የሚንስትሮች ምክር ቤት ተጨማሪ 581.9 ቢልዮን ብር በጀት በማፅደቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላልፏል::
ዛሬ በተደርገው የሚንስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ከዚህ በፊት ከፀደቀው 1 ትሪልዮን ብር በተጨማሪ 581.9 ቢሊዮን ብር አፅድቋል።
የተጨማሪ በጀት እና የወጪ አሸፋፈን ማስተካከያው የተሻሻለውን የ2017-2021 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማስፈጸም በሚያስችል መልኩ የመንግስት የፋይናንስ አቅምና ተጠባቂ ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግ፣ የተጨማሪ በጀት ታሳቢዎችንና የወጭ ታሳቢዎችን ግምት ውስጥ በማስገባት ተዘጋጅቷል ብሏል ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ በመግለጫው፡፡
ምክር ቤቱ በሌላ በኩል የሂሣብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የተወያየ ሲሆን ኢንስቲትዩቱ ብቁ እና ብዛት ያላቸውን ባለሙያዎች በማፍራት በመንግስት እና በግል ተቋማት የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀት እና አቀራረብ ሥርዓት በመዘርጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚኖረው ነው ተብሏል፡፡
ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብዓቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
Website
LinkedIn | YouTube | X | Facebook | TikTok
ዛሬ በተደርገው የሚንስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ከዚህ በፊት ከፀደቀው 1 ትሪልዮን ብር በተጨማሪ 581.9 ቢሊዮን ብር አፅድቋል።
የተጨማሪ በጀት እና የወጪ አሸፋፈን ማስተካከያው የተሻሻለውን የ2017-2021 የመካከለኛ ዘመን የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማስፈጸም በሚያስችል መልኩ የመንግስት የፋይናንስ አቅምና ተጠባቂ ገቢዎችን ታሳቢ በማድረግ፣ የተጨማሪ በጀት ታሳቢዎችንና የወጭ ታሳቢዎችን ግምት ውስጥ በማስገባት ተዘጋጅቷል ብሏል ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ በመግለጫው፡፡
ምክር ቤቱ በሌላ በኩል የሂሣብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ የተወያየ ሲሆን ኢንስቲትዩቱ ብቁ እና ብዛት ያላቸውን ባለሙያዎች በማፍራት በመንግስት እና በግል ተቋማት የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀት እና አቀራረብ ሥርዓት በመዘርጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚኖረው ነው ተብሏል፡፡
ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብዓቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
Website
LinkedIn | YouTube | X | Facebook | TikTok
YouTube
ET Securities
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.
Moreover, we will bringing up-to-date news and information and exchange ideas on issues…
Moreover, we will bringing up-to-date news and information and exchange ideas on issues…
Tilahun Kassahun, CEO of the Ethiopian Securities Exchange, underlined the essence of inclusivity in the market, envisioning listings from startups, SMEs, family-owned businesses, state-owned companies and financial institutions. He warned that without diversity, the Exchange could face stagnation and called for domestic banks to take on roles as investment banks and corporate issuers.
Read More
Source: addisfortune
@Etstocks
Read More
Source: addisfortune
@Etstocks
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የብድር ወለድ እና የአገልግሎት ዋጋ ማሻሻያ ሊያደረግ ነው‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያ በሚያደርግበት ወቅት ለደንበኞቹ ቀደም ብሎ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡
ይህን ተከትሎም ባንኩ በሚሰጣቸው የብድር፣ የቅርንጫፍ እና የዲጂታል እንዲሁም በዓለም አቀፍ የባንክ አገልግሎቶች ላይ በቅርቡ የብድር ወለድ እና የአገልግሎት ዋጋ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን አስታውቋል።
ባንኩ በቅርቡ ለሰራተኞቹ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉ ይታወሳል።
https://www.condoaddis.com/category/etstocks
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያ በሚያደርግበት ወቅት ለደንበኞቹ ቀደም ብሎ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡
ይህን ተከትሎም ባንኩ በሚሰጣቸው የብድር፣ የቅርንጫፍ እና የዲጂታል እንዲሁም በዓለም አቀፍ የባንክ አገልግሎቶች ላይ በቅርቡ የብድር ወለድ እና የአገልግሎት ዋጋ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን አስታውቋል።
ባንኩ በቅርቡ ለሰራተኞቹ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉ ይታወሳል።
https://www.condoaddis.com/category/etstocks
የአዋሽ ባንክ ትርፍ!!
