ET Securities
739 subscribers
751 photos
9 videos
34 files
430 links
At ET Securities, our mission goes beyond simply offering financial services. We are dedicated to strengthening Ethiopia’s financial ecosystem by deliveri

Support us https://t.me/boost/Etstocks

www.Etsecurities.com

YouTube.com/@etstocks

Fb.me/etstocks
Download Telegram
May 7
ኢብባ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ፡- የተመዘነ አማካይ ዋጋ በ132.9643 ብር በአንድ ዶላር

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያደርገውን የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ዛሬ ይፋ አድርጓል።

ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው ማስታወቂያ መሠረት በጨረታው አሸናፊ የሆኑት ሁሉም አማካኝ ዋጋ በዶላር 132.9643 ብር ነበር።

በጨረታው የውጪ ምንዛሪ ድልድል ጥያቄዎችን በማቅረብ በአጠቃላይ 16 ባንኮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክም በቀጣይ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የሚካሄድበትን መርሃ ግብር አመልክቷል። የሚቀጥለው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ይካሄዳል።
May 7
May 7
ኤርሚያስ አመልጋን ጨምሮ ህገወጥ የገንዘብ ማሰባሰብ ላይ ምርመራ ተጀመረ - የካፒታል ገበያ ባለስልጣን

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ታዋቂውን ስራ ፈጣሪ አቶ ኤርሚያስ አመልጋን እና "ጀነሲስ ኢንቨስትመንት ሰርቪስ" የተባለ ኩባንያን ጨምሮ ህገወጥ በሆነ መንገድ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮችን ለህዝብ በመሸጥ ገንዘብ ሲያሰባስቡ በነበሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ የቀረቡ ቅሬታዎችን ተቀብሎ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ በሰጠው መግለጫ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ህገወጥ የሰነድ ሽያጭን በመጠቀም ከህዝብ ገንዘብ በማሰባሰብ ተግባር ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ገልጿል።

በተለይም በአቶ ኤርሚያስ አመልጋ እና በ"ጀነሲስ ኢንቨስትመንት ሰርቪስ" ኩባንያ ላይ እየተካሄዱ ያሉት ምርመራዎች በህገ መንግስት የተረጋገጠ የመሰማት እና የመከላከል ሙሉ መብታቸው በተጠበቀ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ባለስልጣኑ አረጋግጧል።

በተጨማሪም ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ከካፒታል ገበያ ጋር በተያያዙ እንቅስቃሴዎች ላይ ሲሳተፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።

በተለይም በንግድ ድርጅቶች ምስረታ ላይ ሲሳተፉ የንግድ ምዝገባ እና ምስረታ ሰነዶችን ከሚመለከተው አካል እንዲያረጋግጡ እንዲሁም ገንዘብ ከመክፈላቸው በፊት በባለስልጣኑ ፈቃድ ከተሰጣቸው የኢንቨስትመንት አማካሪዎች ብቻ ምክር እንዲፈልጉ ጠቁሟል።

ባለስልጣኑ ፈቃድ ሳይኖራቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት የሚሰጡ ወይም ለማቅረብ የሚሞክሩ አካላት ካሉ ለባለስልጣኑ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ በእንደዚህ አይነት ህገ-ወጥ ድርጊቶች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አረጋግጧል።

Source: capitalethiopia
@Etstocks
May 8
May 8
May 8
May 9
May 10
May 15
May 15
የባንኩ ሰው ለይኩን ብርሃኑ  ( ከ1937 - 2017 )

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ጨምሮ በተለያዩ አገራዊ ባንኮች ከገዥነት እስከ ፕሬዚዳንትነት ያገለገሉት የአቶ ለይኩን ብርሃኑ ከአባታቸው ከአቶ ብርሃኑ ገምታ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ጉደቱ አንበቻ  ሰኔ 4 ቀን 1937 ዓ.ም በቀድሞ ወለጋ ክፍለ ሀገር በጊምቢ አውራጃ ተወለዱ።

ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በጊምቢ ደጅአዝማች ገ/እግዚአብሔር አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በቀድሞ አጠራር ነቀምቴ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡

ከዚያም በመቀጠል የከፍተኛ ትምህርታቸውን በቀድሞ አጠራር ኃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሐምሌ ወር 1961 ዓ.ም. በከፍተኛ ውጤት አጠናቀው በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የአቶ ለይኩን ብርሃኑ የሕይወት ታሪካቸው እንደሚያሳየው በሕይወት ዘመናቸው በተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ለ47 ዓመታት በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች አገልግለዋል፡፡

ከጥር 1968 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 1971 ዓ.ም. የቀድሞ የአዲስ ባንክ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ከጥቅምት 1971 ዓ.ም. እስከ 1972 ዓ.ም. ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው አገልግለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ወቅት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እንዲሁም ለባንኪንግ ኢንዱስትሪው እድገት ላደረጉት በጐ ተጽእኖ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ  ማኔጅመንት ሚያዝያ 7 ቀን 2011ዓ.ም. በስማቸው ‘’ለይኩን ብርሃኑ’’ ቅርንጫፍ ከፍቶ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡

አቶ ለይኩን ብርሃኑ ከጥቅምት 1972 ዓ.ም. እስከ ግንቦት 1975 ዓ.ም. የእርሻ ሰብል ገበያ ድርጅት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፣ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ከመጋቢት 1978 ዓ.ም. እስከ መስከረም 1981 ዓ.ም. የትራንስፖርትና ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ ዋና ኃላፊ እንዲሁም ከጥቅምት 1982 እስከ ጥቅምት 1984 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር  በመሆን ኃላፊነታቸውን በብቃት ተወጥተዋል፡፡

