ET Securities
648 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
287 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
የኢትዮጵያ ሠነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያሞሮኮ አክሲዮን ገበያ ጋር የትብብር ስምምነት ፈጸመ!!

የኢትዮጵያ ሠነደ ሙዓለ-ንዋዮች ገበያ ከሞሮኮ ካዛብላንካ አክሲዮን ገበያ ጋር ስትራቴጂካዊ የትብብር ስምምነት መፈራረሙ ተገለፀ።

አላማውም በዋናነት በእውቀት ማጋራት እና ተግባራዊ ድጋፍ መስጠት ላይ የሚያተኩር መሆኑ ተገልጿል።

ደኅንነቱን የጠበቀ እና ቀልጣፋ የንግድ ሥርዓት እንዲፈጥር የቴክኖሎጂ ማዕቀፍን፣ የአሠራር አቅም እና የአደጋ አሥተዳደር አቅምን የሚያጎለብቱ ሥራዎች ለመስራት ያስችላል ተብሏል።

በተጨማሪም ኢንቨስትመንትን እና ዘላቂ እድገትን ለማበረታታት እንደሚያግዝ ተገልጿል፡።
ከታክስ በፊት 930 ሚሊየን ብር ትርፍ አተረፍኩ! – ቡና ባንክ
ከተመሰረተ 15 አመት የሞላው ባንኩ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ትርፉ በ4መቶ29 ሚሊየን ብር ቅናሽ ማሳየቱንም አስታውቋል።

በበጀት አመቱ እንደ አገር የተከሰተው ከፍተኛ የዋጋ ንረት ፣ የውጭ ምንዛሬ ዕጥረት ፣ ተደራራቢ የሆኑ የተቆጣጣሪ አካላት መመሪያዎች መውጣት እንዲሁም ተግባራዊ መሆን ለባንኩ ዘርፍ አስቸጋሪ ሁኔታ እንደነበር ተገልጿል።

የባንኩ የቦርድ ሊቀመንበር አምባሳደር አለማየሁ ሰዋገኝ፤ እነዚህ ችግሮች የባንኮችን የማበደር ብቻ ሳይሆን ተቀማጭ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ ላይም ተፅዕኖ ማሳደራቸውን ተናግረዋል።

ነገርግን ባንኩ ላስመዘገበው የሀብት ዕድገት የተሰጡ የብድር አቅርቦቶች ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙም ገልጸዋል።

በዚህም የባንኩ አጠቃላይ የሀብት መጠን ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ8.14 ቢሊየን ብር ዕድገት በማሳየት 54.53 ቢሊየን ብር መድረሱን አስታውቀዋል።

በበጀት አመቱ የተመዘገበው የባንኩ የተከፈለ ካፒታል ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ549.2 ሚሊየን ብር ጭማሪ በማሳየት ወደ ብር 4.83 ቢሊየን ማደግ ችሏል ነው የተባለው።

ባንኩ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የተቀመጠውን ዝቅተኛ የካፒታል መጠን እንዲሁም የተከፈለ ካፒታል መጠን ከተቀመጠው ጊዜ ቀደም ብሎ ለማሟላት ዕቅድ አውጥቶ እየሰራ መሆኑም ተገልጿል።

ከዕቅዱ አንፃር ዝቅ ያለ ቢሆንም 4መቶ90 ሚሊየን 1መቶ16 ሺህ ብር ለባንኩ ባለአክሲዮኖች በትርፍ ክፍያ እንዲከፋፈል ውሳኔ መደረሱንም ገልፀዋል።

ባንኩ በያዝነው በጀት አመት ሩብ አመት መጀመሪያ ላይ ከዕቅዱ በላይ 1.2 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንም ሰምተናል።

ቡና ባንክ የባለአክሲዮኖች 15ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በማካሄድ ላይ ይገኛል።
ገቢዎች ቢሮ ድርጅቶች ሊኖራቸው የሚገባውን የሰራተኞችን ቁጥር እና ሊከፈል የሚገባውን ዝቅተኛ ደመወዝ ወለል ወሰነ!

