💠ፕሮስፔክተስ ለባለሀብቶች ስለማቀርብ የሰነደ መዋለ ነዋይ መረጃ የሚሰጥ የጽሁፍ ሰነድ ነው።
ዓላማ
ፕሮስፔክተስ እንደ አክሲዮኖች፣ ቦንዶች ወይም የጋራ ፈንድ ላሉ ዋስትናዎች ለሚሰጡ ኩባንያዎች ዋና የሽያጭ መሣሪያ ነው።
ለባለሀብቶች የገንዘብ ነክ አደጋዎችን እና ዋስትናዎችን የሚገልጽ ይፋ ማድረጊያ ሰነድ ነው።
ዓላማ
ፕሮስፔክተስ እንደ አክሲዮኖች፣ ቦንዶች ወይም የጋራ ፈንድ ላሉ ዋስትናዎች ለሚሰጡ ኩባንያዎች ዋና የሽያጭ መሣሪያ ነው።
ለባለሀብቶች የገንዘብ ነክ አደጋዎችን እና ዋስትናዎችን የሚገልጽ ይፋ ማድረጊያ ሰነድ ነው።
አንድ ሰው ከኢትዮ ቴሌኮም የገዛውን አክሲዮን ድርሻ ማዘዋወር፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ቢፈልግ ይችላል ወይ ?
አትዮ ቴሌኮም አሁን የሚጀመረው የአክሲዮን ሺያጭ የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ አስታውቋል።
በዚህ ምዕራፍ ዜጎች የአክሲዮን ድርሻ ብቻ መግዛት የሚችሉ ይሆናል።
ዜጎች ድርሻቸውን ማዘዋወር ፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም የሚችሉት ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛ ምዕራፍ ብሎ ባስቀመጠው ሲሆን ይህም ገና በሂደት ላይ እንዳለ ተጠቅሷል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴሌኮም በ " listing " ሂደት ላይ እንደሚገኝ እና ይህም በአጭር ጊዜ እንደሚጠናቀቅ የጠቀሱ ሲሆን ይፋዊ ቀን ግን አልተቆረጠለትም።
የሁለተኛው ዙር አክሲዮን ሽያጭ ሲጀመር ደግሞ ዜጎች ድርሻ ማዘዋወር ፣ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ያስችላቸዋል።
እንዴት ነው አክሲዮን የሚገዛው ?
➡ በቴሌብር ላይ ነው መግዛት የሚቻለው። ቴሌብር ላይ ሲገቡ አክሲዎን ለመግዛት የሚል አማራጭ ይገናኛል (ልክ ላውንች ሲደረግ) በዛ አማካኝነት ነው መግዛት የሚቻለው። በዛ ዝርዝር መረጃ ይገኛል፤ የደብንበኝነት ውልን ስለሚኖር አንብቦ መቀጠል ይችላል ከተስማሙ።
(እስካሁን ድረስ ቴሌብር ላይ ይህ የአክሲዎችን ሽያጭ አማራጭ አልመጣም ልክ ሲመጣ እናሳውቃችኃለን)
➡ ፎርሙን በ48 ሰዓት ውስጥ ማስተካከል ይቻላል ፤ በተመሳሳይ ክፍያም በ48 ሰዓት ውስጥ መከፈል አለበት። ከ48 ሰዓት በኃላ ፎርሙን ማስተካከል አይቻልም።
➡ ፎርሙን መጀመሪያ በመደበኛ መታወቂያ፣ መንጃ ፍቃድ ፣ ፓስፖርት መሙላት የሚቻል ሲሆን መጨረሻ ላይ የሼር ባለቤት ለመሆን የናሽናል አይዲ (ፋይዳ) ያስፈልጋል።
➡ ሼር ገዢ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ለሽያጭ ከቀረበው ሼር በላይ ከመጣ ከዛ ውስጥ እነማን የሼሩ ባለቤት ይሆናሉ የሚለውን ለመለየት የሚያስችል አሰራር ተቀምጧል። (በቀጣይ በዚህ ላይ መረጃ እናቀርባለን)
➡️ ሼር መግዛት ማመልከይ የሚችለው ኢትዮጵያዊ ዜጋ እና እዚሁ ሀገር ውስጥ በአካል ያለ ነው።
2016 ዓ/ም በወጣ የሂሳብ ሪፖርት የድርጅቱ የካፒታል 100 ቢሊዮን ብር ሲሆን በዓለም አቀፍ የ3ተኛ ወገን የገበያ ተመን መሰረት ድርጅቱ የሚያወጣው ዋጋ 300 ቢሊዮን ብር ነው።
በመጀመሪያ ዙር መደበኛ የአክሲዮን ሽያጭ የቀረበው ደግሞ 100 ሚሊዮን ሼር ነው። የአንድ ሼር ዋጋም 300 ብር ነው። ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 33 ሼር ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 9,900 ብር ይሆናል። ከፍተኛው መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 3,333 ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 999,900 ብር ይሆናል።
