የአፍሪካ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን መቅረጽ ከአፍሪካውያን ጋር እንደ ድልድይ ሆኖ የሚያገናኝ ስትራቴጂ እንደሆነ ስለታመነበት፤ አካዳሚው አራት ጠቅላላ (General LDP) (Executive Level Leadership Development Program, Emerging Leaders Development Program, Women Leadership Development Program and Public Leadership Development Program) እና ሰላሳ ስምንት ልዩ (Specialized LDP) የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ለይቶ ወደ ስራ ገብቷል። እነዚህ የአመራር ልማት ፕሮግራሞች በአፍሪካ ውስጥ ለሚገኙ አመራሮች በሙሉ የሚሰጡ ሲሆኑ፤ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የአፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች ገለጻ ተደርጎላቸው የተገኘው ግብረ መልስ የሚያመላክተው ፕሮግራሞቹ ለአህጉሪቷ አመራሮች አቅም ግንባታ የሚኖራቸው ጥቅም የጎላ እንደሆነ ነው።
አፍሌክስ የጀመራቸው የሪፎርም፤ የማስፋት እና የሽግግር ስራዎች አፍሪካውያንን ወደ አንድ ጥላ የሚያሰባስቡ፤ ስብራትን የሚጠግኑ፤ እና የጋራ አፍሪካዊ ትርክትን ለመፍጠር የሚያግዙ እንደሆኑም ይታመናል።
አፍሌክስ የጀመራቸው የሪፎርም፤ የማስፋት እና የሽግግር ስራዎች አፍሪካውያንን ወደ አንድ ጥላ የሚያሰባስቡ፤ ስብራትን የሚጠግኑ፤ እና የጋራ አፍሪካዊ ትርክትን ለመፍጠር የሚያግዙ እንደሆኑም ይታመናል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰላም እና ደህንነት ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ለሆኑት ፋና ገብረሰንበት (ዶ/ር) ስለ አፍሌክስ የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ገለጻ ተደረገላቸው::
ገለፃውን ያደረጉት አቶ መስፍን በሀይሉ በአካዳሚው የሴቶች አመራር ልማት ፕሮግራም ፕሮጀክት ሀላፊ ሲሆኑ አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እንደገባ እና ለስምንቱ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ስምንት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ለሀገራችን እና ለአፍሪካ መሪዎች እንደተቀረጸ ገልፀዋል።
ፋና ገብረሰንበት (ዶ/ር) ለተደረገላቸው ገለፃ አመስግነው ኢንስቲትዩቱ ከአፍሌክስ ጋር በቅንጅት ሊሰራ የሚችልባቸው መስኮች እንዳሉ ገልጸዋል:: በተለይም አካዳሚው ለአፍሪካውያን ከሚከፍታቸው ሶስት ትምህርት ቤቶች ጋር በተያያዘ በትብብር መስራት የሚቻልባቸው መንገዶች እንዳሉ ጠቁመው በቀጣይ በሚኖሩ ውይይቶች የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የአፍሌክስ ሪፎርም ማስፋት እና ሽግግር እንዲሳካ ኢንስቲትዩቱ ያግዛል ብለዋል::
ገለፃውን ያደረጉት አቶ መስፍን በሀይሉ በአካዳሚው የሴቶች አመራር ልማት ፕሮግራም ፕሮጀክት ሀላፊ ሲሆኑ አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እንደገባ እና ለስምንቱ ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነ ጠቅሰው አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ስምንት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ለሀገራችን እና ለአፍሪካ መሪዎች እንደተቀረጸ ገልፀዋል።
ፋና ገብረሰንበት (ዶ/ር) ለተደረገላቸው ገለፃ አመስግነው ኢንስቲትዩቱ ከአፍሌክስ ጋር በቅንጅት ሊሰራ የሚችልባቸው መስኮች እንዳሉ ገልጸዋል:: በተለይም አካዳሚው ለአፍሪካውያን ከሚከፍታቸው ሶስት ትምህርት ቤቶች ጋር በተያያዘ በትብብር መስራት የሚቻልባቸው መንገዶች እንዳሉ ጠቁመው በቀጣይ በሚኖሩ ውይይቶች የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የአፍሌክስ ሪፎርም ማስፋት እና ሽግግር እንዲሳካ ኢንስቲትዩቱ ያግዛል ብለዋል::