አዋሽ ባንክ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ከግብር በፊት ማትረፉ በ29ኛው የባለአሲዮኖች መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ተገልጿል፡፡
በ2016 ዓ.ም 45 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰቡን ያስታወቀው ባንኩ የተቀማጭ ገንዘቡ ከባላፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ እድገት ማሳየቱንና በፈረንጆቹ ጁን 30፣ 2024 የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ 232 ነጥብ 4 ቢሊዮን መድረሱም ተገልጿል፡፡
ባንኩ ዘንድሮ ያገኘው ትርፍ ደግሞ በሰኔ 30፣ 2024 ያገኘው ትርፍ የ11 በመቶ እድገትን ያሳየ ነው ተብሏል፡፡
በተጠናቀቀው የሂሳብ ዓመት የባንኩ የብድር መጠን ካለፈው ዓመት በ21 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወይም በ13 ነጥብ 3 በመቶ እድገት ያሳየ ሲሆን የባንኩ አጠቃላይ የብድር መጠንም 183 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡
በሌላም በኩል ከውጭ ይገባሉ በተባሉትና በሀገር ውስጥ በቅርቡ በተመሰረቱት ባንኮች የተነሳ ከፍተኛ ውድድር ይኖራል ይሄንንም በቁርጠኝነት ለመወጣት ባንኩ ዝግጁ ነው ተብሏል፡፡
የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በተመለከተ ባንኩ በሂሳብ ዓመቱ 1 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰቡንም የባንኩ ዳይሬክተሮች የቦርድ ሊቀመንበር ጉሬ ኩምሳ አክለው ገልጸዋል።
አዋሽ ባንክ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ከግብር በፊት ማትረፉ በ29ኛው የባለአሲዮኖች መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ተገልጿል፡፡
በ2016 ዓ.ም 45 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰቡን ያስታወቀው ባንኩ የተቀማጭ ገንዘቡ ከባላፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ እድገት ማሳየቱንና በፈረንጆቹ ጁን 30፣ 2024 የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ 232 ነጥብ 4 ቢሊዮን መድረሱም ተገልጿል፡፡
ባንኩ ዘንድሮ ያገኘው ትርፍ ደግሞ በሰኔ 30፣ 2024 ያገኘው ትርፍ የ11 በመቶ እድገትን ያሳየ ነው ተብሏል፡፡
በተጠናቀቀው የሂሳብ ዓመት የባንኩ የብድር መጠን ካለፈው ዓመት በ21 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወይም በ13 ነጥብ 3 በመቶ እድገት ያሳየ ሲሆን የባንኩ አጠቃላይ የብድር መጠንም 183 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡
በሌላም በኩል ከውጭ ይገባሉ በተባሉትና በሀገር ውስጥ በቅርቡ በተመሰረቱት ባንኮች የተነሳ ከፍተኛ ውድድር ይኖራል ይሄንንም በቁርጠኝነት ለመወጣት ባንኩ ዝግጁ ነው ተብሏል፡፡
የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በተመለከተ ባንኩ በሂሳብ ዓመቱ 1 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰቡንም የባንኩ ዳይሬክተሮች የቦርድ ሊቀመንበር ጉሬ ኩምሳ አክለው ገልጸዋል።
Wegagen Bank has made monumental strides in its operations to provide value to its shareholders, including optimising fund management for ensured liquidity and focusing on loan collections. Analysts see these moves as crucial, particularly in light of regulatory credit caps imposed by the National Bank of Ethiopia (NBE). The Bank has also seen a surge in income by 40pc to 9.8 billion Br, indicating its strategy's effectiveness.
Read More
Source: addisfortune
@Etstocks
Read More
Source: addisfortune
@Etstocks
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ትርፍ!!
