ET Securities
651 subscribers
576 photos
7 videos
27 files
290 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
As Ethio Telecom aims to raise 30 billion birr selling shares to the public, here are key figures from the operator’s recently released prospectus.

Source: shegamedia
@Etstocks
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከ5 ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ምርቶችን አገበያይቷል
***
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድማገኝ ነገራ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት አራት የግብርና ምርቶች ወደ ዘመናዊ የገበያ ስርአት እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከአምስት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ምርቶች ማገበያየቱን ገልጸዋል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከጸደይ ባንክ ጋር የክፍያ አጋርነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

ስምምነቱም አርሶ አደሮችና ኤክስፖርተሮች በመጋዘን የሚኖራቸዉን ምርቶች በማስያዝ ብድር እንዲያገኙ የሚያስችላቸዉ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የግብርና ምርታና ምርታማነት ለማሳደግ ተጨማሪ የግብርና አይነቶች በብዙ አካባቢ እንዲመረቱ እንዲሁም ወደ ዘመናዊ ግብይት እንዲሸጋገሩ እየሰራ ይገኛል።

በመስከረም ሰይፉ

ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓም
@etstocks
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የንግድ ባንኮች የሚገጥማቸውን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ለመፍታት አሻሽሎ ያወጣውን መመሪያ ይፋ አድርጓል።

መመሪያው ያስፈለገው፣ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የሚገጥማቸው ንግድ ባንኮች ከብሄራዊ ባንክ ሲበደሩ ግልጽና ተጠያቂነት ያለው አሠራር በማስፈለጉ እንደኾነ ባንኩ ገልጧል። ከባንኩ የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት የሚችሉት ባንኮች፣ ጊዜያዊ የሆነ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የገጠማቸው፣ በቀጣይነት አስተማማኝ ካፒታል መያዝ የሚችሉ፣ ችግራቸውን ለመፍታት ኹሉንም አማራጮች አሟጠው ስለመጠቀማቸው የሚያስረዱ፣ የመጠባበቂያ እቅዳቸውን ተግባራዊ አድርገው ችግሩን መቅረፍ እንዳልቻሉ ማስረጃ የሚያቀርቡና ተቀባይነት ያለው የእዳ ማስመያዣ ያላቸው እንደኾኑ አስታውቋል።


[ዋዜማ]
Ethiopian Securities Exchange Signs MoU with Nairobi Securities Exchange and iCapital Africa Institute

Ethiopian Securities Exchange (ESX) has signed a Memorandum of Understanding (MoU) with the Nairobi Securities Exchange (NSE) and iCapital Africa Institute, aiming to accelerate the growth and integration of capital markets in Ethiopia and Kenya.

Source: 2merkato
@Etstocks
ሌላው በግምገማ ላይ የሚገኘው መመሪያ ስለ የራስ አስተዳደር ድርጅቶችን (SROs) ፈቃድ መስጠት እና መቆጣጠር ነው።  እንደ ESX እና CSD አቅራቢዎች ፈቃድ ያላቸው አካላት በካፒታል ገበያ ውስጥ አገልግሎት አቅራቢዎችን የመቆጣጠር ኃላፊነት እንደ SROs ይመደባሉ።  እነዚህ ድርጅቶች የገበያውን ታማኝነት በመጠበቅ እና የስርዓት አደጋዎችን በመቀነስ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።

ተጨማሪ ያንብቡ
ምንጭ፡ addisfortune
@etstocks
የኢትዮ ቴሌኮምን አክሲዮን ገዝተዋል??
Anonymous Poll
16%
አዎ ገዝቻለሁ
84%
አይ አልገዛሁም
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የስማርት ስልክ ፋይናንስ፣ ማይክሮ ክሬዲት እና የኢንቨስትመንት አገልግሎቶችን አስተዋወቀ!!

