ET Securities
651 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
287 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
ሌላው በግምገማ ላይ የሚገኘው መመሪያ ስለ የራስ አስተዳደር ድርጅቶችን (SROs) ፈቃድ መስጠት እና መቆጣጠር ነው።  እንደ ESX እና CSD አቅራቢዎች ፈቃድ ያላቸው አካላት በካፒታል ገበያ ውስጥ አገልግሎት አቅራቢዎችን የመቆጣጠር ኃላፊነት እንደ SROs ይመደባሉ።  እነዚህ ድርጅቶች የገበያውን ታማኝነት በመጠበቅ እና የስርዓት አደጋዎችን በመቀነስ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።

ተጨማሪ ያንብቡ
ምንጭ፡ addisfortune
@etstocks
የኢትዮ ቴሌኮምን አክሲዮን ገዝተዋል??
Anonymous Poll
16%
አዎ ገዝቻለሁ
84%
አይ አልገዛሁም
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የስማርት ስልክ ፋይናንስ፣ ማይክሮ ክሬዲት እና የኢንቨስትመንት አገልግሎቶችን አስተዋወቀ!!

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የስማርት ስልክ ግዢን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመቅረብ የሚያስችል ፋይናንስ ፕሮግራም ለመክፈት ማቀዱ ተገልጿል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ዊም ቫንሄሌፑት ይህ ፕሮግራም በኬንያ 3 ሚሊየን ስማርት ስልኮችን በማዳረስ ውጤታማነቱን ገልፀው ወጪን ለመቀነስ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለመስራት መታቀዱንም ጠቁመዋል።

ሳፋሪኮም ከሁለት አመት በፊት በኢትዮጵያ ስራ ከጀመረ ወዲህ 1 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ ከ3,500 በላይ ታወሮችን ገንብቶ ወደ 6 ሚሊዮን የሚጠጉ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ ተገልጿል። የኤም-ፔሳ አገልግሎቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ያነሰ ቢሆንም 4.5 ሚሊዮን ደንበኞችን አሉት ተብሏል።

ሳፋሪኮም 'አሁን ግዛ፣ በኋላ ክፈል ' የብድር ተቋም እና ደንበኞች እንዲቆጥቡ ፣ በቦንድ ወይም ስቶኮች ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል በኬንያ ማሊ ፈንድ ጋር የሚመሳስለ "Wealth" የተሰኘ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት እንዳቀደ ሸጋ ሚዲያ ዘግቧል።

@etstocks
የባንኮች የብድር ወለድ ምጣኔ አለመቀነስ!!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ የባንኮች የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንደማይደረግ ተናግረዋል፡፡

የባንኩ ገዢ ይህንን ለብሉምበርግ የተናገሩት በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ባንክና የገንዘብ ተቋም የጸደይ ጉባዔ ላይ ሲሆን ውሳኔም በገበያው ያለውን ገንዘብ መጠን በመቀነስ ተበዳሪዎች ብዙ እንዳይበደሩ ለማድረግና የዋጋ ንረቱን ለመቀነስ ታስቦ መሆኑም ተገልጿል፡፡

የነሐሴ ወር 2016 ዓ.ም የዋጋ ንረት ከዓመት በፊት ከነበረበት ከ29 በመቶ ወደ 17 ነጥብ 5 በመቶ መቀነስ መቻሉን ብሔራዊ ባንክ መግለጹ አይዘነጋም፡፡

በሚቀጥለው 2018 ዓ.ም ይህንን የዋጋ ንረት ከ10 በመቶ በታች ወደ ነጠላ አሃዝ የማውረድ ዕቅድ ተቀምጧል፡፡

ይሁንና የዓለም ገንዘብ ድርጅት (IMF) የዚህ ዓመት የኢትዮጵያ የዋጋ ንረት 25 በመቶ እንደሚሆንና ወደ ነጠላ አሃዝ የሚወርደው በፈረንጆቹ 2028/29 እንደሚሆን ትንበያውን አስቀምጧል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለም ብሔራዊ ባንኩ ተግባራዊ ባደረገው በወለድ ተመን በሚመራ የገንዘብ ፖሊስ ሲሆን በዚህም ምክንያት ለመጀመሪያ ጊዜ ይህ የብድር ወለድ ምጣኔ 15 በመቶ  መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡

የብድር ወለድ ምጣኔው ወቅታዊ የዋጋ ንረትን፣ ዝቅተኛ የመሰረታዊ ገንዘብ እድገትና ካለፉት ዓመታት ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ እየወረደ የመጣውን የባንክ ብድር ዕድገትን እንዲሁም ሌሎችንም የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ ያሰገባ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

የፖሊሲ አውጪ ባንኩ የውጭ ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በዚህም የመንግስት በጀትንና የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ወጪዎችን በጥብቅ መቆጣጠርን ገቢራዊ ያደርጋል፡፡

ለዚህ ማሳያ የሚሆነውም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውጤታማ ባለመሆናቸው የሚያጠፏቸውን ብድሮች መቀነስና አጠቃላይ ኢኮኖሚው ውስጥ የጥሬ ገንዘብ (Broad Money) እንዳይበዛ የመከላከል ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው የሚጠበቀው፡፡

@Etstocks
Interested in becoming a broker or expanding your expertise in Ethiopia’s capital market?

