ET Securities
665 subscribers
589 photos
7 videos
28 files
299 links
At ET Securities, our goal is to provide services in the financial sector, with a special focus on capital markets and financial markets.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 𝗧𝗼 𝗢𝗽𝗲𝗻 𝗥𝗲𝗮𝗹 𝗘𝘀𝘁𝗮𝘁𝗲 𝗠𝗮𝗿𝗸𝗲𝘁 𝘁𝗼 𝗙𝗼𝗿𝗲𝗶𝗴𝗻𝗲𝗿𝘀 𝗜𝗻 𝗡𝗲𝘄 𝗗𝗿𝗮𝗳𝘁 𝗟𝗮𝘄

The Council of Ministers has approved a draft law that would allow foreigners to own immovable property—part of a broader effort to attract foreign capital, expand housing access, and spur job creation. The Council also ratified major international agreements, including interest-free development loans from Italy and the World Bank, Ethiopia’s accession to the African Finance Corporation, and implementation of the African Continental Free Trade Area tariff reduction. A new air transport deal with Austria and updated service fee regulations were also approved.

Source - ERB
@Etstocks
From Ledger to Leadership.pdf
351.6 KB
An articulated and yet very recommended piece of article. Worth reading!!

From Ledger to Leadership: Transforming Ethiopia's Finance Professionals
ለአምስተኛው ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 60 ሚሊዮን ዶላር ለሽያጭ ማቅረቡን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል! ጨረታው ዛሬ እስከ 6 ሰዓት ይከናወናል!
ኢብባ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ፡- የተመዘነ አማካይ ዋጋ በ132.9643 ብር በአንድ ዶላር

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያደርገውን የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ዛሬ ይፋ አድርጓል።

ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው ማስታወቂያ መሠረት በጨረታው አሸናፊ የሆኑት ሁሉም አማካኝ ዋጋ በዶላር 132.9643 ብር ነበር።

በጨረታው የውጪ ምንዛሪ ድልድል ጥያቄዎችን በማቅረብ በአጠቃላይ 16 ባንኮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክም በቀጣይ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የሚካሄድበትን መርሃ ግብር አመልክቷል። የሚቀጥለው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ይካሄዳል።
ኤርሚያስ አመልጋን ጨምሮ ህገወጥ የገንዘብ ማሰባሰብ ላይ ምርመራ ተጀመረ - የካፒታል ገበያ ባለስልጣን

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ታዋቂውን ስራ ፈጣሪ አቶ ኤርሚያስ አመልጋን እና "ጀነሲስ ኢንቨስትመንት ሰርቪስ" የተባለ ኩባንያን ጨምሮ ህገወጥ በሆነ መንገድ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮችን ለህዝብ በመሸጥ ገንዘብ ሲያሰባስቡ በነበሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ የቀረቡ ቅሬታዎችን ተቀብሎ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ በሰጠው መግለጫ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ህገወጥ የሰነድ ሽያጭን በመጠቀም ከህዝብ ገንዘብ በማሰባሰብ ተግባር ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ገልጿል።

በተለይም በአቶ ኤርሚያስ አመልጋ እና በ"ጀነሲስ ኢንቨስትመንት ሰርቪስ" ኩባንያ ላይ እየተካሄዱ ያሉት ምርመራዎች በህገ መንግስት የተረጋገጠ የመሰማት እና የመከላከል ሙሉ መብታቸው በተጠበቀ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ባለስልጣኑ አረጋግጧል።

በተጨማሪም ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ከካፒታል ገበያ ጋር በተያያዙ እንቅስቃሴዎች ላይ ሲሳተፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።

በተለይም በንግድ ድርጅቶች ምስረታ ላይ ሲሳተፉ የንግድ ምዝገባ እና ምስረታ ሰነዶችን ከሚመለከተው አካል እንዲያረጋግጡ እንዲሁም ገንዘብ ከመክፈላቸው በፊት በባለስልጣኑ ፈቃድ ከተሰጣቸው የኢንቨስትመንት አማካሪዎች ብቻ ምክር እንዲፈልጉ ጠቁሟል።

ባለስልጣኑ ፈቃድ ሳይኖራቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት የሚሰጡ ወይም ለማቅረብ የሚሞክሩ አካላት ካሉ ለባለስልጣኑ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ በእንደዚህ አይነት ህገ-ወጥ ድርጊቶች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አረጋግጧል።

Source: capitalethiopia
@Etstocks
#Vacancy

If you are passionate in regulatory compliance, market oversight, or financial supervision, and want to contribute to building a strong, transparent capital market in Ethiopia—this is your opportunity!

