ET Securities
651 subscribers
576 photos
7 videos
27 files
290 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
#News አማራ ባንክ ከታክስ በፊት ከ 377 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን የገለፀ ሲሆን ተቀማጭ ገንዘብ ከ 25 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል ሲል አስታዉቋል ።

ባንኩ በተጠናቀቀው የ2023/24 በጀት ዓመት የተሻለ ከታክስ በፊት ብር 377.2 ሚሊየን ትርፍ ያስመዘገበ መሆኑን እና ብር ተቀማጭ ገንዘብ ከ 25.1 ቢሊየን ብር ላይ መድረሱን ገሌጿል።

ከ1.8 ሚሊየን በላይ ደንበኞች እንዳሉት የሚነገርለት ባንኩ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች አጠቃላይ ብር 20.3 ቢሊየን ብድር መስጠቱን ገለጿል።

አማራ ባንክ የበጀት ዓመቱን አፈፃፀም በተመከለተ በሰጠዉ መግለጫ ከ 571 ሺ በላይ የሞባይል ባንክ ተጠቃሚዎችን እንዲሁም ከ50 ሺ በላይ የካርድ ተገልጋዮችን ማፍራት የቻለ ሲሆን በርካታ የኤቲኤም እና የፖስ ማሽኖችን በተለያዩ ቦታዎች በማኖር በዲጂታል ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ ችያለሁ ብሏል ።

ካፒታል
የኅብረት ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ከበደ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ!
***
በኅብረት ባንክ በተለያዩ የኃለፊነት መደቦች ከ20 ዓመታት በላይ ሲያገለግሉ የቆዩት፣ ባለፉት 5 ዓመታት ደግሞ በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የነበሩት አቶ መላኩ ከበደ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ፡፡

የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት አቶ መላኩ ከኃላፊነታቸው የለቀቁት በገዛ ፈቃዳቸው ሲሆን፣ ይህንንም በመልቀቂያ ደብዳቤያቸው ላይ ያሰፈሩ ቢሆንም፣ ውሳኔያቸው ድንገተኛ ነው ተብሏል፡፡ ከባንኩ የተገኘው መረጃ ደግሞ አቶ መላኩ ኃላፊነታቸውን የለቀቁት ከግል ምክንያት ጋር በተያያዘ ነው፡፡

ድንገተኛ የተባለውን የአቶ መላኩ የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ የተቀበለው የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አዎንታዊ መልስ እንደሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

ቦርዱ በአቶ መላኩ ምትክ ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እንዲያገለግሉ፣ የባንኩ ሲኒየር ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ (ኦፕሬሽን) ሆነው በማገልገል ላይ የሚገኙትን ወ/ሮ ጽጌሬዳ ተስፋዬን መሰየሙ ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ልምድ አላቸው ተብለው ከሚጠቀሱ የባንክ ባለሙያዎች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ መላኩ፣ በኅብረት ባንክ ብቻ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ በተለይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ከመሾማቸው በፊት፣ ከ11 ዓመታት በላይ በምክትል ሥራ አስፈጻሚነት ሲያገለግሉ ነበር፡፡

አቶ መላኩ በኅብረት ባንክ ቆይታቸው በተለይ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የተከናወኑ ሥራዎችን በሙሉ በማስተባበርና በመምራት፣ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበራቸው ይጠቀሳል፡፡

ም/ፕሬዚዳንትና ዳይሬክተር በመሆን የዲጂታል የባንክ አገልግሎት ዘርፉን  ለ11 ዓመታት መምራታቸውን የተገኘው የባንኩ መረጃ ያስረዳል፡፡
Siket Bank registers 1.6 billion birr profit in first year after banking transition

Siket Bank, formerly known as Addis Credit and Saving S.C., has marked a significant milestone in its first year as a full-fledged bank, reporting an impressive profit of 1.6 billion birr for the 2023/24 financial year. This marks the end of a successful inaugural year since its transition from a microfinance institution to a commercial bank.

