ET Securities
646 subscribers
572 photos
7 videos
26 files
287 links
At Et securities our aim is in creating condusive space concerning capital markets and financial markets so as to enable learning and awareness creation to the society.

Support us https://t.me/boost/Etstocks

https://www.youtube.com/@etstocks
Download Telegram
ባንኮች 1.3 ቢሊዮን ብር ተጭበርበሩ‼️
28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መጭበርበራቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርትን ጠቅሶ የፌደራል የሥነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሞሽን ይፋ አደረገ፡፡

የባንኩ ሪፖርት እስከ ሰኔ 2024 ድረስ ያሉ የገንዘብ እንቅስቀሴዎች ዙሪያ ትኩረቱን አድርጓል፡፡

ባንኩ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በአጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን አጥተዋል ብሏል።

የማጭበርበር ድርጊቶቹ የተፈጸሙት በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች፣ በተሰረቁ የኤትኤም ማሽኖች፣ በሐሰተኛ ቼኮች፣ በሐሰተኛ የስልክ መልዕክት እና ተያያዥ መንገዶች አማካኝነት ነው፡፡

በዚህ ዓመት ባንኮች ያጡት ገንዘብ ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ300 ሚሊዮን ብር ጭማሪ እንዳሳየም በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ካሉ 31 ባንኮች ውስጥ 28ቱ ሲጭበረበሩ የቀሪዎቹ ሶስት ባንኮች ማንነት ግን በሪፖርቱ ላይ አልተጠቀሰም፡፡

ባንኮች ከአነስተኛ የብድር እና ቁጠባ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ብድሮችን እየሰጡ ነው የተባለ ሲሆን ይህ አገልግሎት እየጨመረ መሄድ እና የበይነ መረብ ማጭበርበሮች መበራከት ባንኮች የሚያጡት ገንዘብ ሊጨምር እንደሚችል ብሔራዊ ባንክ በሪፖርቱ ላይ ጠቅሷል፡፡

@Etstocks
#ለመረጃ፡ የዚህ ዓመት የአፍሪካ ሀገራት የGDP እድገት ምጣኔ ትንበያ በቅደም ተከተል (IMF)!

ሴኔጋል: 8.4%
ሩዋንዳ: 7.1%
ጊኒ፡ 7.1%
ኢትዮጵያ: 6.6%
ቤኒን: 6.5%
ደቡብ ሱዳን፡ -4.3%

የደቡብ ሱዳን ህዝብ የIMF ትንበያን ተመልክቶ የሚጓጓውን ፖለቲከኞቹ በዜሮ ያጣፉበታል!

ዓምና ከ25% በላይ ታድግ ይሆናል የተባለላት ደቡብ ሱዳን ወደ ግጭት ገብታ ከዜሮ በታች 27% አድጋ ነው አዲሱ ዓመት የጀመረው!

IMF ደቡብ ሱዳን ዘንድሮ ከዜሮ በታች በ4.3% ታድግና በቀጣይ ዓመት ሰላም ሆና ከበረታች በ64.5% ታድጋለች እያለ ነው!
#Vacancy Wegagen Capital Investment Bank is hiring.

Open Positions:

1. Sr. Securities Rating Officer
2. Sr. Securities Appraisal Officer
3. Sr. Securities Research Officer

Deadline: May 3, 2025
@Etstocks
ET Securities pinned «https://youtu.be/iAAXilq1e1o?si=pbFroYwRuVg5lhJc»
" ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች (ነጋዴዎችና ወኪሎች አነስተኛ ንግድ) ቢዝነስ እንዲጀምሩ ወይም እዲያስፋፉ በዋስትና እና ያለዋስትና እስከ 1.2 ሚሊየን ብር የሚደርስ ብድር ማግኘት ያስችላቸዋል " - ኢትዮ ቴሌኮም

ኢትዮ ቴሌኮም በሲንቄ ባንክ የ15 ቢሊየን ብር የፋይናንስ ድጋፍ አቅራቢነት አዳዲስ የፋይናንስ ፕሮዳክቶችን የማስተዋወቅ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት አከናውኗል።

ይፋ የተደረጉት ፕሮዳክቶች በቴሌ ብር ሱፐር አፕ ' Financial service with Siinqee ' ስር የሚገኙ አራት ፕሮዳክቶች ናቸው።

አገልግሎቶቹ ፦
- ወቢ የብድር አገልግሎት ፣
- የትናንሽ እና የመካከለኛ ብድር አገልግሎት(SME) ፣
- የማይክሮ ሴቪንግ
- የዲቫይስ ፋይናኒስንግ አገልግሎቶች ናቸው።

የብድር አገልግሎቶቹ የሚቀርቡት ደንበኞች በቴሌ ብር ላይ ባደረጓቸው የገንዘብ እንቅስቃሴዎች ታይተው በሚቀመጥላቸው የብድር ጣሪያ መሰረት እንደየአቅማቸው ይሆናል ተብሏል።

ሲንቄ ባንክ ካቀረበው 15 ቢሊየን ብር ውስጥ 10 ቢሊየን ብር የሚሆነው ትናንሽ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ለማስፋፋት የብድር አገልግሎት የሚውል ገንዘብ ነው።

ብድሩ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል መንገድ በቴሌ ብር ሱፕር አፕ አማካኝነት የሚከናወን ሲሆን በማስያዣ እና ያለ ማስያዣ ይከናወናል ተብሏል።