አቶ ለይኩን ብርሃኑ በ1983 ዓ.ም. የደርግ መንግሥትን መውደቅ ተከትሎ አገራችን ኢትዮጵያ የተከተለችውን የኢኮኖሚክ ሪፎርም ኘሮግራም ከህዳር 1984 ዓ.ም. እስከ መስከረም 1987 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ በመሆን በአስተባባሪነትና በአስፈጻሚነት ጉልህ ድርሻ አበርክተዋል፡፡ 

በተለይም በደርግ ዘመነ መንግሥት ለ17 ዓመታት ለግሉ ዘርፍ ዝግ ሆኖ የቆየውን የባንክና የኢንሹራንስ ዘርፍ ለግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ክፍት ለማድረግ አዳዲስ ባንኮችና ኢንሹራንሶች እንዲቋቋሙ የባንክና ኢንሹራንስ ሥራ ፈቃድ አዋጆችን በማውጣት በአሁኑ ጊዜ 30 የግል ባንኮች እና 17 የግል ኢንሹራንስ ኩባንያዎች  እንዲቋቋሙ መንገድ የከፈቱና የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጡ መሪ ነበሩ፡፡

አቶ ለይኩን ብርሃኑ በመጨረሻው የሥራ ዘመናቸው ከመጋቢት 1988 ዓ.ም. እስከ ታህሣስ 2003 ዓ.ም. የአዋሽ ባንክ አክሲዮን ማህበር ኘሬዚዳንት በመሆን ባንኩን ከ14 ዓመታት በላይ በኘሬዚዳንትነት አገልግለዋል፡፡ አቶ ለይኩን ብርሃኑ በተወለዱ በ80 ዓመታቸው ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም አርፈዋል  ።

የቅዳሜገበያ
@Etstocks
May 15
ኢትዮጵያ በይፋ የአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽንን ተቀላቀለች!

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  አዋጅ
ቁጥር 1379/2017ን
በማፅደቅ ሀገሪቷ ወደ አፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ለመቀላቀል የሚያስችላትን ውሣኔ አሳልፏል።

ማንበብ ይቀጥሉ
https://www.2merkato.com/news/alerts/8436-ethiopian-parliament-ratifies-proclamation-to-join-african-finance-corporation
May 15
May 15
ባለፉት 10 ዓመታት ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ (Gross Domestic Product per capital) ከፍተኛ ዕድገት ያስመዘገቡ 10 ምርጥ የአፍሪካ ሀገራት

የነፍስ ወከፍ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ብዙውን ጊዜ ከግለሰብ ገቢ እና ፍጆታ መጨመር ጋር ይዛመዳል። ይህ የሚያሳየው በአማካይ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች ካለፈው አመት በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘታቸውን ነው።

ሌላው የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ ገፅታ ደግሞ የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ የግዢ ሃይል እኩልነት(Purchasing power parity) ሲሆን ይህም በእያንዳንዱ ሰው አማካይ የኢኮኖሚ ውጤትን የሚያመለክት እና በአገሮች ያለውን የኑሮ ውድነት ታሳቢ ያደረገ ነው።

መረጃ ምንጭ - World Economics
May 16
አሜሪካ በሬሚታንስ ላይ ታክስ የመጣል ዕቅድ እንዳላት ተገለፀ።

በዚህ ሳምንት ታክስን በተመለከተ በቀረበው ዕቅድ ላይ በአሜሪካ ከሚኖሩ ሰዎች ወደ ሌላ ሃገር የሚደረጉ ክፍያዎች (ሬሚታንስ) ላይ የ5 በመቶ ተብሎ ታክስ ለመጣል ታቅዷል ተብሏል።

በታክሱ አብዛኞቹ በአሜሪካ ዜጎች የሚፈፀሙ ዝውውሮች ባይካተቱም በሌሎች ሀገር ዜጎች እና አንዳንድ በአሜሪካ ዜጎች የሚላኩ ገንዘቦች ግን ታክሱ ይፈፀምባቸዋል።

በ2023 ብቻ በአሜሪካ የሚኖሩ ሰዎች ከ93 ቢሊየን ዶላር በላይ ሬሚታንስ ወደ ሀገሮቻቸው የላኩ ስለመሆኑ የዓለም ባንክ ሪፖርት ያሳያል።

እንደ ኬንያ፣ ጋና እና ናይጄሪያ ያሉ ብዙ ሬሚታንስ ተቀባይ የሆኑ አፍሪካውያንም በጉዳዩ ስጋት ገብቷቸዋል።

በእነዚህ ሀገራት ሬሚታንስ ከሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዝ ሲሆን ከሬሚታንስ የሚገኘው ገንዘብ አንዳንዴ በእርዳታ እና ኢንቨስትመንት መልኩ ከሚያገኙት ገንዘብ ጭምር እንደሚበልጥም ተነግሯል።

ኢትዮጵያ በ2023/24 ከሬሚታንስ 6 ቢሊየን ዶላር ያገኘች ሲሆን ታክሱ ተግባራዊ ከሆነ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታት ይሆናል።

Source: tikvahethmagazine
@Etstocks
May 16
Ethiopian Securities Exchange (ESX) and IFC - International Finance Corporation ) have made an agreement and officially launched the Ethiopia Money Market Capacity Building Project. The initiative is expected to play a pivotal role in shaping the future of Ethiopia’s capital markets by investing in critical human capital and institutional development.
May 16
May 18