በዚህ ውሳኔ በሆቴሎች እና ሌሎች የንግድ ዘርፎች ላይ አሰሪዎች ለሰራተኞቻቸው የደሞዝ ጭማሪ እንዲያደርጉ የሚያስገድድ ተመን ይሆናል።

ከአስተናጋጅ፣ ጥበቃና የፅዳት ሙያ ውጭ ላሉ ሰራተኞች ትንሹ የሚከፍሉት ደመወዝ 5,000 ብር ሆኖ ተተምኗል።

በዚህም የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በግብር  ሂደት  ውስጥ የሚፈጠሩ ማጭበርበሮችን ለመቀነስ ዓላማው ያደረገ ለሆቴሎች፣ ለስጋ ቤቶች፣ ለመጠጥ ቤቶች እና ለተለያዩ የተመረጡ የንግድ ዘርፎች ለሰራተኞቻቸው አነስተኛ የደመወዝ ወለል እና የሰራተኞችን ብዛት የሚተምን ተመን ይፋ አድርጓል።

Source: theethiopianeconomistview
@Etstocks
የውጭ ሀገራት ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ የሚፈቅደው የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ መርምሮ እንደሚያፀድቅ ተገለፀ፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ከተወያየ በኃላ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡

በነገው መደበኛ ስብሰባ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የባንክ ስራ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ ለምክር ቤቱ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ሰኔ 18 ቀን ፣ 2ዐ16 ዓ/ም ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የተመራ ሲሆን ምክር ቤቱ፤ ቋሚ ኮሚቴው የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅም ይጠበቃል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ሲጸድቅ የውጭ ባንኮች በሃገር ውስጥ ተቀጥላ ወይም ሰብሲዲያሪ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲከፍቱ ከመፍቀዱ በተጨማሪም የሀገር ውስጥ ባንኮችን ድርሻ መግዛት እንዲችሉ የሚፈቅድም ነው፡፡

ከዚህም ባሻገር የውጭ ባንኮች ቅርንጫፎቻቸውን እንዲከፍቱ፣ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገራት ዜጎችም በባንኮቻቸው የሥራ እድልን ማግኘትና የቦርድ ሊቀመንበር አባላት እንዲሆኑ መንገዱን የሚያቀናላቸው ነው ይኸው ረቂቅ አዋጅ፡፡

መንግስትም የአዋጁን መጽደቅ ተከትሎ ለአምስት የውጭ ባንኮች ፈቃድ ለመስጠት ያስችለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ገበያ ለመሥራት ፍላጎት ካሳዩ የውጭ ባንኮች ውስጥ የኬንያው ኬሲቢ እንዲሁም ስታንዳርድ ባንኮች ይጠቀሳሉ፡፡
ኦሮሚያ ባንክ አጠቃላይ ሀብቱ ከ 68 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አስታወቀ

ኦሮሚያ ባንክ የተከፈለ ካፒታል 6.5 ቢሊየን ብር መድረሱን ያስታወቀ ሲሆን አጠቃላይ ሀብቱ ደግሞ ወደ 68 ቢሊዮን ብር ማደጉን በሪፖርቱ ገልጿል።

ዘንድሮ አለም አቀፍ እና ሀገራዊ ተግዳሮቶች የባንኪንግ ዘርፉን በተለያየ መልኩ ቢፈትኑትም፣ ኦሮሚያ በንክ ይህን መቋቋም መቻሉን ነዉ በሪፖርቱ የገለፀዉ። ይህን ተከትሎ በተጠናቀቀዉ ሂሳብ ዓመት ከወለድ ነፃ የባንክ ገቢ 56.4 ቢሊዮን ብር መድረጉን አመልከቷል ።

15ኛ የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት ያደረገው ባንኩ ኦሮዲጂታል የተሰኘ ዲጂታል የባንክ አገልግሎት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ2.9 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራት መቻሉን አስታዉቋል።

በዚህም አጠቃላይ የባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር 3.7 ሚሊዮን ከባለፈው ተመሳሳይ የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ157 % እድገት አሳይቷል ብሏል።
የኢትዮጵያ ፓርላማ የውጭ ባንኮች በኢትዮጵያ የሚፈቅደውን ታሪካዊ አዋጅ አፀደቀ።

Read more
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዋጅን አጸደቀ!!

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  በመደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት አድርጓል።

ቋሚ ኮሚቴው የብሄራዊ ባንክ ረቂቅ አዋጅ በተመለከተ ሪፖርት ካቀረበ በኋላ  የውሳኔ ሀሳቡ ላይ ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ ተሰጥቷል።

ስለ ክሪፕቶ ከረንሲ ቁጥጥር ፣ የብድር ዋስትና ፣ ወንጀልን የማጣሪያ የጊዜ ገደብ እና ከመመሪያ ይልቅ ደንብ ቢሆን በሚል የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ አንስተዋል።

የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ የአዋጁን ጠቀሜታ አፅኖት ሰጥተው ለመጀመሪያ ጊዜ የብሔራዊ ባንክን ዋና ስራ በቅደም ተከተል ያስቀመጠ መሆኑን ተናግረዋል ።

