1699114161827.pdf
355.4 KB
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ረቂቅ የክፍያ መመሪያ ለህዝብ ምክክር ወጥቷል።
አስተያየትዎን እና ጥያቄዎን ወደ፡ Communications@ecma.gov.et እንዲልኩ የEthiopian Capital Market Authority ጠይቋል።
አስተያየትዎን እና ጥያቄዎን ወደ፡ Communications@ecma.gov.et እንዲልኩ የEthiopian Capital Market Authority ጠይቋል።
የአክሲዮን ዋጋ ምንድን ነው?
የአክሲዮን ዋጋ የሚለው ስያሜ የሚያመለክተው የአክሲዮን ድርሻ በገበያ ላይ የሚነግደውን የአሁኑን ዋጋ ነው።
የአክሲዮን ዋጋ
እያንዳንዱ የሕዝብ ንግድ ኩባንያ ድርሻው ሲወጣ ዋጋ ይሰጠዋል ፤ ይህም የኩባንያውን ዋጋ በሚገባ የሚያንጸባርቅ ነው ። በአጠቃላይ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚከሰቱ ለውጦችን፣ በኢንዱስትሪዎች ውስጥ የሚከሰቱ ለውጦችን፣ የፖለቲካ ክስተቶችን፣ ጦርነትን እና የአካባቢ ለውጥን ጨምሮ የአክሲዮን ዋጋ ከተለያየ ምክንያቶች ጋር ሲነፃፀር ዝቅ ይላል።
የአንድ ኩባንያ የአክሲዮን ዋጋ መቀየር
ማንኛውም የአክሲዮን ዋጋ ለውጥ ከሚያደርጉ ሌሎች ነገሮች በተጨማሪ በአንድ ኩባንያ ውስጥ የአክሲዮን ዋጋው ወደ ሁለቱም አቅጣጫ እንዲቀየር የሚያደርጉ ጉዳዮች ሊኖሩ ይችላሉ።
1. የአቅርቦትና የፍላጎት ሕግ
አንድ ኩባንያ ሌሎች ብዙ ምርታ ወይም ከፍተኛ ፍላጎት ወይም አስፈላጊ የሆነ ጥሩ ምርት የሚያመርት ከሆነ ተፈላጊነቱ ከፍተኛ በመሆኑ የአክስዮን ዋጋ ይጨምራል። ጥሩው አቅርቦት ከተፈላጊነቱ ጋር በሚመጣጠንበት ጊዜ የአክሲዮን ዋጋ ከፍተኛ ይሆናል። አቅርቦቱ ከተፈላጊው በላይ ከሆነ የኩባንያው ድርሻ ዋጋ ሊቀንስ ይችላል።
በተጨማሪም ኩባንያው ጥሩውን ምርት ውጤታማና ልዩ በሆነ መንገድ በማምረት ላይ የተመካ ነው ። በአሮጌ መስፈርት ላይ ልዩነት ከፈጠሩ፣ የድርሻቸው ዋጋ ከፍ ያለ ቢሆንም እንኳ ተመሳሳይ ሆኖ ሊቆይ ወይም ሊጨምር ይችላል።
በመጨረሻም, በእርግጥ ስለ አቅርቦት እና ፍላጎት ሕግ ነው.
2. አስተዳደር ወይም የምርት ለውጥ
በአስተዳደር ወይም በምርት ላይ የሚከሰቱ ለውጦችም የአንድ ኩባንያ ድርሻ ዋጋ ከፍ እንዲል ወይም እንዲቀንስ ሊያደርጉ ይችላሉ። ኩባንያው ውጤታማና ውጤታማ በሆነ መንገድ በሚተዳደርበትና ሸቀጦችን በሚመረትበት መንገድ ላይ የተመካ ነው ። የአስተዳደር ቡድን፣ የአጻጻፍ ስልት ወይም ሸቀጦች እንዴት እንደሚመረቱ መለወጥ ውጤታማነትን እና አጠቃላይ ውጤታማነትን ሊጨምር ይችላል - ትርፍ መጨመር እና የሽያጭ ዋጋ እንዲጨምር ያደርጋል። ይሁን እንጂ አሉታዊ ለውጦች ፍጹም ተቃራኒ ውጤት ሊያስከትሉ ይችላሉ።
3. የኩባንያውን ስም መጥቀስ
በአክሲዮን ዋጋ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችል ሌላው የማስታወሻ ነጥብ ደግሞ ኩባንያው ስም በዜና፣ በማህበራዊ ሚዲያ ወይም በቃል መጠቀሱ ነው። በተለይ ከሁለት ክንውኖች መካከል አንዱን ማለትም ቅሬታን ወይም ስኬትን በተመለከተ ነው ።
ቅሌቶች – እውነተኛ ወይም እውነት ያልሆኑ – ከአሉታዊ ነገር ጋር በመዛመድ ብቻ የአንድ ኩባንያ ድርሻ ዋጋ እንዲቀንስ ሊያደርጉ ይችላሉ. በተጨማሪም, በገበያ ወይም በየኢንዱስትሪው ውስጥ አንድ ግኝት ጋር መገናኘት, ወይም ተጠያቂ መሆን አብዛኛውን ጊዜ የአክሲዮን ዋጋ እንዲጨምር ያደርጋል.