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ2017 የመጀመሪያ ሩብ አመት 1.2 ቢሊዮን ትርፍ ማግኘቱን ገለፀ።
ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ258 በመቶ ብልጫ አለው ተብሏል።
የሩብ አመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ያካሄደው ባንኩ በግብርና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ዘርፍ የብድር አሰጣጡን በማሳደግ የብድር አሰባሰብ ሂደቱ ተሻሽሏል ብሏል።
የባንኩ የቦንድ ሽያጭ 19 በመቶ ማደጉ የባንኩ ቁልፍ ስኬት ማሳያ መሆኑም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር እመቤት ባንኩ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጋር ራሱን በማጣጣም እና በተሻሻሉ የምርምር ችሎታዎች በመጠቀም ትርፋማነቱን እንዳሳደገ ተናግረዋል።
Condoaddis.com
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ2017 የመጀመሪያ ሩብ አመት 1.2 ቢሊዮን ትርፍ ማግኘቱን ገለፀ።
ይህም ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ258 በመቶ ብልጫ አለው ተብሏል።
የሩብ አመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ያካሄደው ባንኩ በግብርና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ዘርፍ የብድር አሰጣጡን በማሳደግ የብድር አሰባሰብ ሂደቱ ተሻሽሏል ብሏል።
የባንኩ የቦንድ ሽያጭ 19 በመቶ ማደጉ የባንኩ ቁልፍ ስኬት ማሳያ መሆኑም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር እመቤት ባንኩ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጋር ራሱን በማጣጣም እና በተሻሻሉ የምርምር ችሎታዎች በመጠቀም ትርፋማነቱን እንዳሳደገ ተናግረዋል።
Condoaddis.com
ዓባይ ባንክ ከወለድ ነፃ አገልግሎት ከ 3 ቢሊዮን ብር በላይ ማግኘት መቻሉን አስታውቋል
በ2016 ሂሳብ ዓመት 8 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘት መቻሉን የገለፀው ዓባይ ባንክ ከወለድ ነፃ አገልግሎት ዘርፍ 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር እንዳገኘም አመልክቷል።
ዓመታዊ ሪፖርቱን ከሰሞኑ ያቀረበዉ ባንኩ ተቀማጭ ገንዘቡን 52 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ማድረሱንም አስታዉቋል።
ዓባይ ባንክ አጠቃላይ የሃብት መጠኑ 66 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ እና የደንበኞቹን ቁጥርም 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ማድረስ እንደቻለም ገልጿል።
ዓባይ ባንክ በሀገር አቀፍ ደረጃ 548 ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን፤ ከዘጠኝ ሺህ በላይ ቋሚና ጊዜያዊ ሰራተኞችን በስሩ ይዞ እንደሚገኝ ለካፒታል በላከው ሪፖርት መረዳት ተችሏል።
የባንኩ 15ኛው የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንደተገለጸው በሂሳብ አመቱ ከግብር በፊት 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን እና የዲጂታል ግብይቶች ደግሞ ከጠቅላላው ግብይቶች 54% እንደሚሸፍኑ አስታውቋል።
Source: capitalethiopia
@ETstocks
በ2016 ሂሳብ ዓመት 8 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘት መቻሉን የገለፀው ዓባይ ባንክ ከወለድ ነፃ አገልግሎት ዘርፍ 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር እንዳገኘም አመልክቷል።