-tikvah
አትዮ ቴሌኮም አሁን የሚጀመረው የአክሲዮን ሺያጭ የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ አስታውቋል።
በዚህ ምዕራፍ ዜጎች የአክሲዮን ድርሻ ብቻ መግዛት የሚችሉ ይሆናል።
ዜጎች ድርሻቸውን ማዘዋወር ፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም የሚችሉት ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛ ምዕራፍ ብሎ ባስቀመጠው ሲሆን ይህም ገና በሂደት ላይ እንዳለ ተጠቅሷል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴሌኮም በ " listing " ሂደት ላይ እንደሚገኝ እና ይህም በአጭር ጊዜ እንደሚጠናቀቅ የጠቀሱ ሲሆን ይፋዊ ቀን ግን አልተቆረጠለትም።
የሁለተኛው ዙር አክሲዮን ሽያጭ ሲጀመር ደግሞ ዜጎች ድርሻ ማዘዋወር ፣ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ያስችላቸዋል።
እንዴት ነው አክሲዮን የሚገዛው ?
➡ በቴሌብር ላይ ነው መግዛት የሚቻለው። ቴሌብር ላይ ሲገቡ አክሲዎን ለመግዛት የሚል አማራጭ ይገናኛል (ልክ ላውንች ሲደረግ) በዛ አማካኝነት ነው መግዛት የሚቻለው። በዛ ዝርዝር መረጃ ይገኛል፤ የደብንበኝነት ውልን ስለሚኖር አንብቦ መቀጠል ይችላል ከተስማሙ።
(እስካሁን ድረስ ቴሌብር ላይ ይህ የአክሲዎችን ሽያጭ አማራጭ አልመጣም ልክ ሲመጣ እናሳውቃችኃለን)
➡ ፎርሙን በ48 ሰዓት ውስጥ ማስተካከል ይቻላል ፤ በተመሳሳይ ክፍያም በ48 ሰዓት ውስጥ መከፈል አለበት። ከ48 ሰዓት በኃላ ፎርሙን ማስተካከል አይቻልም።
➡ ፎርሙን መጀመሪያ በመደበኛ መታወቂያ፣ መንጃ ፍቃድ ፣ ፓስፖርት መሙላት የሚቻል ሲሆን መጨረሻ ላይ የሼር ባለቤት ለመሆን የናሽናል አይዲ (ፋይዳ) ያስፈልጋል።
➡ ሼር ገዢ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ለሽያጭ ከቀረበው ሼር በላይ ከመጣ ከዛ ውስጥ እነማን የሼሩ ባለቤት ይሆናሉ የሚለውን ለመለየት የሚያስችል አሰራር ተቀምጧል። (በቀጣይ በዚህ ላይ መረጃ እናቀርባለን)
➡️ ሼር መግዛት ማመልከይ የሚችለው ኢትዮጵያዊ ዜጋ እና እዚሁ ሀገር ውስጥ በአካል ያለ ነው።
2016 ዓ/ም በወጣ የሂሳብ ሪፖርት የድርጅቱ የካፒታል 100 ቢሊዮን ብር ሲሆን በዓለም አቀፍ የ3ተኛ ወገን የገበያ ተመን መሰረት ድርጅቱ የሚያወጣው ዋጋ 300 ቢሊዮን ብር ነው።
በመጀመሪያ ዙር መደበኛ የአክሲዮን ሽያጭ የቀረበው ደግሞ 100 ሚሊዮን ሼር ነው። የአንድ ሼር ዋጋም 300 ብር ነው። ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 33 ሼር ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 9,900 ብር ይሆናል። ከፍተኛው መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 3,333 ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 999,900 ብር ይሆናል።
-tikvah
As Ethio Telecom aims to raise 30 billion birr selling shares to the public, here are key figures from the operator’s recently released prospectus.
