት የተጣለባቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ አሳስበዋል።
መሪዎች የሚኖራቸው ቆይታ ስኬታማ እንዲሆን በተግባር እና በንድፈ ሀሳብ የተሰጡ ስልጠናዎችን ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን በአይበገሬ ህዝቦቿ ያስከበረች የአኩሪ ታሪክ ባለቤት መሆኗን የጠቀሱት ሚኒስትሩ እነዚህን ወረቶች በሚገባ መጠቀም ይገባል ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ በበኩላቸው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤን ከፍ ባለ ሁኔታ ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
የተሰጠው ስልጠና ጉባዔውን በተሳካ መልኩ ለማካሄድ ያለመ መሆኑን ጠቁመው ለካዴቶቹ ከ 10 በላይ በሆኑ ርእሰ ጉዳዮች የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል።
ስልጠናው በታቀደለት መልኩ መከናወኑን ገልጸው ስኬታማ እንዲሆን ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
ካዴቶቹ ያገኙት ስልጠና ለጉባኤው ብቻ ሳይሆን ለእለት ተእለት ስራዎችም ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል።
👍10
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሀሳብ የሃይል ምንጭ ነው!

ኤሎን ማስክን ከስደተኝነት አሜሪካን ወደመቆጣጠር ያሸጋገረው የሃሳብ ሃይል።

የአፍሌክስ ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ እንዲህ ይላሉ!
#The_power_of_idea
#AFLEX
👍14
ታኀሳስ 21፣2017 ዓ.ም (ሱሉልታ - አፍሌክስ ):- የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አመራሮችን በማብቃት የባህል የስፖርትና የኪነጥበብ ዘርፍ ለሀገር አንድነትና ብልፅግና ያለውን ሚና አጠናክሮ ለማስቀጠል በአፍሌክስ ስልጠና መስጠት ጀመረ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሸዊት ሻንካ የስልጠናውን ማስጀመሪያ መርሀ ግብር አስመልክቶ ንግግር አድርገዋል።
ክብርት ሸዊት ሻንካ እንደተናገሩት በዓለም ላይ ባህል፣ ኪነጥበብ፣ ፈጠራ እና ስፖርት ሕዝቦችን በማስተሳሰር፣ ኢኮኖሚ በማመነጨት፣ ለብዙ ሰዎች የሥራ እድልን በመፍጠር፣ ማኅበራዊ ትስስርን እና ትብብርን በማጎልበት የአንድን አገር ጠንካራ መሰረት የሚጥሉ ዘርፎች እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡
መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ሴክተሩ ለሀገር ገፅታ ግንባታ እና ለኢኮኖሚ እድገት ሚያበረክተውን አስተዋኦ ለማበርከት የተሰጠንን ታላቅ ሀገራዊ ሀላፊነት ለመወጣት እንዲህ አይነት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች ለዘርፉ ተዋንያኖች መስጠት ወሳኝ መሆኑን ክብርት ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡
በንግግራቸው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ብቁ አመራሮችን ማፍራት የሚያስችል መሰረተ ልማት እንዲሁም ብቁ አመራር እና ባለሞያዎች ያሉት ሃገራዊ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው፤ የሚሰጡ ስልጠናዎችም አሁን ያለንበት ደረጃ እና የወደፊት አዝማሚያዎችን ለማሟላት ታስበው የተዘጋጁ በመሆናቸው የስልጠናው ተሳታፊዎች በቆይታችሁ ተፈላጊውን ችሎታ በመቅሰም ከምትሠሩት የዕለት ከዕለት ተግባር ጋር በማዛመድ ተግባራዊ ልታደርጉ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ የአመራር ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ መሰረት ደስታ በመክፈቻ ስነ ስርዐቱ ላይ ተገኝተው ስለአካዳሚው ገለጻ አድርገዋል።
👍14
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከአፍሪካ አመራር ልህቀት ማዕከል ጋር በመተባበር እየሰጠ ባለው ስለጠና ላይ ባህል፣ ስፖርት እና ኪነጥበብ ለማህበረሰብ አንድነት እና ለሀገር ግንባታ ያለው ፋይዳ፣ ታሪካዊና ስልታዊ አመለካከቶች ፣ብሔራዊ የህግ እና የፖሊሲ ማዕቀፎች ለኢኮኖሚ ያለው አስተዋፅኦ ከአገራችን የልማት እቅድ አኳያ፣ስልታዊ ችግር አፈታት እና ውሳኔ አሰጣጥ እንዲሁም የአመራር አስተሳሰብ እና ዘላቂነት ለዘላቂ ተጵእኖ አስተሳሰብን ማሳደግ የሚሉት የስልጠናው ይዘቶች ናቸው።
በስልጠናው የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች፣ የተጠሪ ተቋማቱ ዳይሬክተሮች፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር የባህልና ስፖርት ቢሮ ሃላፊዎች የስልጠናው ተሳታፊዎች ናቸው።
👍9
"አፍሌክስ ነባር እና ተተኪ የአፍሪካ አመራሮች በጋራ ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ የሚያበጁበት ተቋም ነው።" ወ/ሮ መሰረት ደስታ የአፍሌክስ የአመራር ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ