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ እና የአሜሪካ ኤምባሲ በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከአሜሪካ ምክትል አምባሳደር GWENDOLYN “WENDY” GREEN, Deputy Chief of Mission እና ከባህል ጉዳዮች ሀላፊ RYAN BRADEEN, Cultural Affairs Officer ጋር ተወያይተዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ በውይይቱ ላይ ስለ አፍሌክስ ሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ገለጻ አድርገዋል።
የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን መሪዎች አቅም ለመገንባት እና ተተኪ አመራሮችን ለማፍራት አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እንደገባ የጠቀሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት ስርዓት በመዘርጋት ሂደት ውስጥ የአሜሪካ መንግስት ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በተለይም በሁሉን አቀፍ የአመራር ስርዓት ፕሮግራም ቀረጻ፤ በአፍሪካ የአመራር ልማት እና ትምህርት ፕሮግራሞች ትግበራ፤ እንዲሁም አፍሌክስ ራሱን ለመላው ዓለም እንዲያስተዋውቅ የሚረዱ የብራንዲንግ እና የኮሙዩኒኬሽን ስትራቴጂ ቀረጻዎች ላይ ኤምባሲው የቴክኒክ እና የመሰረተ ልማት ድጋፍ እንዲያደርግ ግብዣ አቅርበዋል።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከአሜሪካ ምክትል አምባሳደር GWENDOLYN “WENDY” GREEN, Deputy Chief of Mission እና ከባህል ጉዳዮች ሀላፊ RYAN BRADEEN, Cultural Affairs Officer ጋር ተወያይተዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ በውይይቱ ላይ ስለ አፍሌክስ ሪፎርም፤ ማስፋት እና ሽግግር ገለጻ አድርገዋል።
የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን መሪዎች አቅም ለመገንባት እና ተተኪ አመራሮችን ለማፍራት አፍሌክስ አስራ ሶስት ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ወደ ስራ እንደገባ የጠቀሱት ርዕሰ አካዳሚው፤ ሁሉን አቀፍ የአመራር ልማት ስርዓት በመዘርጋት ሂደት ውስጥ የአሜሪካ መንግስት ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በተለይም በሁሉን አቀፍ የአመራር ስርዓት ፕሮግራም ቀረጻ፤ በአፍሪካ የአመራር ልማት እና ትምህርት ፕሮግራሞች ትግበራ፤ እንዲሁም አፍሌክስ ራሱን ለመላው ዓለም እንዲያስተዋውቅ የሚረዱ የብራንዲንግ እና የኮሙዩኒኬሽን ስትራቴጂ ቀረጻዎች ላይ ኤምባሲው የቴክኒክ እና የመሰረተ ልማት ድጋፍ እንዲያደርግ ግብዣ አቅርበዋል።
ምክትል አምባሳደሯ GWENDOLYN “WENDY” GREEN, Deputy Chief of Mission በበኩላቸው ከአፍሌክስ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ መስኮች መኖራቸውን ጠቁመው፤ በተለይም በአሜሪካን ሀገር ከሚገኙ የስልጠና እና የትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን የአካዳሚውን የአመራር ልማት ፕሮግራሞች መደገፍ እንደሚቻል ተናግረዋል።
በአሜሪካ ኤምባሲ የባህል ጉዳዮች ሀላፊ RYAN BRADEEN, Cultural Affairs Officer እንደገለጹት አፍሌክስ ሊሰራ ባቀዳቸው ፕሮጀክቶች ዙሪያ በአሜሪካን ሀገር ከፍተኛ አቅም እና ልምድ ያላቸው ተቋማት እንዳሉ ጠቅሰው፤ ወደ ፊት በሚደረጉ ውይይቶች ላይ በዝርዝር በመነጋገር የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን መደገፍ ይቻላል ብለዋል።
ምክትል አምባሳደሯ GWENDOLYN “WENDY” GREEN, Deputy Chief of Mission የአሜሪካው አምባሳደር Ervin Massinga ባጋጠማቸው አስቸኳይ ስራ ምክንያት በውይይቱ ላይ ባለመገኘታቸውም ይቅርታ ጠይቀዋል።
በአሜሪካ ኤምባሲ የባህል ጉዳዮች ሀላፊ RYAN BRADEEN, Cultural Affairs Officer እንደገለጹት አፍሌክስ ሊሰራ ባቀዳቸው ፕሮጀክቶች ዙሪያ በአሜሪካን ሀገር ከፍተኛ አቅም እና ልምድ ያላቸው ተቋማት እንዳሉ ጠቅሰው፤ ወደ ፊት በሚደረጉ ውይይቶች ላይ በዝርዝር በመነጋገር የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚን መደገፍ ይቻላል ብለዋል።