የአክሲዮን ዋጋ፣ ገቢና ባለድርሻ አካላት
የአክሲዮን ዋጋ በመጀመሪያ የሚወሰነው አንድ ኩባንያ ለመጀመሪያ ጊዜ ድርሻውን ወደ ገበያ በሚያስገባበት ጊዜ መጀመሪያ ላይ በሕዝብ ፊት በሚያቀርበው መዋጮ (IPO) ነው። የኢንቨስትመንት ድርጅቶች የአክሲዮን ዋጋ ምን መሆን እንዳለበት ለመወሰን የተለያዩ መለኪያዎችን ይጠቀማሉ። ከዚያ በኋላ ከላይ የተጠቀሱት በርካታ ምክንያቶች የድርሻው ዋጋ ከፍ እንዲልና እንዲወድቅ ያደርጋሉ። ይህ ደግሞ በአብዛኛው ከኩባንያው ሊጠበቅ የሚችለው ገቢ ነው።
ነጋዴዎች፣ ኩባንያው የሚያገኘውን ገቢ፣ በገበያ ላይ የሚከሰቱ ለውጦችንና የሚያስገኘውን ትርፍ ጨምሮ ያለውን ዋጋ በየጊዜው ለማወቅ የገንዘብ መለኪያዎችን ይጠቀማሉ። ነጋዴዎች የሽያጭ ዋጋ ከፍ እንዲሉና እንዲቀንሱ ያደርጋል።
ነጋዴዎች በኢንቨስትመንቶቻቸው ላይ ትርፍ ለማግኘት ጥረት ያደርጋሉ። በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይከናወናል።
ዲቪደንድ– የኩባንያው አክሲዮን ትርፍ ከከፈለ ለባለድርሻ አካላት በየድርሻው ቋሚ ክፍያ ይደረጋል
በአነስተኛ ዋጋ ሲገዙ ና ዋጋው ከጨረሰ በኋላ መልሰው መሸጥ፡፡
በአጠቃላይ
አንድ የንግድ ድርጅት ለሚያወጣው ለእያንዳንዱ ድርሻ የአክሲዮን ዋጋ ይሰጣል ። ዋጋው የኩባንያው ዋጋ ነጸብራቅ ነው – ህዝብ ለአንድ ኩባንያ ለመክፈል ፈቃደኛ ነው። በዓለም አቀፉ መልክዓ ምድርና በኩባንያው ውስጥ ባሉት የተለያዩ ምክንያቶች ላይ ተመሥርቶ ሊነሳና ሊወድቅ ይችላል ፡፡
fb.me/Etstocks
የአክሲዮን ዋጋ የሚለው ስያሜ የሚያመለክተው የአክሲዮን ድርሻ በገበያ ላይ የሚነግደውን የአሁኑን ዋጋ ነው።
የአክሲዮን ዋጋ
እያንዳንዱ የሕዝብ ንግድ ኩባንያ ድርሻው ሲወጣ ዋጋ ይሰጠዋል ፤ ይህም የኩባንያውን ዋጋ በሚገባ የሚያንጸባርቅ ነው ። በአጠቃላይ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚከሰቱ ለውጦችን፣ በኢንዱስትሪዎች ውስጥ የሚከሰቱ ለውጦችን፣ የፖለቲካ ክስተቶችን፣ ጦርነትን እና የአካባቢ ለውጥን ጨምሮ የአክሲዮን ዋጋ ከተለያየ ምክንያቶች ጋር ሲነፃፀር ዝቅ ይላል።
የአንድ ኩባንያ የአክሲዮን ዋጋ መቀየር
ማንኛውም የአክሲዮን ዋጋ ለውጥ ከሚያደርጉ ሌሎች ነገሮች በተጨማሪ በአንድ ኩባንያ ውስጥ የአክሲዮን ዋጋው ወደ ሁለቱም አቅጣጫ እንዲቀየር የሚያደርጉ ጉዳዮች ሊኖሩ ይችላሉ።
1. የአቅርቦትና የፍላጎት ሕግ
አንድ ኩባንያ ሌሎች ብዙ ምርታ ወይም ከፍተኛ ፍላጎት ወይም አስፈላጊ የሆነ ጥሩ ምርት የሚያመርት ከሆነ ተፈላጊነቱ ከፍተኛ በመሆኑ የአክስዮን ዋጋ ይጨምራል። ጥሩው አቅርቦት ከተፈላጊነቱ ጋር በሚመጣጠንበት ጊዜ የአክሲዮን ዋጋ ከፍተኛ ይሆናል። አቅርቦቱ ከተፈላጊው በላይ ከሆነ የኩባንያው ድርሻ ዋጋ ሊቀንስ ይችላል።
በተጨማሪም ኩባንያው ጥሩውን ምርት ውጤታማና ልዩ በሆነ መንገድ በማምረት ላይ የተመካ ነው ። በአሮጌ መስፈርት ላይ ልዩነት ከፈጠሩ፣ የድርሻቸው ዋጋ ከፍ ያለ ቢሆንም እንኳ ተመሳሳይ ሆኖ ሊቆይ ወይም ሊጨምር ይችላል።
በመጨረሻም, በእርግጥ ስለ አቅርቦት እና ፍላጎት ሕግ ነው.
2. አስተዳደር ወይም የምርት ለውጥ
በአስተዳደር ወይም በምርት ላይ የሚከሰቱ ለውጦችም የአንድ ኩባንያ ድርሻ ዋጋ ከፍ እንዲል ወይም እንዲቀንስ ሊያደርጉ ይችላሉ። ኩባንያው ውጤታማና ውጤታማ በሆነ መንገድ በሚተዳደርበትና ሸቀጦችን በሚመረትበት መንገድ ላይ የተመካ ነው ። የአስተዳደር ቡድን፣ የአጻጻፍ ስልት ወይም ሸቀጦች እንዴት እንደሚመረቱ መለወጥ ውጤታማነትን እና አጠቃላይ ውጤታማነትን ሊጨምር ይችላል - ትርፍ መጨመር እና የሽያጭ ዋጋ እንዲጨምር ያደርጋል። ይሁን እንጂ አሉታዊ ለውጦች ፍጹም ተቃራኒ ውጤት ሊያስከትሉ ይችላሉ።
3. የኩባንያውን ስም መጥቀስ
በአክሲዮን ዋጋ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችል ሌላው የማስታወሻ ነጥብ ደግሞ ኩባንያው ስም በዜና፣ በማህበራዊ ሚዲያ ወይም በቃል መጠቀሱ ነው። በተለይ ከሁለት ክንውኖች መካከል አንዱን ማለትም ቅሬታን ወይም ስኬትን በተመለከተ ነው ።
ቅሌቶች – እውነተኛ ወይም እውነት ያልሆኑ – ከአሉታዊ ነገር ጋር በመዛመድ ብቻ የአንድ ኩባንያ ድርሻ ዋጋ እንዲቀንስ ሊያደርጉ ይችላሉ. በተጨማሪም, በገበያ ወይም በየኢንዱስትሪው ውስጥ አንድ ግኝት ጋር መገናኘት, ወይም ተጠያቂ መሆን አብዛኛውን ጊዜ የአክሲዮን ዋጋ እንዲጨምር ያደርጋል.