አፍሌክስ ለባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች ስልጠና መስጠት ጀመረ
ታኅሣሥ 21/2017 (ሱሉልታ - አፍሌክስ):- የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ከ300 በላይ ለሚሆኑ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች የአመራር ልማት መስጠት ጀምሯል።
ስልጠናው የአመራሩን ብቃት በማጠናከር ኪነ ጥበብ፣ ባህል፣ እና ስፖርት ለሃገር አንድነት እና ብልጽግና ያላቸውን ሚና አጠናክሮ ለማስቀጠል ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
በመክፈቻ ስነ ስርዐቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የአፍሌክስ የአመራር ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ ወ/ሮ መሰረት ደስታ "አፍሌክስ ነባር እና ተተኪ የአፍሪካ አመራሮች በጋራ ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ የሚያበጁበት ተቋም ነው።" ብለዋል።
አያይዘውም "አፍሌክስ በሚሰጣቸው ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች ውስጥ የመንግስት ተቋማትን አመራሮችን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፣ ይህ ስልጠናም የዚሁ አካል ነው።" ሲሉ ገልጸዋል።
የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በዚሁ የመክፈቻ ስነስርዐት ላይ ባደረጉት ንግግር "አፍሌክስ ብቁ አመራሮችን ማፍራት የሚያስችል መሰረተ ልማት እንዲሁም ብቁ አመራር እና ባለሞያዎች ያሉት ሃገራዊ ተቋም ነው።" ብለዋል።
አፍሌክስ በኢትዮጵያ የመንግስት ተቋማት አመራሮችን ብቃት ለማሳደግ አቅዶ ብሰፊው እየሰራ ይገኛል።
👍12
More conferences
AFLEX is gearing up for an amazing year ahead, focused on hosting impactful conferences across various sectors in Africa!
What to Expect⁉️
• Diverse Conferences: We will host engaging events featuring leaders from all levels - existing, emerging, women, executives. and others.
-This diversity will create a vibrant platform for sharing innovative ideas.
• Sululta as an Idea Hub: By bringing together diverse voices and perspectives, we aim to establish Sululta, Ethiopia, as an idea hub for Africa, akin to Davos in Switzerland. #This vision strengthens our commitment to making Ethiopia a premier host for global conferences, enhancing its reputation on the international stage. 🏛
Sululta Davos Project
👍10
• Networking and Problem-Solving: Our conferences will not only foster invaluable networking opportunities but also focus on collaborative problem-solving and idea generation.
-Together, we’ll tackle challenges and create actionable solutions.🤝
Your thoughts always matter!
👉What challenges do you think are most pressing in our communities, and what solutions would you like to see discussed?
#AFLEX #2025 #
👍8
የኢቢሲ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተገኝተው ኪነ ጥበብ፣ ባህል እና ስፖርት ለሃገረ መንግስት ግንባታ በሚኖራቸው ሚና ዙሪያ ለከፌዴራል፤ ከክልሎችና ከሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች ለመጡ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች ገለጻ አድርገዋል።

በገለጻቸውም "ሃገር ለመገንባት በቅድሚያ የጋራ ህልም፣ ቀጥሎ ህልምን የሚያሳኩ ተቋማትን መገንባት ያስፈልጋል!" ሲሉ ተናግረው ኪነ ጥበብ፣ ባህል እና ስፖርት የጋራ ትርክት ለመፍጠር ቁልፎ መሳሪያዎች ናቸው ብለዋል።
👍11
"አፍሌክስ ብቁ አመራሮችን ማፍራት የሚያስችል መሰረተ ልማት እንዲሁም ብቁ አመራር እና ባለሞያዎች ያሉት ሃገራዊ ተቋም ነው።" ክብርት ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር።
👍7
Strong policies create strong nations. 🌍

The leaders who focus on inclusive and innovative policies leave a lasting legacy.

If you were to draft one policy to improve your community, what would it be?