ምክትል አምባሳደሯ GWENDOLYN “WENDY” GREEN, Deputy Chief of Mission የአሜሪካው አምባሳደር Ervin Massinga ባጋጠማቸው አስቸኳይ ስራ ምክንያት በውይይቱ ላይ ባለመገኘታቸውም ይቅርታ ጠይቀዋል።
አቶ ዛዲግ አብርሃ ከ UNIDO ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር ተወያዩ።
ርዕሰ አካዳሚው የተወያዩት ከአኡሬሊአ ፓትሪዚአ (Aurelia Patrizia Calabro, UNIDO Representative and Director of the Regional Office) እና አሰግድ አዳነ የ UNIDO ምክትል ተወካይ (Deputy UNIDO Representative) ጋር ነው ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከከፍተኛ የስረ ሃላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል።
ርዕሰ አካዳሚው አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተለይም ልዩ የኢንዱስትሪ አመራር ልማት ፕሮግራም መቀረጹን የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ከUNIDO ጋር በመሆን የኢንዱስትሪውን ዘርፍ አመራር ለማብቃት እንሰራለን ብለዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም UNIDO በአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቀረጻ፤ በአፍሌክስ አመራር ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ግንባታ ላይ ከአፍሌክስ ጋር አብሮ እንዲሰራ ግብዣ አቅርበዋል።
ርዕሰ አካዳሚው የተወያዩት ከአኡሬሊአ ፓትሪዚአ (Aurelia Patrizia Calabro, UNIDO Representative and Director of the Regional Office) እና አሰግድ አዳነ የ UNIDO ምክትል ተወካይ (Deputy UNIDO Representative) ጋር ነው ።
የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ ከከፍተኛ የስረ ሃላፊዎች ጋር በአፍሌክስ ሪፎርም፤ ሽግግር እና ማስፋት ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የአካዳሚውን የሪፎርም (Reform)፤ የማስፋት (Scaling Up) እና የሽግግር (Transformation) ስራዎች ለሀላፊዎቹ አብራርተዋል።
ርዕሰ አካዳሚው አቶ ዛዲግ በገለጻቸው ላይ እንዳብራሩት አካዳሚው ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካውያን የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ እንደሆነ እና ይህንን ዓላማውን ለማሳካትም አራት የጠቅላላ እና ሰላሳ ሰባት ልዩ የአመራር ልማት ፕሮግራሞችን ቀርጾ በሶሰት ዓመት ውስጥ ለመፈጸም እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተለይም ልዩ የኢንዱስትሪ አመራር ልማት ፕሮግራም መቀረጹን የጠቀሱት አቶ ዛዲግ ከUNIDO ጋር በመሆን የኢንዱስትሪውን ዘርፍ አመራር ለማብቃት እንሰራለን ብለዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም UNIDO በአመራር ልማት ፕሮግራሞች ቀረጻ፤ በአፍሌክስ አመራር ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ግንባታ ላይ ከአፍሌክስ ጋር አብሮ እንዲሰራ ግብዣ አቅርበዋል።
አኡሬሊአ ፓትሪዚአ (Aurelia Patrizia Calabro, UNIDO Representative and Director of the Regional Office) በበኩላቸው በኢንዱስትሪ አመራር ልማት ፕሮግራም፤ በአፍሌክስ ሽልማት እና በሀሳብ ማመንጫ ማዕከላት ላይ የአፍሌክስ ፕሮጀክቶችን በቴክኒክ እና በባለሙያ መደገፍ እንደሚቻል ገልጸው፤ ለዚሁ የሚረዳ ዝርዝር ሀሳቦችን የሚያሳይ ፕሮፖዛል ለ UNIDO እንዲቀርብ ጠይቀዋል።
ዝርዝር የድጋፍ እና እገዛ ፍላጎቶችን የሚገልጽ ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ለ UNIDO እንዲቀርብ በመስማማትም ውይይቱ ተጠናቋል።