Apply now using the below link.
https://ethiojobs.net/job/fV61CpAz5Q-market-supervision-officer
#ለመረጃ፦ ከሚያዝያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ ተለውጧል! ቤንዚን ከ112.67 ወደ 122.53 ብር አድጓል!
ኢትዮ ቴሌኮም ለንግድ ድርጅቶች እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ሰጭዎች የአጋርነት ጥሪ አቀረበ

ግዙፉ መንግስታዊዉ የቴሌኮም አቅራቢ የሆነዉ ኢትዮ ቴሌኮም በትላንትናው ዕለት ሚያዚያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም. "ዘመን ገበያ" የተሰኘ ሀገር አቀፍ የዲጂታል የገበያ ቦታን በይፋ ካስጀመረ በኋላ፣ ከዚህ ፕላትፎርም ጋር ለመተባበር ፍላጎት ላላቸው የንግድ ድርጅቶች እና የሎጂስቲክስ አገልግሎት ሰጭዎች ጥሪ አቅርቧል ።

ኩባንያው ከዘመን ገበያ ጋር ለመስራት ባቀረበው ጥሪ መሰረት፣ ከ42 በላይ የተለያዩ የንግድ ድርጅቶች እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ሰጭዎች አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል ።

"ዘመን ገበያ" የኢኮኖሚ እድገትን በማፋጠን፣ የስራ እድል በመፍጠር፣ ዲጂታል አካታችነትን በማስፋፋትና የአገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።

ተቋሙ እንዳስታወቀው በቀጣይም የኢትዮጵያን ዲጂታል ኢኮኖሚ ለማሳደግ ከሚፈልጉ አካላት ጋር ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል።

ይህ የዲጂታል መድረክ ለአምራቾችና ለአገልግሎት አቅራቢዎች ሰፊ የገበያ ተደራሽነትን እንደሚያረጋግጥ፣ የሥራ ማስኬጃ ወጪን እንደሚቀንስ፣ ከደንበኞች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመገንባት እንደሚያግዝ እንዲሁም የዲጂታል ክፍያ መፍትሄዎችን ጨምሮ የተለያዩ ጥቅሞችን ይሰጣል ተብሏል።

ለሸማቾች በበኩሉ ሰፋ ያሉ የምርትና የአገልግሎት አማራጮችን፣ ምቹና ተደራሽ ግብይትን እንዲሁም ተወዳዳሪ ዋጋዎችን ያቀርባል። ለሎጂስቲክስ ኩባንያዎች ደግሞ ሰፊ ገበያ እንዲያገኙና በአገልግሎት አፈጻጸማቸው ላይ መሻሻል እንዲያመጡ ያግዛል ሲል ኢትዮቴሌኮም ገልጿል።

Source: capitalethiopia
@Etstocks
ወጋገን ካፒታል ቀዳሚ ያደረገውን የመጀመሪያው የግብይት አባልነት ሰርትፊኬት ከየኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለንዋይ ገበያ ተቀብሏል።

ይህም ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከካፒታል ገበያ ባለስልጣን የተቀበለውን ፍቃድ የተከተለ ነው።
የባንኩ ሰው ለይኩን ብርሃኑ  ( ከ1937 - 2017 )