አክለውም የብሔራዊ ባንክ አደረጃጀት እና የአመራር ሁኔታ እንዲሁም ባንኩ ከመንግስት ጋር ያለውን ልዩነት በግልፅ ያሰፈር አዋጅ መሆኑን ጠቁመዋል።

የብሔራዊ ባንክ ዋና ተግባር የዋጋ መረጋጋት እንዲኖር ማስቻል፣ የፋይናንስ ስርአቱን ጤናማ እንዲሆን ማድረግ እና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋፅኦ ማድረግ እንደሆነ ገልፀዋል።

ረቂቁ አዋጅ ቁጥር 1359 /2017 በመሆን በሙሉ ድምጽ ጸደቋል፡፡
Siinqee Bank's shareholders voted to establish an investment bank as part of a wider plan to venture into the capital market ecosystem.

Read More

Source: addisfortune
@Etstocks
የኢትዮጲያ ሰነደመዋለንዋይ ገበያ ዲጂታል አካዳሚ መጀመሩን በይፋ አብስሯል።

የኢትዮጲያ ሰነደመዋለንዋይ ገበያ "ESX Academy" የተሰኘውን የመማሪያ ፕላትፎርም ያስተዋወቀ ሲሆን ይህም ከ FSD Ethiopia ጋር በመተባበር  የተሰራ ፕሮጀክት ነው።

መጪው ካፒታል ገበያ ሲጀመር ክፍተት ይሆናል ተብሎ የታሰበውን የፋይናንስ እውቀት ለመቅረፍ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ኢሰገ ገልጿል።

በኢትዮጲያ ካፒታል ገበያ ሰሚት ላይ አቶ ሚካኤል ሃብቴ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ አካዳሚ እንጀምራለን ማለታቸው አይዘነጋም ነበር።

ፕላትፎርሙ የተለያዩ ኮርሶችን አንድላይ የያዘ ሲሆን ከነዚህም፡

1. ካፒታል ገበያ እንዴት ነው ሚሰራው
2. ኢንቨስትመንት ስትራቴጂ
3. ሻሪያን ስላገናዘቡ ምርቶች
4. የኢትዮጲያ ሰነደመዋለንዋይ ገበያ በኢትዮጲያ ኢኮኖሚ ላይ ስላለው ሚናና ያካትታል።

ኮርሶቹን ለመወሰድ esxacademy.com ላይ ገብተው መውሰድ ይችላሉ።
| YouTube | X | TikTok
አዲሱን የባንክ ስራ አዋጅ ከማብራሪያው ጋር እነሆ!!
ገዳ ባንክ ከታክስ በፊት 101 ሚሊዮን ብር ማትረፉ ተገለፀ!!

ገዳ ባንክ የባለ አክሲዮኖች ሶስተኛ መደበኛ ጉባኤውን  ባካሄደበት ወቅት  በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት 101 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አስታውቋል።

በ2016በጀት አመት ያገኘው ገቢ 790 ሚሊዮን ብር  ሲሆን ካለፈው አመት ጋር ሲነፃጸር የ609 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ተገልጿል፡፡

በ 2,88,174 ደንበኞች አጠቃላይ ተቀማጭ የገንዘብ መጠኑ 4 ቢሊዮን  መድረሱም ተጠቁሟል።

ካሉት ደንበኞች የሞባይል ባንኪንግ ተጠቃሚ 42,930 መሆናቸውን ባንኩ አሳውቋል።

በበጀት አመቱ 2.9 ሚሊዮን ብር ብድር መስጠት መቻሉም ተገልጿል፡፡
ዓለም ባንክ፣ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማጠናከር የሚውል የ700 ሚሊዮን ዶላር ብድር አጽድቋል

#Ethiopia  | ከብድሩ 90 በመቶው የንግድ ባንክን ሒሳብ ለማስተካከልና ባንኩን መልሶ ለማዋቀር እንደሚውል ዓለም ባንክ ገልጧል።

ከፊሉ ብድር ለብሄራዊ ባንክና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ማጠናከሪያና መዋቅራዊ ማሻሻያ እንደሚሰጥ ባንኩ ጠቅሷል።

ብድሩ በአራት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚለቀቀው፣ የባንኮቹ አፈጻጸም፣ የደንቦችና የመዋቅሮች ማሻሻያ ሂደት እየታየ የሚለቀቅ ነው።

የብድሩ ዓላማ፣ የአገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ ጠንካራና አስተማማኝ ለማድረግና ተደራሽነቱን ለማስፋት ያለመ እንደኾነም ባንኩ ባሠራጨው አጭር መግለጫ አንስቷል።

https://t.me/etstocks