The bank, which became Ethiopia’s 32nd commercial bank after receiving approval from the National Bank of Ethiopia last year, earned more than 2.3 billion birr in revenue during the fiscal year. This represents a 42 percent increase in income compared to the previous year, when the institution was still operating as a microfinance entity.



Source: capitalethiopia
የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችለውን እንቅስቃሴ ጀመረ

የአሊባባ ግሩፕ (AliExpress) በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችለውን እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገለጸ።
የቻይናው አሊባባ ግሩፕ ከኢትዮጵያ አየር መንገድና ከኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማህበር ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ስራ ለመጀመር የሚያስችለውን እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ ያደረገበት መድረክ ዛሬ ተካሄዷል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን አለማየሁ(ዶ/ር) የአሊባባ አሊ ኤክስፕረስ በኢትዮጵያ ስራ መጀመሩ
ኢትዮጵያውያን ሸማቾችና ነጋዴዎች በአዲሱ የዓለም ገበያ ምርትና አገልግሎትን ለመገበያየትና ኢትዮጵያን ወደ ዓለም አቀፍ ንግድ እንዲገቡ ማስቻሉን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢኮሜርስ ሎጂስቲክስ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ ቴዎድሮስ አያሌው አየር መንገዱ አሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የኢኮሜርስ ስራ ለማሳለጥ የሚያስችል የኢኮሜርስ ሎጂስቲክስ አገልግሎትን የሚሰጥ ማዕከል(ሀብ) ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።

የአሊ ኤክስፕረስ ቢዝነስ ዳይሬክተር ጄፍሪ ጂያንግ ድርጅቱ በኢኮሜርስ ያለውን ዓለም አቀፍ ልምድ በመጠቀም የኢትዮጵያውያን ሸማቾችንና የንግድ ቦታዎችን እንቅስቃሴ ለማስተሳሰር እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ምንጭ :ኢዜአ
Source ~ Banks Ethiopia
@etstocks
Highest Dollar offer DBE

@etstocks
ብሔራዊ ባንክ የዉጪ ምንዛሪ ቢሮ ፍቃድ መስጠት የሚያስችለውን ሂደት መጨረሱን ገለፀ‼️

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም መደበኛ ባልሆነ መንገድ የዉጪ ምንዛሪ ላይ የሚሳተፉ አካላትን ህጋዊ ሆነዉ ፍቃድ አዉጥተዉ መስራት እንዲችሉ መፍቀዱን ተከትሎ ከወዲሁ ብዙ ሰዎችና ኩባንያዎችን እየተቀበለ እንደሚገኝ አስታዉቋል።

የዉጪ ምንዛሪ ገበያ ዉስጥ የሚሳተፉ በፊት ባንኮች ብቻ የነበሩ ቢሆንም አሁን ግን ከባንኮች በተጨማሪ ሌሎች በግላቸው በዘርፉ ላይ ለመሰማራት የሚፈልጉ አካላት እንዲሰሩ ተደርጓል።

ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ክትትልና መጠባበቂያ አስተዳደር ምክትል ዳይሬክተር አቶ አበባየሁ ዱፈራ እንደተናገሩት " የዉጪ ምንዛሪ ዚሮዉን ለመክፈት ፍላጎት አሳይተዋል ያላቸዉን ሰዎች መቀበሉን " የገለፁ ሲሆን ከንግድ ሚኒስትር ጋር ያለዉ ጉዳይ ከተፈታ ወዲያው ፍቃድ መስጠት እንጀምራለን በእኛ በኩል ሁሉም ነገር አልቋል ሲሉ ተደምጠዋል ።

እንደ ምክትል ዳይሬክተሩ ገለፃ "ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚኖሩ የዉጪ ሀገር ዜጎችም አካዉንት ከፍተዉ ሲፈልጉ ብቻ ወደ ብር ቀይረዉ እንዲጠቀሙ ተፈቅዷል " ይህም በድፍረት የተደረገ ነዉ ማለት ይቻላል ሲሉም እርጃዉን አድንቀውታል።