Join on November 1st for an in-depth look at what it takes to enter and excel as a broker. From understanding the regulatory landscape to mastering brokerage operations, this webinar will unpack the essentials. Don’t miss this opportunity to learn directly from industry experts and connect with others shaping the future of finance in Ethiopia.

🗓 Date: November 1, 2024
🕘 Time: 9 AM – 12 PM
💻 Location: Virtual

Secure your spot today and start your journey in capital markets. Link to register: https://events.teams.microsoft.com/event/54ebacca-52ca-4d05-92f6-df335c9be112@8aeb7792-5347-4256-8ba7-a033cabe8c86/registration
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበት የገንዘብ ገበያ ይፋ አደርገ::


ET Securities
ድረ ገጽ: www.condoaddis.com/category/Etstocks
ቴሌግራም      t.me/Etstocks
ትዊተር         https://twitter.com/Etstocks1
ፌስ ቡክ፡   https://www.facebook.com/Etstocks
Youtube:https://www.youtube.com/@etstocks
Linkedin(ሊንክዲን):https://www.linkedin.com/company/etstocks
Alibaba Teams Up with Local Company to Open First Showroom in Addis Ababa

Alibaba’s first showroom has opened its doors in Addis Ababa through a foundational partnership with local firm Echelon Groups.

Read more

@Etstocks
ንብ ባንክ አቶ ሔኖክ ከበደን ዋና ሥራ አስፈጻሚነት መረጠ።
****
#ሪፖርተር
የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ የቀድሞውን የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሔኖክ ከበደን፣ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አድርጎ እንደገና መምረጡ ታወቀ፡፡

አቶ ሔኖክ የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲያገለግሉ ከቦርዱ የቀረበላቸውን ጥያቄ በመቀበላቸው፣ የንብ ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሹመቱ እንዲፀድቅለት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማመልከቱ ታውቋል፡፡

ንብ ባንክ ከስድስት ወራት በፊት አቶ ሔኖክን ለዋና ሥራ አስፈጻሚነት ዕጩ አድርጎ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም፣ በወቅቱ ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን እንዳላፀደቀው ይታወሳል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ሹመታቸውን ያላፀደቀው ከአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸው እንዲነሱ የተደረጉበት ምክንያት ሊጣራ ይገባል ተብሎ እንደነበር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ሆኖም አቶ ሔኖክ ከአማራ ባንክ የለቀቁበት ምክንያት አግባብ እንዳልነበር ከሥራ ሲሰናበቱ በአማራ ባንክ ቦርድ የተጻፈባቸው ደብዳቤ እሳቸውን የማይገልጽ መሆኑን በማመልከት ለብሔራዊ ባንክ ባቀረቡ አቤቱታ መሠረት፣ በአማራ ባንክ የተጻፈባቸውን ደብዳቤ መሠረት ያደረገው ዕግድ በብሔራዊ ባንክ ተነስቶላቸዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አድርጎ መርጧቸዋል፡፡

ብሔራዊ ባንክም ከዚህ ቀደም ጥሎባቸው የነበረውን ዕገዳ በማንሳቱ እንደገና በዋና ሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ የቀረበውን ጥያቄ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የቀድሞዋ የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ከኃላፊነታቸው ከለቀቁ በኋላ፣ ባንኩ አቶ በላይ ጎርፉን በተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚነት መመደቡ ይታወሳል፡፡

የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁት አቶ ሔኖክ በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ ልምድ ያላቸው ናቸው፡፡ በትምህርት ዝግጅታቸውም ከእንግሊዝ ግሪንዊች ዩኒቨርሲቲ በበዓለም አቀፍ ቢዝነስ የኤምቢኤ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው፡፡

በሥራው ዓለምም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተለያዩ ኃላፊነቶች ከስድስት ዓመታት በላይ የሠሩ ሲሆን፣ የባንኩ የብራንች ኦፊሰር ሆነው አገልግለዋል፡፡ በተለይም ለሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲስትሪክት ማኔጀር በመሆንም ሠርተዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከለቀቁ በኋላ ዳሸን ባንክን በመቀላቀል ከስድስት ዓመታት በላይ የባንኩ ቺፍ ባንኪንግ ኦፊሰር (ምክትል ፕሬዚዳንት) በመሆን ሠርተዋል፡፡ ከዳሸን ባንክ የለቀቁት የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲያገለግሉ የቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀብለው ነበር፡፡

የአማራ ባንክ የመጀመሪያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆንም ለሁለት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ፣ ከአማራ ባንክ ቦርድ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ኃላፊነታቸውን መልቀቃቸው አይዘነጋም፡፡ የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እስከታጩበት ጊዜ ድረስም በአንድ የፋይናንስ ተቋም ውስጥ በከፍተኛ አማካሪነት እያገለገሉ ነበር፡፡
Source~ Banks Ethiopia
@etstocks
The federal government is set to reform the franco valuta scheme due to concerns over market distortion, capital flight, and its impact on parallel market rates. Originally aimed at easing foreign currency flows for manufacturers and traders amid a forex shortage, the scheme allowed businesses to import goods without presenting foreign currency documentation. However, issues have arisen, with officials noting its impact on parallel market rates and concerns over capital flight.