የአክሲዮን ዋጋ፣ ገቢና ባለድርሻ አካላት
የአክሲዮን ዋጋ በመጀመሪያ የሚወሰነው አንድ ኩባንያ ለመጀመሪያ ጊዜ ድርሻውን ወደ ገበያ በሚያስገባበት ጊዜ መጀመሪያ ላይ በሕዝብ ፊት በሚያቀርበው መዋጮ (IPO) ነው። የኢንቨስትመንት ድርጅቶች የአክሲዮን ዋጋ ምን መሆን እንዳለበት ለመወሰን የተለያዩ መለኪያዎችን ይጠቀማሉ። ከዚያ በኋላ ከላይ የተጠቀሱት በርካታ ምክንያቶች የድርሻው ዋጋ ከፍ እንዲልና እንዲወድቅ ያደርጋሉ። ይህ ደግሞ በአብዛኛው ከኩባንያው ሊጠበቅ የሚችለው ገቢ ነው።
ነጋዴዎች፣ ኩባንያው የሚያገኘውን ገቢ፣ በገበያ ላይ የሚከሰቱ ለውጦችንና የሚያስገኘውን ትርፍ ጨምሮ ያለውን ዋጋ በየጊዜው ለማወቅ የገንዘብ መለኪያዎችን ይጠቀማሉ። ነጋዴዎች የሽያጭ ዋጋ ከፍ እንዲሉና እንዲቀንሱ ያደርጋል።
ነጋዴዎች በኢንቨስትመንቶቻቸው ላይ ትርፍ ለማግኘት ጥረት ያደርጋሉ። በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይከናወናል።
ዲቪደንድ– የኩባንያው አክሲዮን ትርፍ ከከፈለ ለባለድርሻ አካላት በየድርሻው ቋሚ ክፍያ ይደረጋል
በአነስተኛ ዋጋ ሲገዙ ና ዋጋው ከጨረሰ በኋላ መልሰው መሸጥ፡፡
በአጠቃላይ
አንድ የንግድ ድርጅት ለሚያወጣው ለእያንዳንዱ ድርሻ የአክሲዮን ዋጋ ይሰጣል ። ዋጋው የኩባንያው ዋጋ ነጸብራቅ ነው – ህዝብ ለአንድ ኩባንያ ለመክፈል ፈቃደኛ ነው። በዓለም አቀፉ መልክዓ ምድርና በኩባንያው ውስጥ ባሉት የተለያዩ ምክንያቶች ላይ ተመሥርቶ ሊነሳና ሊወድቅ ይችላል ፡፡
fb.me/Etstocks
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ዓባይ ባንክ ከፍተኛ ገቢ አስመዘገበ
ዓባይ ባንክ በ2015 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ገቢ ማስመዝገቡን አስታውቋል።
ይህ የተገለፀው የባንኩ የባለአክሲዮኖች ዓመታዊ 14ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በአዲስ አበባ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ዛሬ በተካሄደበት ወቅት ነዉ።
የባንኩ ጠቅላላ የተቀማጭ ገንዘብ የ29 በመቶ ዓመታዊ ዕድገት በማስመዝገብ 41 ነጥብ 8 ቢሊዮን መድረሱን ተገልጿል፡፡
Fb.me/etstocks
ዓባይ ባንክ በ2015 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ገቢ ማስመዝገቡን አስታውቋል።
ይህ የተገለፀው የባንኩ የባለአክሲዮኖች ዓመታዊ 14ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በአዲስ አበባ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ዛሬ በተካሄደበት ወቅት ነዉ።
የባንኩ ጠቅላላ የተቀማጭ ገንዘብ የ29 በመቶ ዓመታዊ ዕድገት በማስመዝገብ 41 ነጥብ 8 ቢሊዮን መድረሱን ተገልጿል፡፡
Fb.me/etstocks
#StockMarket
ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ የ ' ስቶክ ማርኬት ' ስራ እንደሚጀመር ተገለፀ።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የ ' ስቶክ ማርኬት ' ለመደገፍ ከወዲሁ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቅርበዋል።
ስቶክ ማርኬት በከፍተኛ ደረጃ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይደግፋል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ " በጣም ብዙ ሰው ሃሳብ አለው ገንዘብ የለውም፤ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብ የላቸውም ፤ ጥቂቶች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብም ገብቷቸዋል ተቋም የላቸውም ፤ ስቶክ ማርኬት ማለት ገንዘብ ያለውን ሃሳብ ያለውንና ተቋምን የሚያገናኝ ምርጥ ሀሳብ ማለት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ለአብነት ፦
- በአረብ ሀገራት ያሉ እህቶች ' ስቶክ ማርኬት ' ውስጥ ሼር ገዝተው እዛ እየሰሩ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚችሉ ፤
- አርሶ አደሮችም ከስቶክ ማርኬት ሼር ገዝተው እያረሱ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ ፤
- ዲያስፖራዎችም ወደ ሀገር ሲመለሱ ምንም የሌላቸው እንዳይሆኑ ከወዲሁ ዋና ዋና ኩባንያዎች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ " ሲሉ ተናግረዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፤ ቴሌኮሚኒኬሽን በቅርቡ የተወሰነ ፐርሰንት ለህዝቡ እንደሚሸጥ አሳውቀዋል።
በሂደት ቴሌን፣ አየር መንገድን የህዝብ ተቋማት የማድረግ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።
" እኛ ሂልተንንም፣ ጊዮንንም፣ አየር መንገድንም፣ ቴሌኮምን ይዘን አንዘልቀውም " ያሉ ሲሆን እነዚህ ኩባንያዎች ላይ ብዙዎች ኢንቨስት እንዲያደርጉበት ካደረግን የተሻለ እድገት ሊያመጡ ይችላሉ፤ ለኢትዮጵያ እድገትም እገዛ ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት ምክር ቤቱ ከወዲሁ ድጋፍ ለማድረግ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።
#etstocks
ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርቡ የ ' ስቶክ ማርኬት ' ስራ እንደሚጀመር ተገለፀ።
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በኢትዮጵያ የሚጀምረውን የ ' ስቶክ ማርኬት ' ለመደገፍ ከወዲሁ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቅርበዋል።
ስቶክ ማርኬት በከፍተኛ ደረጃ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይደግፋል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ " በጣም ብዙ ሰው ሃሳብ አለው ገንዘብ የለውም፤ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብ የላቸውም ፤ ጥቂቶች ደግሞ ገንዘብ አላቸው ሃሳብም ገብቷቸዋል ተቋም የላቸውም ፤ ስቶክ ማርኬት ማለት ገንዘብ ያለውን ሃሳብ ያለውንና ተቋምን የሚያገናኝ ምርጥ ሀሳብ ማለት ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ለአብነት ፦
- በአረብ ሀገራት ያሉ እህቶች ' ስቶክ ማርኬት ' ውስጥ ሼር ገዝተው እዛ እየሰሩ ኢንቨስት ማድረግ እንደሚችሉ ፤
- አርሶ አደሮችም ከስቶክ ማርኬት ሼር ገዝተው እያረሱ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ ፤
- ዲያስፖራዎችም ወደ ሀገር ሲመለሱ ምንም የሌላቸው እንዳይሆኑ ከወዲሁ ዋና ዋና ኩባንያዎች ላይ ኢንቨስት ማድረግ ይችላሉ " ሲሉ ተናግረዋል።
ዶ/ር ዐቢይ ፤ ቴሌኮሚኒኬሽን በቅርቡ የተወሰነ ፐርሰንት ለህዝቡ እንደሚሸጥ አሳውቀዋል።
በሂደት ቴሌን፣ አየር መንገድን የህዝብ ተቋማት የማድረግ ስራ እንደሚሰራ አመልክተዋል።
" እኛ ሂልተንንም፣ ጊዮንንም፣ አየር መንገድንም፣ ቴሌኮምን ይዘን አንዘልቀውም " ያሉ ሲሆን እነዚህ ኩባንያዎች ላይ ብዙዎች ኢንቨስት እንዲያደርጉበት ካደረግን የተሻለ እድገት ሊያመጡ ይችላሉ፤ ለኢትዮጵያ እድገትም እገዛ ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል።
ለዚህም ተግባራዊነት ምክር ቤቱ ከወዲሁ ድጋፍ ለማድረግ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።
#etstocks
#StockMarket
(የኢትዮጵያን ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳዮችን በቅርበት በሚከታተሉት አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ በአንድ ወቅት ለቢቢሲ ድረገፅ ከሰጡት ቃለምልልስ የተወሰደ)
ስቶክ ገበያ ምንድነው ?