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የስማርት ስልክ ግዢን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመቅረብ የሚያስችል ፋይናንስ ፕሮግራም ለመክፈት ማቀዱ ተገልጿል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ዊም ቫንሄሌፑት ይህ ፕሮግራም በኬንያ 3 ሚሊየን ስማርት ስልኮችን በማዳረስ ውጤታማነቱን ገልፀው ወጪን ለመቀነስ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለመስራት መታቀዱንም ጠቁመዋል።

ሳፋሪኮም ከሁለት አመት በፊት በኢትዮጵያ ስራ ከጀመረ ወዲህ 1 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ ከ3,500 በላይ ታወሮችን ገንብቶ ወደ 6 ሚሊዮን የሚጠጉ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ ተገልጿል። የኤም-ፔሳ አገልግሎቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ያነሰ ቢሆንም 4.5 ሚሊዮን ደንበኞችን አሉት ተብሏል።

ሳፋሪኮም 'አሁን ግዛ፣ በኋላ ክፈል ' የብድር ተቋም እና ደንበኞች እንዲቆጥቡ ፣ በቦንድ ወይም ስቶኮች ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል በኬንያ ማሊ ፈንድ ጋር የሚመሳስለ "Wealth" የተሰኘ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት እንዳቀደ ሸጋ ሚዲያ ዘግቧል።

@etstocks
የባንኮች የብድር ወለድ ምጣኔ አለመቀነስ!!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ የባንኮች የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንደማይደረግ ተናግረዋል፡፡

የባንኩ ገዢ ይህንን ለብሉምበርግ የተናገሩት በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ባንክና የገንዘብ ተቋም የጸደይ ጉባዔ ላይ ሲሆን ውሳኔም በገበያው ያለውን ገንዘብ መጠን በመቀነስ ተበዳሪዎች ብዙ እንዳይበደሩ ለማድረግና የዋጋ ንረቱን ለመቀነስ ታስቦ መሆኑም ተገልጿል፡፡

የነሐሴ ወር 2016 ዓ.ም የዋጋ ንረት ከዓመት በፊት ከነበረበት ከ29 በመቶ ወደ 17 ነጥብ 5 በመቶ መቀነስ መቻሉን ብሔራዊ ባንክ መግለጹ አይዘነጋም፡፡

በሚቀጥለው 2018 ዓ.ም ይህንን የዋጋ ንረት ከ10 በመቶ በታች ወደ ነጠላ አሃዝ የማውረድ ዕቅድ ተቀምጧል፡፡

ይሁንና የዓለም ገንዘብ ድርጅት (IMF) የዚህ ዓመት የኢትዮጵያ የዋጋ ንረት 25 በመቶ እንደሚሆንና ወደ ነጠላ አሃዝ የሚወርደው በፈረንጆቹ 2028/29 እንደሚሆን ትንበያውን አስቀምጧል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለም ብሔራዊ ባንኩ ተግባራዊ ባደረገው በወለድ ተመን በሚመራ የገንዘብ ፖሊስ ሲሆን በዚህም ምክንያት ለመጀመሪያ ጊዜ ይህ የብድር ወለድ ምጣኔ 15 በመቶ  መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡

የብድር ወለድ ምጣኔው ወቅታዊ የዋጋ ንረትን፣ ዝቅተኛ የመሰረታዊ ገንዘብ እድገትና ካለፉት ዓመታት ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ እየወረደ የመጣውን የባንክ ብድር ዕድገትን እንዲሁም ሌሎችንም የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ ያሰገባ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

የፖሊሲ አውጪ ባንኩ የውጭ ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በዚህም የመንግስት በጀትንና የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ወጪዎችን በጥብቅ መቆጣጠርን ገቢራዊ ያደርጋል፡፡

ለዚህ ማሳያ የሚሆነውም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውጤታማ ባለመሆናቸው የሚያጠፏቸውን ብድሮች መቀነስና አጠቃላይ ኢኮኖሚው ውስጥ የጥሬ ገንዘብ (Broad Money) እንዳይበዛ የመከላከል ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው የሚጠበቀው፡፡

@Etstocks
Interested in becoming a broker or expanding your expertise in Ethiopia’s capital market?

Join on November 1st for an in-depth look at what it takes to enter and excel as a broker. From understanding the regulatory landscape to mastering brokerage operations, this webinar will unpack the essentials. Don’t miss this opportunity to learn directly from industry experts and connect with others shaping the future of finance in Ethiopia.