ሀገር ዉስጥ ያሉ ማንኛውም የዉጪ ምንዛሪ የሚያገኙ ግለሰቦች በትንሹ በ 100 ዶላር የዉጪ ምንዛሪ አካዉንት መክፈት እንደሚችሉ የጠቆሙት አበባየሁ ዱፈራ ይህ ጥቅሙ ለግለሰቦች ሳይሆን ሀገርም ጭምር ተጠቃሚ ይሆናል ብለዋል።
#Capital
የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 8.6 ቢሊዮን ብር የአርቦን ገቢ ማስመዝገብ መቻሉን እና የእቅዱን 92.4 በመቶ ማሳካት መቻሉን አስታወቀ

ብቸናዉ መንግስታዊ የኢንሹራንስ ኩባንያ የሆነዉ ተቋሙ ካስመዘገበዉ የአረቦን መጠን ዉስጥ 8.3 ቢሊዮን ያህሉ ከመድን ዘርፍ የተመዘገበ ካለፈው በጀት ቀሪዉ 306.5 ሚሊዮን የሚሆነዉ ከረጅም ጊዜ መድን ዘርፍ የተመዘገበ መሆኑን በዓመታዊ ሪፖርቱ ገልጿል።

በበጀት አመቱ ከተመዘገበው አረቦን ውስጥ 85 በመቶውን ለመሰብሰብ እቀድ የተያዘ ቢሆንም የተሰበሰበው የአረቦን መጠን 89.7 በመቶውን ነው፡፡ ይህም ከተቀመጠው እቅድ አንጻር ሲገመገም አፈጻጸሙ 105.5 በመቶ መሆኑን ያስታወቀዉ ድርጅቱ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ግን አፈጻጸሙ የ9.3 በመቶ ብልጫ አለዉ ብሏል።

የኢትዮጵያ መድን ድርጅት እንዳስታወቀው በተጠናቀቀው ሂሳብ ዓመት ከታክስ በፊት ከ 1.66 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን እና ይህም ከተያዘው እቅድ ጋር ሲነፃፀር 7.5 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ሲል በሪፖርቱ ገልጿል ።

Source: ENA
Source _ Banks Ethiopia

@etstocks
አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ከታክስ በፊት 47 ሚሊዮን ብር አተረፈ!

የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ በ2023/24 ሒሳብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ጥሩ ውጤት ማስመዝገቡን አብስሯል፡፡ በቀረበው ሪፖርት መሠረት ባሳለፍነው የሒሳብ ዓመት ከታክስ በፊት 47 ሚሊዮን ብር አትርፏል፡፡

ብር 232 ሚሊዮን አጠቃላይ ገቢ የተገኘ ሲሆን

አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ብር 1.8 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አገልግሎት ለ8250 ደንበኞች አቅርቧል፤ የተሰጡ ብድሮች ለግል ፍጆታ ብድር፣ ለቢዝነስ ማስፋፊያ፣ ለግብርና ብድር፣ ለቤት መስሪያና ማደሻ እና ለተሽከርካሪ ግዥ ብድር ለማኅበረሰባችን ተደራሽ አድጓል፡፡

የተከፈለ ካፒታል ብር 136 ሚሊዮን እንዲሁም ጠቅላላ የተቋሙ ሃብት ብር 1.9 ቢሊዮን ደርሷል፡፡
Wegagen Bank overtakes DBE offering the highest rate for buying of USD
Ethiopia and China strike a historic currency swap deal to boost trade.