ዓመታዊ ሪፖርቱን ከሰሞኑ ያቀረበዉ ባንኩ ተቀማጭ ገንዘቡን 52 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ማድረሱንም አስታዉቋል።
ዓባይ ባንክ አጠቃላይ የሃብት መጠኑ 66 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ እና የደንበኞቹን ቁጥርም 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ማድረስ እንደቻለም ገልጿል።
ዓባይ ባንክ በሀገር አቀፍ ደረጃ 548 ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን፤ ከዘጠኝ ሺህ በላይ ቋሚና ጊዜያዊ ሰራተኞችን በስሩ ይዞ እንደሚገኝ ለካፒታል በላከው ሪፖርት መረዳት ተችሏል።
የባንኩ 15ኛው የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንደተገለጸው በሂሳብ አመቱ ከግብር በፊት 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን እና የዲጂታል ግብይቶች ደግሞ ከጠቅላላው ግብይቶች 54% እንደሚሸፍኑ አስታውቋል።
Source: capitalethiopia
@ETstocks
በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ስነ-ምህዳርን ለማሳደግ ወሳኝ እርምጃ መሆኑ የተነገረለት መመሪያ ተግባራዊ መደረጉን ባለስልጣኑ አስታወቀ
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ሲጠበቅ የነበረዉን መመሪያ መፅደቁን ያስታወቀ ሲሆን ይህም የባለስልጣኑን የተወሰኑትን ስልጣን እና ኃላፊነት በዉክልና ለመስጠት እንደሚያስችለዉ ተገልጿል ።
"ራሳቸውን በራሳቸው የሚቆጣጠሩ ድርጅቶች እዉቅና አሰጣጥ እና ቁጥጥር" የተሰኘዉ መመሪያ ቁጥር 1031/2017 ከባለስጣኑ ኃላፊነቶቹ ውስጥ እንዳስፈላጊነቱ የተወሰኑትን ስልጣን እና ሀላፊነትን በውክልና እውቅና ለሚሰጠው ራሱን በራሱ ለሚቆጣጠር ድርጅት የሚያስተላልፍበትን ስርዐት እንደሆነም ተነግሯል ።
በካፒታል ገበያ አዋጅ 1248/2021 መሠረት ይህን ራሳቸውን በራሳቸው የሚቆጣጠሩ ድርጅቶች እውቅና አሰጣጥ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር መፅደቁን እና 1031/2017 ሆኖ መመዝገቡን ባለስልጣኑ አስታዉቋል ።
ይህ ምእራፍ በኢትዮጵያ በሚገባ የተስተካከለ የካፒታል ገበያ ስነ-ምህዳርን ለማሳደግ ወሳኝ እርምጃ መሆኑ የተሰማ ሲሆን ይህ አዲሱ መመሪያ ፍትሃዊ ውድድርን በማጎልበት እና የባለስልጣኑን የቁጥጥር ሀላፊነት ጫና በመቀነስ ረገድ ጠቃሚ ሚና እንደሚጫወቱ ለመረዳት ተችሏል።
Source: capitalethiopia
@Etstocks
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ሲጠበቅ የነበረዉን መመሪያ መፅደቁን ያስታወቀ ሲሆን ይህም የባለስልጣኑን የተወሰኑትን ስልጣን እና ኃላፊነት በዉክልና ለመስጠት እንደሚያስችለዉ ተገልጿል ።
"ራሳቸውን በራሳቸው የሚቆጣጠሩ ድርጅቶች እዉቅና አሰጣጥ እና ቁጥጥር" የተሰኘዉ መመሪያ ቁጥር 1031/2017 ከባለስጣኑ ኃላፊነቶቹ ውስጥ እንዳስፈላጊነቱ የተወሰኑትን ስልጣን እና ሀላፊነትን በውክልና እውቅና ለሚሰጠው ራሱን በራሱ ለሚቆጣጠር ድርጅት የሚያስተላልፍበትን ስርዐት እንደሆነም ተነግሯል ።
በካፒታል ገበያ አዋጅ 1248/2021 መሠረት ይህን ራሳቸውን በራሳቸው የሚቆጣጠሩ ድርጅቶች እውቅና አሰጣጥ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር መፅደቁን እና 1031/2017 ሆኖ መመዝገቡን ባለስልጣኑ አስታዉቋል ።
ይህ ምእራፍ በኢትዮጵያ በሚገባ የተስተካከለ የካፒታል ገበያ ስነ-ምህዳርን ለማሳደግ ወሳኝ እርምጃ መሆኑ የተሰማ ሲሆን ይህ አዲሱ መመሪያ ፍትሃዊ ውድድርን በማጎልበት እና የባለስልጣኑን የቁጥጥር ሀላፊነት ጫና በመቀነስ ረገድ ጠቃሚ ሚና እንደሚጫወቱ ለመረዳት ተችሏል።
Source: capitalethiopia
@Etstocks