ዝርዝር የድጋፍ እና እገዛ ፍላጎቶችን የሚገልጽ ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ለ UNIDO እንዲቀርብ በመስማማትም ውይይቱ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን የሰባ አምስት ዓመታት ስኬታማ ጉዞ የሚያሳይ የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ምርምር ሪፖርት ቀረበ። ጥናቱን ያካሔደው የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ሲሆን የአየር መንገዱ ስራ አመራር አባላት ተገኝተው ሪፖርቱን ገምግመዋል።
የጥናቱ ዋና ዓላማም የአየር መንገዱን የስኬት ምስጢር በሳይንሳዊ ጥናት እና ምርምር ማረጋገጥና ለሌሎች ተቋማት እንደ ግብዓት የሚሆን የጥናት ሪፖርት ማቅረብ እንደሆነ በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ ተመላክቷል።
የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ሪፖርት ሲገመገም በመድረኩ የተገኙት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ታሪክ ለሀገራችን ስኬታማ ጉዞ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቀላል እንዳልሆነ ጠቅሰው፤ አካዳሚው እንደ ኬዝ ጥናት ወስዶ ማጥናቱ ለአመራር ልማት ፕሮግራሞቹ ግብዓት ከመሆኑም በላይ ለሌሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት የስኬት መንገድ ማሳያ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም የተገኘው የጥናት ውጤት እንዴት እንደሚሰፋ እና በስራ ላይ እንደሚውል ሀሳብ የሰጡ ሲሆን፤ ከመድረኩ የተገኘውን ግብዓት በማካተት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ባለድርሻ አካላት ሊጠቀሙበት የሚችል ውጤታማና ተግባራዊ የጥናት ውጤት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የጥናቱ ዋና ዓላማም የአየር መንገዱን የስኬት ምስጢር በሳይንሳዊ ጥናት እና ምርምር ማረጋገጥና ለሌሎች ተቋማት እንደ ግብዓት የሚሆን የጥናት ሪፖርት ማቅረብ እንደሆነ በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ ተመላክቷል።
የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ሪፖርት ሲገመገም በመድረኩ የተገኙት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስኬት ታሪክ ለሀገራችን ስኬታማ ጉዞ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ቀላል እንዳልሆነ ጠቅሰው፤ አካዳሚው እንደ ኬዝ ጥናት ወስዶ ማጥናቱ ለአመራር ልማት ፕሮግራሞቹ ግብዓት ከመሆኑም በላይ ለሌሎች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት የስኬት መንገድ ማሳያ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
አቶ ዛዲግ አያይዘውም የተገኘው የጥናት ውጤት እንዴት እንደሚሰፋ እና በስራ ላይ እንደሚውል ሀሳብ የሰጡ ሲሆን፤ ከመድረኩ የተገኘውን ግብዓት በማካተት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ባለድርሻ አካላት ሊጠቀሙበት የሚችል ውጤታማና ተግባራዊ የጥናት ውጤት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ሪፖርት የተቀመጠለትን ግብ ማሳካቱን እና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መሰራቱን አረጋግጠው፤ ጥናቱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለባለድርሻ አካላት የሚኖረውን ጥቅም ከግምት በማስገባት የተሰጡትን ሀሳቦች እና አስተያየቶች አካቶ ስራ ላይ ቢውል ለተቋም ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