At the China-Africa summit, FDRE Minister of Finance H.E. Ahmed Shide, anounced a significant financial agreement between Ethiopia and China. The two nations have entered in to a currency swap deal, allowing them to conduct trade using their own local currencies.
ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የዉጪ ምንዛሪ ግኝትን ከፍ ማድረጉን አስታዉቋል

👉 በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሐዋላ የዉጪ ምንዛሪ ቢሮ ለሚከፍቱ ከሳምንታት በኃላ ፍቃድ መስጠት እንደሚጀመር ባንኩ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የዉጪ ምንዛሪ ግኝት ከፍ ማድረጉን አስታዉቋል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ደቦ የተሰኘ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን የሚያሻሽል ፕሮግራም ባንኩ ይፋ አድርጓል ።

የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ እንደተናገሩት በህጋዊ መንገድ የሃዋላ የውጭ ምንዛሬ ቢሮ ለሚከፍቱ ግለሰቦች ( ተቋማት) ከሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት በኋላ ፈቃድ መስጠት ይጀምራል ብለዋል።

መንግስት በቅርቡ ተግባራዊ ያደረገዉ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ያበረታታ እና ዜጎችን ወደ ሕጋዊ መንገድ ያመጣ እንደሆነም ተነግሯል ።

በ2023 ከሬሚታንስ ከ653 ሚሊዮን ዶላር በላይ መገኘት መቻሉን የገለፀዉ ብሔራዊ ባንክ ይሄንን ግኝት ከፍ ለማድረግ የሚያስችል አዲስ የውጭ ምንዛሪ አሥተዳደር መመሪያ መዘጋጀቱን አስታዉቋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሃዋላ የውጭ ምንዛሬ ሊያሳድግና የተሻሻለውን የማክሮ ኢኮኖሚ ተግባራዊነት ሊያረጋግጥ እንደሚችል የገለፀዉን የስድስት ወር ንቅናቄ ዛሬ በይፋ አስጀምሯል።

Source: capitalethiopia
@Etstocks
ሰነደ መዋዕለ ንዋይን ለሕዝብ ለማቅረብ የሚያስችል መመርያ ተዘጋጀ

ለአዳዲስ ሥራ ፈጣሪዎች የካፒታል ገበያ ቁጥጥር ማጣሪያ ማዕቀፍ መዘጋጀቱ ተገልጿል
ለካፒታል ገበያ ወደ ሥራ መግባት ትክክለኛና አስፈላጊ ነው የተባለ የሰነደ መዋዕለ ንዋይን ለሕዝብ ለማቅረብ የሚያስችል መመርያ ዝግጅት መጠናቀቁን፣ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን አስታወቀ።

የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን አዳዲስ የሥራ ፈጣሪዎች በሥራ ላይ ያሉትን የቁጥጥር ደንቦችና መመርያዎችን መከተል ሳይጠበቅባቸው፣ አገልግሎቶቻቸውን ለካፒታል ገበያ ማቅረብ የሚያስችል የቁጥጥር ማጣሪያ ማዕቀፍ ሐሙስ ነሐሴ 23 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል።

የካፒታል ገበያን ወደ ሥራ ለማስገባት ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በርካታ የሕግ ማዕቀፎች ሲዘጋጁ መቆየታቸውን የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሪት ሀና ተኸልኩ ለሪፖርተር ገልጸዋል።

የካፒታል ገበያን ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ለማስገባትና የኩባንያዎችን መዋዕለ ንዋይ ለሕዝብ ማቅረብ እንዲቻል፣ ባለሥልጣኑ ሲያዘጋጀው የቆየው መመርያ መጠናቀቁን የገለጹት ወ/ሪት ሀና፣ ተግባራዊ ለማድረግም በፍትሕ ሚኒስቴር ማስመዝገብ ብቻ ነው የቀረው ብለዋል፡፡ ‹‹በዚህ መሀል ሰነደ መዋዕለ ንዋይን ለሕዝብ የሚያቀርቡ ድርጅቶች ሰነዶቻቸውን እንዲያዘጋጁ ለማድረግ እየሠራን ነው፤›› ሲሉም ጠቁመዋል።