ለስቶክ ማርኬት ‘ የድርሻ ገበያ ’ የሚል አቻ የአማርኛ ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን።
ኩባንያዎች የኩባንያውን የባለቤትነት ድርሻ ለገበያ ያቀርባሉ።
ሰዎች ይህን ድርሻ ከገዙ በኋላ ኩባንያው ትርፋማ በሆነ መጠን ያላቸውን ድርሻ መልሰው በመሸጥ ወይም ከትርፍ ክፍፍል ትርፋማ የሚያደርግ አሠራር ነው።
ስቶክ ማርኬት ለኢትዮጵያ ምን ይዞ ይመጣል ?
የስቶክ ገበያ በዋናነኝነት ለኢትዮጵያ የሚከተሉትን ጥቅሞች ይዞ ይመጣል።
1. የካፒታል ገበያ
በርካታ የአገር ውስጥ ባንክ እንዲሁም ኢንሹራንሶች ሲመሠረቱ እና ከምሥረታቸውም በኋላ የአክሲዮን ድርሻዎችን ሲሸጡ ቆይረዋል።
የስቶክ ገበያን ከዚህ የተለየ የሚያደርገው ፤ ይፋዊ በሆነ መልኩ ተደራጅቶ ቁጥጥር እየተገደረገበት በግልጽ መገበያየት ማስቻሉ ነው።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ እውን ሲሆን ፤ ባንኮች እና ኢንሹራንሶች ሲቋቋሙም ሆነ ማስፋፋት ሲፈልጉ አክሲዮን ለመሸጥ ይከተሉት የነበረውን ረዥም መንገድ ያሳጥርላቸዋል።
እነዚህ ኩባንያዎች ሲቋቋሙ ስቶክ ኤክስቼንጅ ስላልነበረ በጣም ረዥም ሂደት በማለፍ ለእያንዳንዱ ሰው እየዞሩ ነው ሼር የሚሸጡት።
ይህ ረዥም ጊዜ እና ገንዘብ ይወስዳል። አዋጭም አይደለም።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ አንዱ ጥቅም አዲስ ለመሚሠረቱም ሆነ ለነባር ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን መፍጠሩ ነው።
ካፒታል ማሰባሰብ ለሚፈልጉ ስቶክ ገበያ መልካም አማራጭ ነው።
ጥሩ ሐሳብ ኖሯቸው የካፒታል እጥረት ላለባቸው ሰዎች ይጠቅማል።
ዛሬ ላይ ከባንክ ብድር ማግኘትም ቀላል አይለደም። ለዘመድ ወይም ለጓደኛ ሼር የመሸጥ ሂደት ቀላል አይደለም። ስቶክ ማርኬት አዲስ ለሆኑም ይሁን መስፋፋት ለሚፈልጉ ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን ይፈጥራል።
2. ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል
የስቶክ ገበያ ፣ ፍትሐዊ እና ተመጣጣኝ በሆነ ሁኔታ ሀብት ማከፋፈል የሚችል ሥርዓት ነው።
በአሁኑ ጊዜ ግዙፍ መንግሥታዊ ኩባንያዎች ወደ ግሉ ዘርፍ እየተሸጋገሩ ነው።
እነዚህ ከመንግሥት ወደ ግሉ የሚዘዋወሩት ግዙፍ ኩባንያዎችን ሲገዙ የቆዩት ጥቂት ግለሰቦች እና ኮርፖሬሽኖች ናቸው። ስቶክ ማርኬት ሲመጣ ግን መንግሥት የሕዝብን ሀብት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ማከፋፈል ይችላል።
ስቶክ ማርኬት ላይ 1 ሼር በአምስትም፣ በአሥርም ዶላር ሲሸጥ ሁሉም የየአቅሙን በመግዛት ኢትዮጵያ ያካበተችውን ሀብት ማከፋፈል ይቻላል።
እነዚህ ወደ ግሉ ዘርፍ የሚዘዋወሩ ኩባንያዎች ወደ ስቶክ ገበያው ሲገቡ፣ ሁሉም የአቅሙን ያህል ባለቤት ይሆናል። ይህም የሀብት ክፍፍልን ያመጣል።
3. ቁጠባ እና የኢንቨስትመንት አማራጭን ማስፋት
የቁጠባ ባህልን ከፍ ያደርጋል። ሰዎች በአሁኑ ጊዜ ኪሳራ አያስከትልም ብለው በሚያስቡት ዘርፍ ላይ ብቻ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ ይገኛሉ።
ገንዘብ ያላቸው ሰዎች #የቤቶች_ልማት ላይ ብቻ ትኩረት ሲያደርጉ ይታያል። የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ደግሞ ተጎድቷል። ይህም ኢንቨስት የሚደረግባቸው ዘርፎችን ውስን በማድረግ የቁጠባ አለመመጣጠን ይፈጥራል።
ስቶክ ማርኬቱ ግን ውጤታማ በሆነ መንገድ ካፒታል በሁሉም ዘርፎች ላይ ማሰራጨት ያስችላል።
4. ግልጽነት
የድርሻ ገበያዎችን በቀላሉ፣ ግልጸኝነት በሰፈነበት መልኩ መግዛት እና መሸጥ ማስቻሉ ነው።
ምን ያህል ሼር በምን ያህል ዋጋ ለገበያ እንደቀረበ ግልጽ ነው።
ሰዎች ስልካቸው ላይ በሚጭኑት መተግበሪያ በቀላሉ የገበያ ድርሻዎችን መግዛት እና የገዙትንም መሸጥ ይችላሉ።
የባንክ ባለ አክሲዮኖች ዓመት ጠብቀው ትርፍ ከመከፋፈል ውጪ በቀላሉ ያላቸውን አክሲዮን መሸጥ አይቻላቸውም።
ስቶክ ማርኬት ሲሆን በቀላሉ አክሲዮን የመሸጥ ዕድል ይዘረጋል።
በስቶክ ገበያ ትርፍና ኪሳራ እንዴት ያጋጥማል ?