Source: shegamedia
@Etstocks
Source: shegamedia
@Etstocks
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከ5 ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ምርቶችን አገበያይቷል
***
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድማገኝ ነገራ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት አራት የግብርና ምርቶች ወደ ዘመናዊ የገበያ ስርአት እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከአምስት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ምርቶች ማገበያየቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከጸደይ ባንክ ጋር የክፍያ አጋርነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ስምምነቱም አርሶ አደሮችና ኤክስፖርተሮች በመጋዘን የሚኖራቸዉን ምርቶች በማስያዝ ብድር እንዲያገኙ የሚያስችላቸዉ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የግብርና ምርታና ምርታማነት ለማሳደግ ተጨማሪ የግብርና አይነቶች በብዙ አካባቢ እንዲመረቱ እንዲሁም ወደ ዘመናዊ ግብይት እንዲሸጋገሩ እየሰራ ይገኛል።
በመስከረም ሰይፉ
ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓም
@etstocks
***
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድማገኝ ነገራ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት አራት የግብርና ምርቶች ወደ ዘመናዊ የገበያ ስርአት እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከአምስት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ምርቶች ማገበያየቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከጸደይ ባንክ ጋር የክፍያ አጋርነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ስምምነቱም አርሶ አደሮችና ኤክስፖርተሮች በመጋዘን የሚኖራቸዉን ምርቶች በማስያዝ ብድር እንዲያገኙ የሚያስችላቸዉ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የግብርና ምርታና ምርታማነት ለማሳደግ ተጨማሪ የግብርና አይነቶች በብዙ አካባቢ እንዲመረቱ እንዲሁም ወደ ዘመናዊ ግብይት እንዲሸጋገሩ እየሰራ ይገኛል።
በመስከረም ሰይፉ
ጥቅምት 8 ቀን 2017 ዓም
@etstocks
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የንግድ ባንኮች የሚገጥማቸውን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ለመፍታት አሻሽሎ ያወጣውን መመሪያ ይፋ አድርጓል።
መመሪያው ያስፈለገው፣ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የሚገጥማቸው ንግድ ባንኮች ከብሄራዊ ባንክ ሲበደሩ ግልጽና ተጠያቂነት ያለው አሠራር በማስፈለጉ እንደኾነ ባንኩ ገልጧል። ከባንኩ የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት የሚችሉት ባንኮች፣ ጊዜያዊ የሆነ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የገጠማቸው፣ በቀጣይነት አስተማማኝ ካፒታል መያዝ የሚችሉ፣ ችግራቸውን ለመፍታት ኹሉንም አማራጮች አሟጠው ስለመጠቀማቸው የሚያስረዱ፣ የመጠባበቂያ እቅዳቸውን ተግባራዊ አድርገው ችግሩን መቅረፍ እንዳልቻሉ ማስረጃ የሚያቀርቡና ተቀባይነት ያለው የእዳ ማስመያዣ ያላቸው እንደኾኑ አስታውቋል።
[ዋዜማ]
መመሪያው ያስፈለገው፣ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የሚገጥማቸው ንግድ ባንኮች ከብሄራዊ ባንክ ሲበደሩ ግልጽና ተጠያቂነት ያለው አሠራር በማስፈለጉ እንደኾነ ባንኩ ገልጧል። ከባንኩ የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት የሚችሉት ባንኮች፣ ጊዜያዊ የሆነ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የገጠማቸው፣ በቀጣይነት አስተማማኝ ካፒታል መያዝ የሚችሉ፣ ችግራቸውን ለመፍታት ኹሉንም አማራጮች አሟጠው ስለመጠቀማቸው የሚያስረዱ፣ የመጠባበቂያ እቅዳቸውን ተግባራዊ አድርገው ችግሩን መቅረፍ እንዳልቻሉ ማስረጃ የሚያቀርቡና ተቀባይነት ያለው የእዳ ማስመያዣ ያላቸው እንደኾኑ አስታውቋል።
[ዋዜማ]
Ethiopian Securities Exchange Signs MoU with Nairobi Securities Exchange and iCapital Africa Institute
Ethiopian Securities Exchange (ESX) has signed a Memorandum of Understanding (MoU) with the Nairobi Securities Exchange (NSE) and iCapital Africa Institute, aiming to accelerate the growth and integration of capital markets in Ethiopia and Kenya.
Source: 2merkato
@Etstocks
Ethiopian Securities Exchange (ESX) has signed a Memorandum of Understanding (MoU) with the Nairobi Securities Exchange (NSE) and iCapital Africa Institute, aiming to accelerate the growth and integration of capital markets in Ethiopia and Kenya.