የውጭ ባለሀብቶች ወደ አገር ውስጥ በመግባት የካፒታል ገበያው ውስጥ አክሲዮን መግዛት እንዲችሉ በቅርቡ የተደረገው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እንደሚፈቅድ የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ነገር ግን የሰነድ መዋዕለ ንዋይን ለሕዝብ ለማቅረብ የሚያስችለው መመርያ ፀድቆ ወደ ሥራ ያልገባ በመሆኑ፣ የውጭ ባለሀብቶች ገብተው አክሲዮን እንዳልገዙ አስታውቀዋል። መመርያው ፀድቆ የካቲፓል ገበያው ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ሲገባ፣ የውጭ ባለህብቶች ወደ አገር ውስጥ ገብተው ሼር የመግዛትም ሆነ የመሸጥ መብት እንዳላቸው ገልጸዋል።

‹‹በካፒታል ገበያ ሰዎች ከተሻሻጡ በኋላ አክሲዮኑን ከአንድ ሰው ገንዘቡን ደግሞ ከሌላ ሰው የሚያቀያይር ሥርዓት (Central Securities Depository) ያስፈልጋል፤›› ያሉ ዋና ዳይሬክተሯ፣ ይህንንም በብሔራዊ ባንክ ግዥ መካሄዱንና የሙከራ ሒደት ላይ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የልማት ድርጅት አዳዲስ የፋይናንስ ሙከራ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሪት ዳግማዊት ሽፈራው በበኩላቸው፣ ባንኮች የሚሰጧቸው እንደ ብድር፣ ገንዘብ ማስቀመጥና ኢንሹራንስ ያሉ አገልግሎቶች ለሚሰጡ ባንኮች፣ ብሔራዊ ባንክ በሚያወጣቸው ሕጎችና መመርያዎች የሚተዳደሩ መሆናቸውን፣ በካፒታል ገበያ ውስጥ ያለ አገልግሎት ከሆነ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሚያወጣቸው ሕጎች እንደሚተዳደሩ ገልጸዋል።

ሆኖም ኢንቨስትመንት ባንክ ሆነው በተለየ መንገድ የሚሠሩ ከሆነና አሁን ባለው የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አሰጣጥ የማይቻል ከሆነ ደግሞ፣ ባለሥልጣኑ ይፋ ባደረገው የካፒታል ገበያ ቁጥጥር ማጣሪያ ማዕቀፍ እንደሚታይ አስታውቀዋል።

በቁጥጥር ማጣሪያ ማዕቀፉ የሚቀርበው ጥያቄ ተቀባይነት ካገኘ በኋላ አገልግሎቱ የፈጠራ ይዘቱ እንደሚመረመር፣ እንዲሁም ለምን ዓይነት ገበያና ተጠቃሚዎች ይቀርባል የሚለው እንደሚጣራ ወ/ሪት ሀና ገልጸዋል። ይህን ሒደት ያለፈ አገልግሎትም ተግባራዊ ሲደረግ የሚፈጠረውን ሁኔታ ለመገንዘብ የሙከራ ጊዜ እንደሚዘጋጅ አመላክተዋል።

ፈጠራን ማበረታታት አንዱ የማዕቀፉ ዓላማ መሆኑና አዳዲስ የፋይናንስ የፈጠራ አገልግሎቶችና ምርቶች ሲመጡ፣ ባለሥልጣኑ እንዴት መቆጣጠር እንደሚችል የሚማርበትና የቁጥጥር አቋም የሚገነባበት እንደሆነም ገልጸዋል።

ሪፖርተር
@etstocks
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዮሀንስ አያሌው (ዶክተር) ስራቸውን ለቀዋል። በተጠባባቂነት/በጊዚያዊነት የባንኩ ምክትል ፕሬዝዳንት ጌታቸው ዋቄ  ሀለፊነቱን ተረክበዋል።

Source: theethiopianeconomistview
@Etstocks
Source:- Banks Ethiopia
@etstocks