ይህንን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት ስቶክ ገበያ ምንድን ነው ? እንዴትስ መሸጥ እና መለወጥ ይቻላል ? የሚለውን እንመልከት።
ስቶክ ገበያን በቀላል ቋንቋ ለመረዳት የምጣሄ ሀብት ባለሙያዎች አዘወትረው የሚጠቀሙትን ቀላል ምሳሌ እንውሰድ። 'ሀ'፣ 'ለ' እና 'ሐ' የሚባሉ ሦስት ምናባዊ የሞባይል ስልክ አምራች ኩባንያዎችን አሉ አንበል።
እርስዎ 6 ዶላር አውጥተው ከእያንዳንዱ ኩባንያ የሁለት ዶላር የገበያ ድርሻ ይገዛሉ።
'ሀ' ለገበያ ያቀረበው ሞባይል ስልክ ባትሪ እየፈነዳ ሰዎችን ለጉዳት እየዳረገ መሆኑን የሚያመለክት ሪፖርት መውጣት ይጀምራል።
የ'ለ' ኩባንያ የሆነው ምርት ደግሞ ባትሪ በፍጥነት እያለቀ ከተጠቃሚዎች ቅሬታ ይደርሰዋል።
የ'ሐ' ምርት የሆነው ሞባይል ስልክ ግን በአግባቡ ይሠራል።
ይህ በገበያ ላይ ያጋጠመው ክስተት በሦስቱ ኩባንያዎች ስቶክ ገበያ ዋጋ ላይ ለውጥ ያመጣል። የአንድ ኩባንያ ምርት ጥራት ሲወርድ የዚያ ኩባንያ ፈላጊዎች ይቀንሳሉ።
በተቀራኒው አንድ ኩባንያ ትርፍማ የሚያደርገውን ውሳኔ ወስኖ ትርፍ ሲያጋብስ፣ የትርፉ ተቋዳሽ መሆን የሚሹ ሰዎች ቁጥር ከፍ ይላል።
በዚህ መሠረት ባትሪው እየፈነዳ ሰዎችን ለአደጋ እያጋለጠ ያለው የሞባይል ኩባንያ ድርሻ በከፍተኛ መጠን ሊወርድ ይችላል።
በሁለት ዶላር የገዙትን ድርሻ መልሰው መሸጥ ቢፈልጉ ከግማሸ ባነሰ ዋጋ እንኳን የሚገዛዎትን ላያገኙ ይችላሉ።
ይህ ሞባይል አምራች ኩባንያ ሲከስር እርስዎም የኩባንያው ባለድርሻ እንደመሆንዎ ኪሳራ ያጋጥምዎታል።
ስለዚህ በኩባንያ 'ሀ' ላይ ያደረጉት ኢንቨስትመንት ኪሳራን ያስከትላል።
የ 'ሐ' ምርት የሆነው ስልክ ግን በገበያ ተፈላጊነቱ ሲጨምር የኩባንያው ዋጋም ከፍ ይላል።
ምናልባት በሁለት ዶላር የገዙትን የኩባንያውን ድርሻ፣ አሁን ላይ በ4 ዶላር ሸጠው ትርፍ ሊያገኙ ይችላሉ።
@etstocks
(የኢትዮጵያን ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳዮችን በቅርበት በሚከታተሉት አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ በአንድ ወቅት ለቢቢሲ ድረገፅ ከሰጡት ቃለምልልስ የተወሰደ)
ስቶክ ገበያ ምንድነው ?
ለስቶክ ማርኬት ‘ የድርሻ ገበያ ’ የሚል አቻ የአማርኛ ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን።
ኩባንያዎች የኩባንያውን የባለቤትነት ድርሻ ለገበያ ያቀርባሉ።
ሰዎች ይህን ድርሻ ከገዙ በኋላ ኩባንያው ትርፋማ በሆነ መጠን ያላቸውን ድርሻ መልሰው በመሸጥ ወይም ከትርፍ ክፍፍል ትርፋማ የሚያደርግ አሠራር ነው።
ስቶክ ማርኬት ለኢትዮጵያ ምን ይዞ ይመጣል ?