#AFLEX #LeadershipDevelopment #FutureLeaders #EmergingLeaders #YouthEmpowerment #PurpuosefulLeadership
#AfricaRising #MakeADifference #LeadershipInAfrica #Empowerment #AfricanLeadership #Impact
#PolicyForChange #InnovationMatters
👍6
Limited-time offer: "Join the AFLEX Community by signing up today and be one of the first 100 members to receive exclusive benefits!"
👍8
"አፍሌክስ ነባር እና ተተኪ የአፍሪካ አመራሮች በጋራ ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ የሚያበጁበት ተቋም ነው።"

ወ/ሮ መሰረት ደስታ የአፍሌክስ የአመራር ልማት ዘርፍ ምክትል ርዕሰ አካዳሚ
👍7
🌍 A New Day for the World, Africa, and AFLEX! 🌍

As we prepare to step into 2025, the African Leadership Excellence Academy (AFLEX) is ready to make a difference like never before. Through our transformative Leadership Development Program, we aim to shape the future leaders of Africa and beyond.

Welcome, 2025! 🚀 We are excited to serve you with new ideas and renewed energy. Together, let’s create an impact and build a brighter tomorrow.

#AFLEX #ShapingFutureLeaders #Welcome2025 #LeadershipExcellence
👍8
Empowering Women Leaders!

At AFLEX, we take pride in our dedication to advancing women in leadership. Our #Women_Leadership_Development_Program is thoughtfully designed to address the unique challenges faced by women in leadership roles.

This program goes beyond traditional training by fostering confidence, building resilience, and cultivating a strong sense of self-worth. Through this initiative, we aim to empower women to lead with purpose, authenticity, and impact, shaping a future where diversity and inclusion are at the forefront of leadership.

#AFLEX # WomenIn Leadership #Leadership In Africa # Purposeful Leadership #Empowerment #Leadership Development #Diversity In Leadership #Equality In Leadership #Resilient Leadership #Advancing Women
👍7
የባህልና ስፖርት ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያለው ሚና፣ ተግዳሮቶችና መልካም አጋጣሚዎች በሚል ርዕስ በአፍሌክስ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

ታኅሳስ 22፣ 2017ዓ.ም (ሱሉልታ- አፍሌክስ)- በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እየተሰጠ የሚገኘው አመራሮችን በማብቃት የባህል፣ የስፖርት እና የኪነ ጥበብ ዘርፍ ለሀገር አንድነትና ብልፅግና ያለውን ሚና አጠናክሮ የማስቀጠል ስልጠና በሁለተኛው ቀን ውሎ የባህልና ስፖርት ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያለው ሚና፣ ተግዳሮቶች እና መልካም አጋጣሚዎች በሚል ርዕስ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የስልጠናውን ሰነድ አዳነ ካሴ (ዶ/ር ) ባቀረቡበት ወቅት ኢትዮጵያ የብዝሀ ባህል እና ቋንቋ ባለቤት፤ የልዩ ልዩ ዕይታዊ፣ ትዕይንታዊ እና ሥነ-ፅሁፋዊ እሴቶችም ባለቤት እንደመሆኗ መጠን ለሀገር ኢኮኖሚ ልማት ያለው እምቅ አቅም ከፍተኛ ድርሻ ያለው እና ያልተነካ እምቅ ሀብት ያለበት ዘርፍ ነው። በቀጣይም መንግስት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በሰጠው ትኩረት ልክ ዘርፉ ለዚህ ዕቅድ ስኬት የዕቅዱ አካል አድርጎ ሊሠራ ይገባል ብለዋል።

አክለውም በስፖርት ዘርፉም ልዩ የሆኑ ባህላዊ ስፖርቶች መገኛ ከመሆኗም ባሻገር ዘመናዊ ስፖርቶች የሚከናወኑባት እና ስፖርት ወዳድ የሆነ ህዝብ ያለባት ሀገር እንደመሆኗ ይህንን ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም የኢኮኖሚ ምንጭ ማድረግ ይገባል።

ሙሉጌታ ጌጡ (ዶ/ር) በበኩላቸው ብሔራዊ የህግ ማዕቀፎችና ዘርፉ ለኢኮኖሚ ያለው አስተዋፅኦ ከሀገሪቱ የልማት ዕቅድ አኳያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የባህል፣ የስፖርት እና የኪነ ጥበብ ዘርፍን በህግ ማቀፍ ከህገ መንግስት፣ ከስትራቴጂክ ፖሊሲ፣ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ የየዘርፉ ፖሊሲዎችንና ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች አንፃር ገለፃ አድርገዋል።
👍9