በመድረኩ የተሳተፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀድሞ ዋና ስራ አስፈጻሚዎች፤ የቀድሞ የቦርድ አመራሮች፤ የማኔጅመንት አባላት እና የአፍሌክስ አመራሮች በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ አስተያየት እና ሀሳብ የሰጡ ሲሆን የተሰጡትን ግብዓቶች በማካተት የመጨረሻ የጥናት ሪፖርት እንደሚቀርብም ለማወቅ ተችሏል።
በመድረኩ የተሳተፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀድሞ ዋና ስራ አስፈጻሚዎች፤ የቀድሞ የቦርድ አመራሮች፤ የማኔጅመንት አባላት እና የአፍሌክስ አመራሮች በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ላይ አስተያየት እና ሀሳብ የሰጡ ሲሆን የተሰጡትን ግብዓቶች በማካተት የመጨረሻ የጥናት ሪፖርት እንደሚቀርብም ለማወቅ ተችሏል።
የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ መፅሐፍ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት በአብርሆት ቤተ መፅሐፍት እየተደረገ ይገኛል
**********
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ" የተሰኘ መፅሐፍ የምረቃ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተደረገ ይገኛል።
መፅሐፉ ለኢትዮጵያ ህልውና ከፍተኛ ሚና ባላቸው የዓባይ ወንዝ እና ቀይ ባሕር ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን፤ በስድስት ምዕራፎችም የተከፋፈለ ነው።
መፅሐፉ የዓባይ ተፋሰስ እና የባሕር በር ጉዳይ ዐቢይ ስትራቴጂ አዲስ ዕይታ፣ በዓባይ ተፋሰስ የውኃ ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና መጫወት፣ የሕግና የፖሊሲ ጉዳዮች እንዲሁም ስለ ባሕር በር የዓለም አቀፍ ሕግ፣ የሀገራት ተሞክሮ እና የባሕር በር ታሪካችን በስፋት ተዳሰውበታል።
የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ መፅሐፍ በሁለቱ የውኃ አካላት ላይ ጥቅሞቻችን፣ ልንከተላቸው የሚገቡ መርሆችና ስትራቴጂዎችም ተካተውበታል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በመፅሃፉ ላይ ዳሰሳ አቅርበዋል::
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይየመንግስት ኃላፊዎችና አመራሮች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ ጋዜጠኞች እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተዋል።
**********
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ከዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት "የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ" የተሰኘ መፅሐፍ የምረቃ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት እየተደረገ ይገኛል።
መፅሐፉ ለኢትዮጵያ ህልውና ከፍተኛ ሚና ባላቸው የዓባይ ወንዝ እና ቀይ ባሕር ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን፤ በስድስት ምዕራፎችም የተከፋፈለ ነው።
መፅሐፉ የዓባይ ተፋሰስ እና የባሕር በር ጉዳይ ዐቢይ ስትራቴጂ አዲስ ዕይታ፣ በዓባይ ተፋሰስ የውኃ ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና መጫወት፣ የሕግና የፖሊሲ ጉዳዮች እንዲሁም ስለ ባሕር በር የዓለም አቀፍ ሕግ፣ የሀገራት ተሞክሮ እና የባሕር በር ታሪካችን በስፋት ተዳሰውበታል።
የሁለት ውኃዎች ዐቢይ ስትራቴጂ መፅሐፍ በሁለቱ የውኃ አካላት ላይ ጥቅሞቻችን፣ ልንከተላቸው የሚገቡ መርሆችና ስትራቴጂዎችም ተካተውበታል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአፍሌክስ ርዕሰ አካዳሚ አቶ ዛዲግ አብርሃ በመፅሃፉ ላይ ዳሰሳ አቅርበዋል::
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይየመንግስት ኃላፊዎችና አመራሮች፣ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፣ ጋዜጠኞች እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች ተገኝተዋል።