የስቶክ ገበያ በዋናነኝነት ለኢትዮጵያ የሚከተሉትን ጥቅሞች ይዞ ይመጣል።
1. የካፒታል ገበያ
በርካታ የአገር ውስጥ ባንክ እንዲሁም ኢንሹራንሶች ሲመሠረቱ እና ከምሥረታቸውም በኋላ የአክሲዮን ድርሻዎችን ሲሸጡ ቆይረዋል።
የስቶክ ገበያን ከዚህ የተለየ የሚያደርገው ፤ ይፋዊ በሆነ መልኩ ተደራጅቶ ቁጥጥር እየተገደረገበት በግልጽ መገበያየት ማስቻሉ ነው።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ እውን ሲሆን ፤ ባንኮች እና ኢንሹራንሶች ሲቋቋሙም ሆነ ማስፋፋት ሲፈልጉ አክሲዮን ለመሸጥ ይከተሉት የነበረውን ረዥም መንገድ ያሳጥርላቸዋል።
እነዚህ ኩባንያዎች ሲቋቋሙ ስቶክ ኤክስቼንጅ ስላልነበረ በጣም ረዥም ሂደት በማለፍ ለእያንዳንዱ ሰው እየዞሩ ነው ሼር የሚሸጡት።
ይህ ረዥም ጊዜ እና ገንዘብ ይወስዳል። አዋጭም አይደለም።
የኢትዮጵያን ሴኪዩሪቲስ ኤክስቼንጅ አንዱ ጥቅም አዲስ ለመሚሠረቱም ሆነ ለነባር ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን መፍጠሩ ነው።
ካፒታል ማሰባሰብ ለሚፈልጉ ስቶክ ገበያ መልካም አማራጭ ነው።
ጥሩ ሐሳብ ኖሯቸው የካፒታል እጥረት ላለባቸው ሰዎች ይጠቅማል።
ዛሬ ላይ ከባንክ ብድር ማግኘትም ቀላል አይለደም። ለዘመድ ወይም ለጓደኛ ሼር የመሸጥ ሂደት ቀላል አይደለም። ስቶክ ማርኬት አዲስ ለሆኑም ይሁን መስፋፋት ለሚፈልጉ ኩባንያዎች የካፒታል ገበያን ይፈጥራል።
2. ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል
የስቶክ ገበያ ፣ ፍትሐዊ እና ተመጣጣኝ በሆነ ሁኔታ ሀብት ማከፋፈል የሚችል ሥርዓት ነው።
በአሁኑ ጊዜ ግዙፍ መንግሥታዊ ኩባንያዎች ወደ ግሉ ዘርፍ እየተሸጋገሩ ነው።
እነዚህ ከመንግሥት ወደ ግሉ የሚዘዋወሩት ግዙፍ ኩባንያዎችን ሲገዙ የቆዩት ጥቂት ግለሰቦች እና ኮርፖሬሽኖች ናቸው። ስቶክ ማርኬት ሲመጣ ግን መንግሥት የሕዝብን ሀብት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ማከፋፈል ይችላል።
ስቶክ ማርኬት ላይ 1 ሼር በአምስትም፣ በአሥርም ዶላር ሲሸጥ ሁሉም የየአቅሙን በመግዛት ኢትዮጵያ ያካበተችውን ሀብት ማከፋፈል ይቻላል።
እነዚህ ወደ ግሉ ዘርፍ የሚዘዋወሩ ኩባንያዎች ወደ ስቶክ ገበያው ሲገቡ፣ ሁሉም የአቅሙን ያህል ባለቤት ይሆናል። ይህም የሀብት ክፍፍልን ያመጣል።
3. ቁጠባ እና የኢንቨስትመንት አማራጭን ማስፋት
የቁጠባ ባህልን ከፍ ያደርጋል። ሰዎች በአሁኑ ጊዜ ኪሳራ አያስከትልም ብለው በሚያስቡት ዘርፍ ላይ ብቻ መዋዕለ ንዋያቸውን እያፈሰሱ ይገኛሉ።
ገንዘብ ያላቸው ሰዎች #የቤቶች_ልማት ላይ ብቻ ትኩረት ሲያደርጉ ይታያል። የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ደግሞ ተጎድቷል። ይህም ኢንቨስት የሚደረግባቸው ዘርፎችን ውስን በማድረግ የቁጠባ አለመመጣጠን ይፈጥራል።
ስቶክ ማርኬቱ ግን ውጤታማ በሆነ መንገድ ካፒታል በሁሉም ዘርፎች ላይ ማሰራጨት ያስችላል።
4. ግልጽነት
የድርሻ ገበያዎችን በቀላሉ፣ ግልጸኝነት በሰፈነበት መልኩ መግዛት እና መሸጥ ማስቻሉ ነው።
ምን ያህል ሼር በምን ያህል ዋጋ ለገበያ እንደቀረበ ግልጽ ነው።
ሰዎች ስልካቸው ላይ በሚጭኑት መተግበሪያ በቀላሉ የገበያ ድርሻዎችን መግዛት እና የገዙትንም መሸጥ ይችላሉ።
የባንክ ባለ አክሲዮኖች ዓመት ጠብቀው ትርፍ ከመከፋፈል ውጪ በቀላሉ ያላቸውን አክሲዮን መሸጥ አይቻላቸውም።
ስቶክ ማርኬት ሲሆን በቀላሉ አክሲዮን የመሸጥ ዕድል ይዘረጋል።
በስቶክ ገበያ ትርፍና ኪሳራ እንዴት ያጋጥማል ?