ከሲንቄ ባንክ ጋር በተደረገ ስምምነት ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች (ነጋዴዎችና ወኪሎች አነስተኛ ንግድ) ቢዝነስ እንዲጀምሩ ወይም እዲያስፋፉ በዋስትና እና ያለዋስትና እስከ 1.2 ሚሊየን ብር ብድር ማግኘት እንደሚያስችል ተገልጿል። በዚህ አገልግሎትም በዓመት እስከ 10 ቢሊዮን ብር እንደሚቀርብ ተመላክቷል።

በዓመት 960 ሺህ ዲቫይሶችን (የሞባይል ቀፎዎችን) ሲያቀርብ መቆየቱን የገለጸው ኢትዮ ቴሌኮም በአሁኑ የሲንቄ ባንክ ስምምነት መሰረት በዓመት እስከ 2 ሚሊየን ዲቫይሶችን እንደሚያቀርብ ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
#Vacancy
CBE Capital Investment Bank is hiring a Chief Compliance Officer. See the details above.

LinkedIn | YouTube | X | Facebook | TikTok
𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 𝗧𝗼 𝗢𝗽𝗲𝗻 𝗥𝗲𝗮𝗹 𝗘𝘀𝘁𝗮𝘁𝗲 𝗠𝗮𝗿𝗸𝗲𝘁 𝘁𝗼 𝗙𝗼𝗿𝗲𝗶𝗴𝗻𝗲𝗿𝘀 𝗜𝗻 𝗡𝗲𝘄 𝗗𝗿𝗮𝗳𝘁 𝗟𝗮𝘄

The Council of Ministers has approved a draft law that would allow foreigners to own immovable property—part of a broader effort to attract foreign capital, expand housing access, and spur job creation. The Council also ratified major international agreements, including interest-free development loans from Italy and the World Bank, Ethiopia’s accession to the African Finance Corporation, and implementation of the African Continental Free Trade Area tariff reduction. A new air transport deal with Austria and updated service fee regulations were also approved.

Source - ERB
@Etstocks
From Ledger to Leadership.pdf
351.6 KB
An articulated and yet very recommended piece of article. Worth reading!!

From Ledger to Leadership: Transforming Ethiopia's Finance Professionals
ለአምስተኛው ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 60 ሚሊዮን ዶላር ለሽያጭ ማቅረቡን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል! ጨረታው ዛሬ እስከ 6 ሰዓት ይከናወናል!
ኢብባ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ፡- የተመዘነ አማካይ ዋጋ በ132.9643 ብር በአንድ ዶላር

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያደርገውን የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት ዛሬ ይፋ አድርጓል።

ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው ማስታወቂያ መሠረት በጨረታው አሸናፊ የሆኑት ሁሉም አማካኝ ዋጋ በዶላር 132.9643 ብር ነበር።

በጨረታው የውጪ ምንዛሪ ድልድል ጥያቄዎችን በማቅረብ በአጠቃላይ 16 ባንኮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክም በቀጣይ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የሚካሄድበትን መርሃ ግብር አመልክቷል። የሚቀጥለው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ይካሄዳል።
ኤርሚያስ አመልጋን ጨምሮ ህገወጥ የገንዘብ ማሰባሰብ ላይ ምርመራ ተጀመረ - የካፒታል ገበያ ባለስልጣን

የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ታዋቂውን ስራ ፈጣሪ አቶ ኤርሚያስ አመልጋን እና "ጀነሲስ ኢንቨስትመንት ሰርቪስ" የተባለ ኩባንያን ጨምሮ ህገወጥ በሆነ መንገድ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮችን ለህዝብ በመሸጥ ገንዘብ ሲያሰባስቡ በነበሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ የቀረቡ ቅሬታዎችን ተቀብሎ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ በሰጠው መግለጫ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ህገወጥ የሰነድ ሽያጭን በመጠቀም ከህዝብ ገንዘብ በማሰባሰብ ተግባር ላይ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ገልጿል።

በተለይም በአቶ ኤርሚያስ አመልጋ እና በ"ጀነሲስ ኢንቨስትመንት ሰርቪስ" ኩባንያ ላይ እየተካሄዱ ያሉት ምርመራዎች በህገ መንግስት የተረጋገጠ የመሰማት እና የመከላከል ሙሉ መብታቸው በተጠበቀ ሁኔታ እንደሚከናወኑ ባለስልጣኑ አረጋግጧል።

በተጨማሪም ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ከካፒታል ገበያ ጋር በተያያዙ እንቅስቃሴዎች ላይ ሲሳተፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል።

በተለይም በንግድ ድርጅቶች ምስረታ ላይ ሲሳተፉ የንግድ ምዝገባ እና ምስረታ ሰነዶችን ከሚመለከተው አካል እንዲያረጋግጡ እንዲሁም ገንዘብ ከመክፈላቸው በፊት በባለስልጣኑ ፈቃድ ከተሰጣቸው የኢንቨስትመንት አማካሪዎች ብቻ ምክር እንዲፈልጉ ጠቁሟል።

ባለስልጣኑ ፈቃድ ሳይኖራቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት የሚሰጡ ወይም ለማቅረብ የሚሞክሩ አካላት ካሉ ለባለስልጣኑ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ በእንደዚህ አይነት ህገ-ወጥ ድርጊቶች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ አረጋግጧል።

Source: capitalethiopia
@Etstocks
#Vacancy

If you are passionate in regulatory compliance, market oversight, or financial supervision, and want to contribute to building a strong, transparent capital market in Ethiopia—this is your opportunity!

Apply now using the below link.
https://ethiojobs.net/job/fV61CpAz5Q-market-supervision-officer