Source: 2merkato
@Etstocks
ሌላው በግምገማ ላይ የሚገኘው መመሪያ ስለ የራስ አስተዳደር ድርጅቶችን (SROs) ፈቃድ መስጠት እና መቆጣጠር ነው። እንደ ESX እና CSD አቅራቢዎች ፈቃድ ያላቸው አካላት በካፒታል ገበያ ውስጥ አገልግሎት አቅራቢዎችን የመቆጣጠር ኃላፊነት እንደ SROs ይመደባሉ። እነዚህ ድርጅቶች የገበያውን ታማኝነት በመጠበቅ እና የስርዓት አደጋዎችን በመቀነስ ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።
ተጨማሪ ያንብቡ
ምንጭ፡ addisfortune
@etstocks
ተጨማሪ ያንብቡ
ምንጭ፡ addisfortune
@etstocks
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የስማርት ስልክ ፋይናንስ፣ ማይክሮ ክሬዲት እና የኢንቨስትመንት አገልግሎቶችን አስተዋወቀ!!
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የስማርት ስልክ ግዢን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመቅረብ የሚያስችል ፋይናንስ ፕሮግራም ለመክፈት ማቀዱ ተገልጿል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው ዊም ቫንሄሌፑት ይህ ፕሮግራም በኬንያ 3 ሚሊየን ስማርት ስልኮችን በማዳረስ ውጤታማነቱን ገልፀው ወጪን ለመቀነስ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለመስራት መታቀዱንም ጠቁመዋል።
ሳፋሪኮም ከሁለት አመት በፊት በኢትዮጵያ ስራ ከጀመረ ወዲህ 1 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ ከ3,500 በላይ ታወሮችን ገንብቶ ወደ 6 ሚሊዮን የሚጠጉ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ ተገልጿል። የኤም-ፔሳ አገልግሎቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ያነሰ ቢሆንም 4.5 ሚሊዮን ደንበኞችን አሉት ተብሏል።
ሳፋሪኮም 'አሁን ግዛ፣ በኋላ ክፈል ' የብድር ተቋም እና ደንበኞች እንዲቆጥቡ ፣ በቦንድ ወይም ስቶኮች ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል በኬንያ ማሊ ፈንድ ጋር የሚመሳስለ "Wealth" የተሰኘ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት እንዳቀደ ሸጋ ሚዲያ ዘግቧል።
@etstocks
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የስማርት ስልክ ግዢን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመቅረብ የሚያስችል ፋይናንስ ፕሮግራም ለመክፈት ማቀዱ ተገልጿል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው ዊም ቫንሄሌፑት ይህ ፕሮግራም በኬንያ 3 ሚሊየን ስማርት ስልኮችን በማዳረስ ውጤታማነቱን ገልፀው ወጪን ለመቀነስ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለመስራት መታቀዱንም ጠቁመዋል።
ሳፋሪኮም ከሁለት አመት በፊት በኢትዮጵያ ስራ ከጀመረ ወዲህ 1 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት በማድረግ ከ3,500 በላይ ታወሮችን ገንብቶ ወደ 6 ሚሊዮን የሚጠጉ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ ተገልጿል። የኤም-ፔሳ አገልግሎቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ቴሌብር ያነሰ ቢሆንም 4.5 ሚሊዮን ደንበኞችን አሉት ተብሏል።
ሳፋሪኮም 'አሁን ግዛ፣ በኋላ ክፈል ' የብድር ተቋም እና ደንበኞች እንዲቆጥቡ ፣ በቦንድ ወይም ስቶኮች ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል በኬንያ ማሊ ፈንድ ጋር የሚመሳስለ "Wealth" የተሰኘ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት እንዳቀደ ሸጋ ሚዲያ ዘግቧል።
@etstocks
የባንኮች የብድር ወለድ ምጣኔ አለመቀነስ!!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ የባንኮች የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንደማይደረግ ተናግረዋል፡፡
የባንኩ ገዢ ይህንን ለብሉምበርግ የተናገሩት በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ባንክና የገንዘብ ተቋም የጸደይ ጉባዔ ላይ ሲሆን ውሳኔም በገበያው ያለውን ገንዘብ መጠን በመቀነስ ተበዳሪዎች ብዙ እንዳይበደሩ ለማድረግና የዋጋ ንረቱን ለመቀነስ ታስቦ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የነሐሴ ወር 2016 ዓ.ም የዋጋ ንረት ከዓመት በፊት ከነበረበት ከ29 በመቶ ወደ 17 ነጥብ 5 በመቶ መቀነስ መቻሉን ብሔራዊ ባንክ መግለጹ አይዘነጋም፡፡