ይህንን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት ስቶክ ገበያ ምንድን ነው ? እንዴትስ መሸጥ እና መለወጥ ይቻላል ? የሚለውን እንመልከት።
ስቶክ ገበያን በቀላል ቋንቋ ለመረዳት የምጣሄ ሀብት ባለሙያዎች አዘወትረው የሚጠቀሙትን ቀላል ምሳሌ እንውሰድ። 'ሀ'፣ 'ለ' እና 'ሐ' የሚባሉ ሦስት ምናባዊ የሞባይል ስልክ አምራች ኩባንያዎችን አሉ አንበል።
እርስዎ 6 ዶላር አውጥተው ከእያንዳንዱ ኩባንያ የሁለት ዶላር የገበያ ድርሻ ይገዛሉ።
'ሀ' ለገበያ ያቀረበው ሞባይል ስልክ ባትሪ እየፈነዳ ሰዎችን ለጉዳት እየዳረገ መሆኑን የሚያመለክት ሪፖርት መውጣት ይጀምራል።
የ'ለ' ኩባንያ የሆነው ምርት ደግሞ ባትሪ በፍጥነት እያለቀ ከተጠቃሚዎች ቅሬታ ይደርሰዋል።
የ'ሐ' ምርት የሆነው ሞባይል ስልክ ግን በአግባቡ ይሠራል።
ይህ በገበያ ላይ ያጋጠመው ክስተት በሦስቱ ኩባንያዎች ስቶክ ገበያ ዋጋ ላይ ለውጥ ያመጣል። የአንድ ኩባንያ ምርት ጥራት ሲወርድ የዚያ ኩባንያ ፈላጊዎች ይቀንሳሉ።
በተቀራኒው አንድ ኩባንያ ትርፍማ የሚያደርገውን ውሳኔ ወስኖ ትርፍ ሲያጋብስ፣ የትርፉ ተቋዳሽ መሆን የሚሹ ሰዎች ቁጥር ከፍ ይላል።
በዚህ መሠረት ባትሪው እየፈነዳ ሰዎችን ለአደጋ እያጋለጠ ያለው የሞባይል ኩባንያ ድርሻ በከፍተኛ መጠን ሊወርድ ይችላል።
በሁለት ዶላር የገዙትን ድርሻ መልሰው መሸጥ ቢፈልጉ ከግማሸ ባነሰ ዋጋ እንኳን የሚገዛዎትን ላያገኙ ይችላሉ።
ይህ ሞባይል አምራች ኩባንያ ሲከስር እርስዎም የኩባንያው ባለድርሻ እንደመሆንዎ ኪሳራ ያጋጥምዎታል።
ስለዚህ በኩባንያ 'ሀ' ላይ ያደረጉት ኢንቨስትመንት ኪሳራን ያስከትላል።
የ 'ሐ' ምርት የሆነው ስልክ ግን በገበያ ተፈላጊነቱ ሲጨምር የኩባንያው ዋጋም ከፍ ይላል።
ምናልባት በሁለት ዶላር የገዙትን የኩባንያውን ድርሻ፣ አሁን ላይ በ4 ዶላር ሸጠው ትርፍ ሊያገኙ ይችላሉ።
@etstocks
የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ በቅድሚያ የወጣው አዋጅ ተፈፃሚነት ሊኖረው እንደሚገባ ተገለጸ
በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ስራ እንዲጀምሩ የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች እና ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን የወጣው አዋጅ በሚኒስትሮች ምክር ቤት እና በህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት እንሚቀርብ ተገልጿል፡፡
የብሄራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ፍቃዱ ድጋፌ እንደሚሉት ከሆነ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ስራዎቻቸውን ማከናወን እንዲችሉ የተለያየ አዋጅ እና መመሪያ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡
አቶ ፍቃዱ አክለውም የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመው መቸ እና እንዴት ወደ ሃገር ውስጥ እንደሚገቡ የተገለጸ ነገር የለም ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፉን ለውጭ ባለ ሃለሃብቶች ክፍት የማድረግ ሂደት ውስን ቁጥር ባላቸው የውጭ ባንኮች ብቻ እንደሚጀምር ከዚህ ቀደም ሲገለጽ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የውጭ ባንኮች በሚያመጡት አሰራሮች በሃገር ውስጥ ያሉ ባንኮችንም እንደሚያነቃቃ ሲገለፅ እንደነበረም የሚታወስ ነው፡፡
በኢትዮጵያ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ስራ እንዲጀምሩ የሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች እና ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን የወጣው አዋጅ በሚኒስትሮች ምክር ቤት እና በህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት እንሚቀርብ ተገልጿል፡፡
የብሄራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ፍቃዱ ድጋፌ እንደሚሉት ከሆነ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ስራዎቻቸውን ማከናወን እንዲችሉ የተለያየ አዋጅ እና መመሪያ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡
አቶ ፍቃዱ አክለውም የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመው መቸ እና እንዴት ወደ ሃገር ውስጥ እንደሚገቡ የተገለጸ ነገር የለም ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፉን ለውጭ ባለ ሃለሃብቶች ክፍት የማድረግ ሂደት ውስን ቁጥር ባላቸው የውጭ ባንኮች ብቻ እንደሚጀምር ከዚህ ቀደም ሲገለጽ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የውጭ ባንኮች በሚያመጡት አሰራሮች በሃገር ውስጥ ያሉ ባንኮችንም እንደሚያነቃቃ ሲገለፅ እንደነበረም የሚታወስ ነው፡፡
⏩⏩⏩ ካፒታል በማሰባሰብ፣ የገንዘብ ስርዓቱን በአዳዲስ ፈጠራዎች በመደገፍ እና የኢንቨስትመንት ስጋቶችን የመጋራት አሰራርን በማስፋፋት የአገሪቱን ኢኮኖሚ ልማት የሚደግፍ የካፒታል ገበያ ማቋቋም በማስፈለጉ፣
⏩⏩⏩ ኢንቨስተሮችን ለመጠበቅ እና ገበያው ፍትሃዊ፣ ተአማኒ እና ቀልጣፋ እንዲሆን የሚያስችል የቁጥጥር እና በበላይነት የመከታተል የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በማስፈለጉ፣
⏩⏩⏩ ከሕዝብ ካፒታል ለመሰብሰብ የሚፈልጉ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ አውጭዎች የሚገዙበትን ወጥ የሆኑ መስፈርቶች በህግ መደንገግ በማስፈለጉ፣
⏩⏩⏩ በሀገሪቱ የፋይናንስ ስርዓት ላይ የሚፈጠሩ መዋቅራዊ ስጋቶችን ለመለየት፣ ለመከላከል፣ እና
ለመቀነስ በካፒታል ገበያ ላይ ጠንካራ የቅርብ ክትትል እና የቅኝት ስርዓት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በማስፈለጉ፣የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣቱ ይታወቃል። ለዛሬም አዋጁን ከላይ አያይዘናል። ⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬
Et Securities Market
ድረ ገጽ: www.condoaddis.com/etstocks
ቴሌግራም t.me/Etstocks
ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Etstocks
Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCYeq9Fbfyjp37w3dsjRNY7A
Linkedin(ሊንክዲን):https://www.linkedin.com/company/etstocks
⏩⏩⏩ ኢንቨስተሮችን ለመጠበቅ እና ገበያው ፍትሃዊ፣ ተአማኒ እና ቀልጣፋ እንዲሆን የሚያስችል የቁጥጥር እና በበላይነት የመከታተል የሕግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በማስፈለጉ፣
⏩⏩⏩ ከሕዝብ ካፒታል ለመሰብሰብ የሚፈልጉ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ አውጭዎች የሚገዙበትን ወጥ የሆኑ መስፈርቶች በህግ መደንገግ በማስፈለጉ፣
⏩⏩⏩ በሀገሪቱ የፋይናንስ ስርዓት ላይ የሚፈጠሩ መዋቅራዊ ስጋቶችን ለመለየት፣ ለመከላከል፣ እና
ለመቀነስ በካፒታል ገበያ ላይ ጠንካራ የቅርብ ክትትል እና የቅኝት ስርዓት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በማስፈለጉ፣የካፒታል ገበያ አዋጅ መውጣቱ ይታወቃል። ለዛሬም አዋጁን ከላይ አያይዘናል። ⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬⏬
Et Securities Market
ድረ ገጽ: www.condoaddis.com/etstocks
ቴሌግራም t.me/Etstocks
ፌስ ቡክ፡ https://www.facebook.com/Etstocks
Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCYeq9Fbfyjp37w3dsjRNY7A
Linkedin(ሊንክዲን):https://www.linkedin.com/company/etstocks
#Daily_Event
Ethiopian Securities Exchange
Register for our upcoming webinar!