Source: Addisfortune
@Etstocks
ሁለት የግል ባንኮች (አዋሽ ባንክ
እና ወጋገን ባንክ) የመጀመርያዎቹ የፋይናንስ ተቋማት በመሆን በኢትዮጵያ ሴኩሪቲስ ገበያ የሚተዳደረው እና በኢንፎ-ቴክ ግሩፕ በተሰራው የኤሌክትሮኒክስ መድረክ ግብይት የፈጸሙ።

Read More
@etstocks
#Ethiotelecom
#Telebirr

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለጊዜው የሞባይል ገንዘብ ግብይት ገደብ አነሳ! ለጊዜው የተነሳው ከባንክ ወደ ቴሌ ብር ለሚደርግ የገንዘብ ዝውውር ብቻ እንደሆነ ተነግሯል።

መንግስት የኢትዮ ቴሌኮምን 10 በመቶ ድርሻ ወደ ገበያ ማውጣቱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎ ባንኮች ከአክስዮን ግዢ ጋር በተገናኘ በቀላሉ ገንዘብ እየለቀቁ እንዳልሆነ ተሰምቷል። የሞባይል ገንዘብ ግብይት ገደብ የተነሳውም ኢትዮ ቴሌኮም ለገበያ ያቀረበውን የአክሲዮን ሽያጭ ሂደቱን እስኪያጠናቅቅ ድረስ ነው።

መረጃው ከሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ነው!
@Etstocks
አዋሽ ኢንሹራንስ በሰፊ ልዩነት ገበያውን በአንደኝነት መምራት መቻሉን ገለፀ!!

አዋሽ ኢንሹራንስ በ2ዐ16 በጀት ዓመት ከ3.1 ቢሊዮን ብር በላይ አጠቃላይ የአረቦን ገቢ አሰባስቦ ከግል ኢንሹራንስ ኩባንያዎች የላቀ በመሆን የገበያውን መሪነት መያዙን ካፒታል ዘግቧል።

ኩባንያው በበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ በጀነራል ኢንሹራንስ ከ2.6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አግኝቷል ተብሏል።

በዚህም ከ17ቱ የግል ኢንሹራንስ ኩባንያዎች በሰፊ ልዩነት ገበያውን በአንደኝነት እየመራ እንደሚገኝ ገልጿል።

በሕይወት ኢንሹራንስ ዘርፍ የ443.7 ሚሊዮን ብር አረቦን ገቢ አሰባስቦ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት 18ቱ ኩባንያዎች ቀዳሚ ሆኗል ተብሏል።

በ2016 ዓ.ም ብቻ በተለያዩ ኩባንያዎች ከ387.9 ሚሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት በማድረግ በድምሩ የ1.25 ቢሊዮን ብር የአክሲዮን ባለድርሻ መሆን ችሏል።

2017 ከገባ እስካሁን አጠቃላይ ሀብቱ ከ7.7 ቢሊዮን ብር በላይ በማድረስ የተከፈለ ካፒታሉ ከ1.9 ቢሊዮን ብር መሻገሩን ተገልጿል።

ምንጭ_ ካፒታል
@Etsticks
የአፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ ባንኮች ወደ የኢትዮጵያ ለመግባት እያጤኑ መሆኑ ተሰማ‼️

መንግስት ሊበራላይዜሽን ሊያጠናቅቅ በተቃረበበት ወቅት ከኬንያ፣ ሞሮኮ እና የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የተውጣጡ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ በባንክ ዘርፍ ሊገቡ መሆኑ ተሰምቷል።
በባለፈው በሰኔ ወር ብሄራዊ ባንክ የውጭ ባንኮች "በጥሩ ሁኔታ የተቋቋመ፣ ታዋቂ እና በፋይናንሺያል ጤናማ የሆነ የውጭ ባንክ" ንዑስ ድርጅት/ቅርንጫፍ፣ ተወካይ ቢሮ ለመመስረት ወይም በአገር ውስጥ ባንኮች ውስጥ አክሲዮኖችን በመግዛት የሚሰማሩበትን ረቂቅ ማፅደቁ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ "ሕጉ በህዳር ወር መጨረሻ አካባቢ በሀገሪቱ ፓርላማ እንደሚፀድቅ" መናገራቸው ይታወሳል።
ማሞ የሞሮኮ፣ የኬንያ እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ባንኮች ፍላጎት እንዳላቸው በወቅቱ መጠቆማቸው ይታወሳል።

@Etstocks