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ጨምሮ በተለያዩ አገራዊ ባንኮች ከገዥነት እስከ ፕሬዚዳንትነት ያገለገሉት የአቶ ለይኩን ብርሃኑ ከአባታቸው ከአቶ ብርሃኑ ገምታ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ጉደቱ አንበቻ  ሰኔ 4 ቀን 1937 ዓ.ም በቀድሞ ወለጋ ክፍለ ሀገር በጊምቢ አውራጃ ተወለዱ።

ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በጊምቢ ደጅአዝማች ገ/እግዚአብሔር አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በቀድሞ አጠራር ነቀምቴ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡

ከዚያም በመቀጠል የከፍተኛ ትምህርታቸውን በቀድሞ አጠራር ኃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሐምሌ ወር 1961 ዓ.ም. በከፍተኛ ውጤት አጠናቀው በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የአቶ ለይኩን ብርሃኑ የሕይወት ታሪካቸው እንደሚያሳየው በሕይወት ዘመናቸው በተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ለ47 ዓመታት በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች አገልግለዋል፡፡

ከጥር 1968 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 1971 ዓ.ም. የቀድሞ የአዲስ ባንክ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ከጥቅምት 1971 ዓ.ም. እስከ 1972 ዓ.ም. ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው አገልግለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ወቅት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እንዲሁም ለባንኪንግ ኢንዱስትሪው እድገት ላደረጉት በጐ ተጽእኖ ማስታወሻ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ  ማኔጅመንት ሚያዝያ 7 ቀን 2011ዓ.ም. በስማቸው ‘’ለይኩን ብርሃኑ’’ ቅርንጫፍ ከፍቶ ለአገልግሎት አብቅቷል፡፡

አቶ ለይኩን ብርሃኑ ከጥቅምት 1972 ዓ.ም. እስከ ግንቦት 1975 ዓ.ም. የእርሻ ሰብል ገበያ ድርጅት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፣ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ከመጋቢት 1978 ዓ.ም. እስከ መስከረም 1981 ዓ.ም. የትራንስፖርትና ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ ዋና ኃላፊ እንዲሁም ከጥቅምት 1982 እስከ ጥቅምት 1984 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር  በመሆን ኃላፊነታቸውን በብቃት ተወጥተዋል፡፡

አቶ ለይኩን ብርሃኑ በ1983 ዓ.ም. የደርግ መንግሥትን መውደቅ ተከትሎ አገራችን ኢትዮጵያ የተከተለችውን የኢኮኖሚክ ሪፎርም ኘሮግራም ከህዳር 1984 ዓ.ም. እስከ መስከረም 1987 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ በመሆን በአስተባባሪነትና በአስፈጻሚነት ጉልህ ድርሻ አበርክተዋል፡፡ 

በተለይም በደርግ ዘመነ መንግሥት ለ17 ዓመታት ለግሉ ዘርፍ ዝግ ሆኖ የቆየውን የባንክና የኢንሹራንስ ዘርፍ ለግሉ ክፍለ ኢኮኖሚ ክፍት ለማድረግ አዳዲስ ባንኮችና ኢንሹራንሶች እንዲቋቋሙ የባንክና ኢንሹራንስ ሥራ ፈቃድ አዋጆችን በማውጣት በአሁኑ ጊዜ 30 የግል ባንኮች እና 17 የግል ኢንሹራንስ ኩባንያዎች  እንዲቋቋሙ መንገድ የከፈቱና የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጡ መሪ ነበሩ፡፡

አቶ ለይኩን ብርሃኑ በመጨረሻው የሥራ ዘመናቸው ከመጋቢት 1988 ዓ.ም. እስከ ታህሣስ 2003 ዓ.ም. የአዋሽ ባንክ አክሲዮን ማህበር ኘሬዚዳንት በመሆን ባንኩን ከ14 ዓመታት በላይ በኘሬዚዳንትነት አገልግለዋል፡፡ አቶ ለይኩን ብርሃኑ በተወለዱ በ80 ዓመታቸው ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም አርፈዋል  ።

የቅዳሜገበያ
@Etstocks
ኢትዮጵያ በይፋ የአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽንን ተቀላቀለች!