🗓 Date: November 1, 2024
🕘 Time: 9 AM – 12 PM
💻 Location: Virtual

Secure your spot today and start your journey in capital markets. Link to register: https://events.teams.microsoft.com/event/54ebacca-52ca-4d05-92f6-df335c9be112@8aeb7792-5347-4256-8ba7-a033cabe8c86/registration
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበት የገንዘብ ገበያ ይፋ አደርገ::


ET Securities
ድረ ገጽ: www.condoaddis.com/category/Etstocks
ቴሌግራም      t.me/Etstocks
ትዊተር         https://twitter.com/Etstocks1
ፌስ ቡክ፡   https://www.facebook.com/Etstocks
Youtube:https://www.youtube.com/@etstocks
Linkedin(ሊንክዲን):https://www.linkedin.com/company/etstocks
Alibaba Teams Up with Local Company to Open First Showroom in Addis Ababa

Alibaba’s first showroom has opened its doors in Addis Ababa through a foundational partnership with local firm Echelon Groups.

Read more

@Etstocks
ንብ ባንክ አቶ ሔኖክ ከበደን ዋና ሥራ አስፈጻሚነት መረጠ።
****
#ሪፖርተር
የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ የቀድሞውን የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሔኖክ ከበደን፣ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አድርጎ እንደገና መምረጡ ታወቀ፡፡

አቶ ሔኖክ የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲያገለግሉ ከቦርዱ የቀረበላቸውን ጥያቄ በመቀበላቸው፣ የንብ ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሹመቱ እንዲፀድቅለት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማመልከቱ ታውቋል፡፡

ንብ ባንክ ከስድስት ወራት በፊት አቶ ሔኖክን ለዋና ሥራ አስፈጻሚነት ዕጩ አድርጎ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም፣ በወቅቱ ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን እንዳላፀደቀው ይታወሳል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ሹመታቸውን ያላፀደቀው ከአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸው እንዲነሱ የተደረጉበት ምክንያት ሊጣራ ይገባል ተብሎ እንደነበር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ሆኖም አቶ ሔኖክ ከአማራ ባንክ የለቀቁበት ምክንያት አግባብ እንዳልነበር ከሥራ ሲሰናበቱ በአማራ ባንክ ቦርድ የተጻፈባቸው ደብዳቤ እሳቸውን የማይገልጽ መሆኑን በማመልከት ለብሔራዊ ባንክ ባቀረቡ አቤቱታ መሠረት፣ በአማራ ባንክ የተጻፈባቸውን ደብዳቤ መሠረት ያደረገው ዕግድ በብሔራዊ ባንክ ተነስቶላቸዋል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አድርጎ መርጧቸዋል፡፡

ብሔራዊ ባንክም ከዚህ ቀደም ጥሎባቸው የነበረውን ዕገዳ በማንሳቱ እንደገና በዋና ሥራ አስፈጻሚነት እንዲያገለግሉ የቀረበውን ጥያቄ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የቀድሞዋ የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እመቤት መለሰ (ዶ/ር) ከኃላፊነታቸው ከለቀቁ በኋላ፣ ባንኩ አቶ በላይ ጎርፉን በተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚነት መመደቡ ይታወሳል፡፡

የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁት አቶ ሔኖክ በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ ልምድ ያላቸው ናቸው፡፡ በትምህርት ዝግጅታቸውም ከእንግሊዝ ግሪንዊች ዩኒቨርሲቲ በበዓለም አቀፍ ቢዝነስ የኤምቢኤ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው፡፡

በሥራው ዓለምም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተለያዩ ኃላፊነቶች ከስድስት ዓመታት በላይ የሠሩ ሲሆን፣ የባንኩ የብራንች ኦፊሰር ሆነው አገልግለዋል፡፡ በተለይም ለሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲስትሪክት ማኔጀር በመሆንም ሠርተዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከለቀቁ በኋላ ዳሸን ባንክን በመቀላቀል ከስድስት ዓመታት በላይ የባንኩ ቺፍ ባንኪንግ ኦፊሰር (ምክትል ፕሬዚዳንት) በመሆን ሠርተዋል፡፡ ከዳሸን ባንክ የለቀቁት የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲያገለግሉ የቀረበላቸውን ጥያቄ ተቀብለው ነበር፡፡

የአማራ ባንክ የመጀመሪያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆንም ለሁለት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ፣ ከአማራ ባንክ ቦርድ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ኃላፊነታቸውን መልቀቃቸው አይዘነጋም፡፡ የንብ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እስከታጩበት ጊዜ ድረስም በአንድ የፋይናንስ ተቋም ውስጥ በከፍተኛ አማካሪነት እያገለገሉ ነበር፡፡