በሚቀጥለው 2018 ዓ.ም ይህንን የዋጋ ንረት ከ10 በመቶ በታች ወደ ነጠላ አሃዝ የማውረድ ዕቅድ ተቀምጧል፡፡
ይሁንና የዓለም ገንዘብ ድርጅት (IMF) የዚህ ዓመት የኢትዮጵያ የዋጋ ንረት 25 በመቶ እንደሚሆንና ወደ ነጠላ አሃዝ የሚወርደው በፈረንጆቹ 2028/29 እንደሚሆን ትንበያውን አስቀምጧል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለም ብሔራዊ ባንኩ ተግባራዊ ባደረገው በወለድ ተመን በሚመራ የገንዘብ ፖሊስ ሲሆን በዚህም ምክንያት ለመጀመሪያ ጊዜ ይህ የብድር ወለድ ምጣኔ 15 በመቶ መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡
የብድር ወለድ ምጣኔው ወቅታዊ የዋጋ ንረትን፣ ዝቅተኛ የመሰረታዊ ገንዘብ እድገትና ካለፉት ዓመታት ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ እየወረደ የመጣውን የባንክ ብድር ዕድገትን እንዲሁም ሌሎችንም የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ ያሰገባ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡
የፖሊሲ አውጪ ባንኩ የውጭ ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በዚህም የመንግስት በጀትንና የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ወጪዎችን በጥብቅ መቆጣጠርን ገቢራዊ ያደርጋል፡፡
ለዚህ ማሳያ የሚሆነውም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውጤታማ ባለመሆናቸው የሚያጠፏቸውን ብድሮች መቀነስና አጠቃላይ ኢኮኖሚው ውስጥ የጥሬ ገንዘብ (Broad Money) እንዳይበዛ የመከላከል ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው የሚጠበቀው፡፡
@Etstocks
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ የባንኮች የወለድ ምጣኔ ዝቅ እንደማይደረግ ተናግረዋል፡፡
የባንኩ ገዢ ይህንን ለብሉምበርግ የተናገሩት በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ባንክና የገንዘብ ተቋም የጸደይ ጉባዔ ላይ ሲሆን ውሳኔም በገበያው ያለውን ገንዘብ መጠን በመቀነስ ተበዳሪዎች ብዙ እንዳይበደሩ ለማድረግና የዋጋ ንረቱን ለመቀነስ ታስቦ መሆኑም ተገልጿል፡፡
የነሐሴ ወር 2016 ዓ.ም የዋጋ ንረት ከዓመት በፊት ከነበረበት ከ29 በመቶ ወደ 17 ነጥብ 5 በመቶ መቀነስ መቻሉን ብሔራዊ ባንክ መግለጹ አይዘነጋም፡፡
በሚቀጥለው 2018 ዓ.ም ይህንን የዋጋ ንረት ከ10 በመቶ በታች ወደ ነጠላ አሃዝ የማውረድ ዕቅድ ተቀምጧል፡፡
ይሁንና የዓለም ገንዘብ ድርጅት (IMF) የዚህ ዓመት የኢትዮጵያ የዋጋ ንረት 25 በመቶ እንደሚሆንና ወደ ነጠላ አሃዝ የሚወርደው በፈረንጆቹ 2028/29 እንደሚሆን ትንበያውን አስቀምጧል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለም ብሔራዊ ባንኩ ተግባራዊ ባደረገው በወለድ ተመን በሚመራ የገንዘብ ፖሊስ ሲሆን በዚህም ምክንያት ለመጀመሪያ ጊዜ ይህ የብድር ወለድ ምጣኔ 15 በመቶ መሆኑ የሚታወስ ነው፡፡
የብድር ወለድ ምጣኔው ወቅታዊ የዋጋ ንረትን፣ ዝቅተኛ የመሰረታዊ ገንዘብ እድገትና ካለፉት ዓመታት ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ እየወረደ የመጣውን የባንክ ብድር ዕድገትን እንዲሁም ሌሎችንም የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ ያሰገባ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡
የፖሊሲ አውጪ ባንኩ የውጭ ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰን ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በዚህም የመንግስት በጀትንና የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ወጪዎችን በጥብቅ መቆጣጠርን ገቢራዊ ያደርጋል፡፡
ለዚህ ማሳያ የሚሆነውም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውጤታማ ባለመሆናቸው የሚያጠፏቸውን ብድሮች መቀነስና አጠቃላይ ኢኮኖሚው ውስጥ የጥሬ ገንዘብ (Broad Money) እንዳይበዛ የመከላከል ሥራዎች እንደሚሰሩም ነው የሚጠበቀው፡፡
@Etstocks