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  አዋጅ
ቁጥር 1379/2017ን
በማፅደቅ ሀገሪቷ ወደ አፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ለመቀላቀል የሚያስችላትን ውሣኔ አሳልፏል።

ማንበብ ይቀጥሉ
https://www.2merkato.com/news/alerts/8436-ethiopian-parliament-ratifies-proclamation-to-join-african-finance-corporation
የኢትዮጵያ ፋይናንስ ፎረም 2025 በአዲስ አበባ የሥነ ጥበብ እና ሳይንስ ሙዚየም ዛሬ በይፋ የተከፈተ ሲሆን፥ ከ150 በላይ የፋይናንስ ተቋማትን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን እና ዓለም አቀፍ ባለሙያዎችን ያካተተ ነው።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ከ12 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከማዕከላዊ ባንክ የሚበደረው ብድር ወደ ዜሮ መውረዱን አስታወቁ።

ለሁለት ቀናት የሚቆየው የውይይት መድረክ በፊንቴክ፣ በመንግስት እና በግል አጋርነት እና በአካባቢያዊ ውህደት ላይ ባሉ ክፍለ ጊዜዎች ቀጥሏል።
ባለፉት 10 ዓመታት ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ (Gross Domestic Product per capital) ከፍተኛ ዕድገት ያስመዘገቡ 10 ምርጥ የአፍሪካ ሀገራት

የነፍስ ወከፍ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ብዙውን ጊዜ ከግለሰብ ገቢ እና ፍጆታ መጨመር ጋር ይዛመዳል። ይህ የሚያሳየው በአማካይ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች ካለፈው አመት በተሻለ ሁኔታ ላይ መገኘታቸውን ነው።

ሌላው የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ ገፅታ ደግሞ የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት በነፍስ ወከፍ የግዢ ሃይል እኩልነት(Purchasing power parity) ሲሆን ይህም በእያንዳንዱ ሰው አማካይ የኢኮኖሚ ውጤትን የሚያመለክት እና በአገሮች ያለውን የኑሮ ውድነት ታሳቢ ያደረገ ነው።

መረጃ ምንጭ - World Economics
አሜሪካ በሬሚታንስ ላይ ታክስ የመጣል ዕቅድ እንዳላት ተገለፀ።

በዚህ ሳምንት ታክስን በተመለከተ በቀረበው ዕቅድ ላይ በአሜሪካ ከሚኖሩ ሰዎች ወደ ሌላ ሃገር የሚደረጉ ክፍያዎች (ሬሚታንስ) ላይ የ5 በመቶ ተብሎ ታክስ ለመጣል ታቅዷል ተብሏል።

በታክሱ አብዛኞቹ በአሜሪካ ዜጎች የሚፈፀሙ ዝውውሮች ባይካተቱም በሌሎች ሀገር ዜጎች እና አንዳንድ በአሜሪካ ዜጎች የሚላኩ ገንዘቦች ግን ታክሱ ይፈፀምባቸዋል።

በ2023 ብቻ በአሜሪካ የሚኖሩ ሰዎች ከ93 ቢሊየን ዶላር በላይ ሬሚታንስ ወደ ሀገሮቻቸው የላኩ ስለመሆኑ የዓለም ባንክ ሪፖርት ያሳያል።

እንደ ኬንያ፣ ጋና እና ናይጄሪያ ያሉ ብዙ ሬሚታንስ ተቀባይ የሆኑ አፍሪካውያንም በጉዳዩ ስጋት ገብቷቸዋል።

በእነዚህ ሀገራት ሬሚታንስ ከሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዝ ሲሆን ከሬሚታንስ የሚገኘው ገንዘብ አንዳንዴ በእርዳታ እና ኢንቨስትመንት መልኩ ከሚያገኙት ገንዘብ ጭምር እንደሚበልጥም ተነግሯል።

ኢትዮጵያ በ2023/24 ከሬሚታንስ 6 ቢሊየን ዶላር ያገኘች ሲሆን ታክሱ ተግባራዊ ከሆነ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታት ይሆናል።

Source: tikvahethmagazine
@Etstocks