https://lnkd.in/eacHWg-9
Ethiopian Securities Exchange
Register for our upcoming webinar!
https://lnkd.in/eacHWg-9
#Treasury_Bill (የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነድ)
መንግስታት በሁለት ምክንያት የግምጃ ቤት ሰነድ ለሽያጭ ያቀርባሉ…
የመጀመሪያዊ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለመስራት የካፒታል ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላት (መንግስት ገቢ ከመሰብሰቡ በፊት ፕሮጀክቶቹ በፋይናንስ እጥረት እንዳይቆሙ ከገበያው በወለድ በመበደር ለማከናወን በማሰብ) ሲሆን…..
በሁለተኝነት በገበያው ያለውን የገንዘብ አቅርቦት እና ፍላጎት ለማመጣጠን ሲል (የገንዘብ አቅርቦትን ለመጨመር ባሰብ ጊዜ ከገበያው ሰነድ በመሸጥ መበደሩን ሲያቆም የገንዘብ አቅርቦት እንዲቀንስ ከገበያው በሰነድ በመበደር ገንዘቡን በዘዴ ይሰበስባል "ሰነድ በሰዎች እጅ ገንዘብ በማዕከላዊ ባንክ እጅ ይገባል ማለት ነው" ነው፡፡
መንግስታት የግምጃ ቤት ሰነድ በቀጥታ በራሳቸው ቻናል ለሽያጭ በጨረታም ሆነ ያለጨረታ ሊያቀርቡም ሆኑ በሁለተኛ ገበያ/በካፒታል ገበያ በኩል ለሽያጭ ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ መንግስት ለሸጠው ሰነድ መተማመኛ የሚሆን ሰርተፍኬት ለሰነድ ገዢ (ግለሰብ ወይም ድርጅት) ይሰጣል፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ ለአጭር ጊዚያት ማለትም (ከ28 ቀን እስከ 365 ቀናት የቆይታ ጊዜ ሊኖራቸው ሲችል እንደቆይታ ጊዚያቸው የወለድ መጠናቸው ሊለያይ ይችላል) የሰነዱ የክፍያ ወቅት (Maturity) ሲደርስ መንግስት ወለዱን በማሰብ ክፍያ የሚፈጽም ይሆናል፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ ወለድ አስተሳሰቡ ሁለት አይነት ዘዴ ሊኖረው ይችላል (ወለድ ማስቀመጥ (ለምሳሌ ለተገዛው ሰነድ መጠን 3 ከመቶ ወለድ ማሰብ እንደማለት) አልያም የመሸጫ እና የመክፈያ መጠን ማስቀመጥ (ለምሳሌ የ100 ብር ሰነድን በ95 ብር እንደመሸጥ አይነት (በ95 የገዛ ሰው 100 ብር ተደርጎ ይከፈለዋል እንደማለት ነው)፡፡
ሃሳቡን በቀላሉ እድትረዱት የኢትዮጲያ ልማት ባንክ የህዳሴ ግድቡን ለመገንባት ቦንድ ለህዝብ አቅርቦ ሰዎች በቻሉት መጠን በሙሉ ገዝተዋል ከአምስት ዓመታት (Maturity) በኋላ ወለድ በማሰብ ክፍያ ሲፈጽም የምትመለከቱት የእዳ ሰነድን ይወክላል (የህዳሴው ግድብ የግምጃ ቤት ሰነድ ሳይሆን እንደቆይታው በኖት እና በቦንድ ውስጥ ሊጠቃለል ይችላል (በኢትዮጲያ ሁኔታ አሁን ላይ የግምጃ ቤት ሰነድ ለልማት ድርጅቶች (የፋይናንስ ተቋማትም ይጋበዛሉ!) በሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ወደፊት የስቶክ ገበያው ሲከፈት ለጠቅላላ ገበያው ሊለቀቀቅ ይችላል፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ ከሌሎች የመንግስት የእዳ ሰነዶች አይነት የአጭር ጊዜ እዳ ነው፡፡ ሌሎቹ Treasury Note ከ1- 10 ዓመት ቆይታ ያለው ብድር ሲሆን Treasury Bond እስከ 30 ዓመት ሊቆይ የሚችል እዳ የሚይዙ ናቸው፡፡
የግምጃ ቤት ሰንድ ሻጩ መንግስት በመሆኑ ላይከፈል ይችላል/ Default የሚል ስጋት የሌለበት ነው፡፡ አንድ ሰነድ የገዛ ሰው የመክፈያው ወቅት እስኪደርስ ወለድም ሆነ የከፈለውን ገንዘብ ባያገኝም ለሌላ ሰው (በካፒታል ገበያ በኩል የመሸጥ እድል ግን ይኖረዋል)፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ በባህሪው ዝቅተኛ እና ቋሚ ወለድ የሚታሰብበት (አንዴ ለሽያጭ ከቀረበ በኋላ ዋጋ ንረትን ከግምት በመክተት የማይለዋወጥ) በመሆኑ ስጋት የሚፈጥር ሲሆን የመንግስት መተማመኛ ያለው እና በካፒታል ገበያ በኩል በቀላሉ ለሌላ ሰው መሸጥ የሚችል መሆኑ እንደ እድል ያስቆጥረዋል፡፡
መንግስታት በሁለት ምክንያት የግምጃ ቤት ሰነድ ለሽያጭ ያቀርባሉ…
የመጀመሪያዊ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለመስራት የካፒታል ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላት (መንግስት ገቢ ከመሰብሰቡ በፊት ፕሮጀክቶቹ በፋይናንስ እጥረት እንዳይቆሙ ከገበያው በወለድ በመበደር ለማከናወን በማሰብ) ሲሆን…..
በሁለተኝነት በገበያው ያለውን የገንዘብ አቅርቦት እና ፍላጎት ለማመጣጠን ሲል (የገንዘብ አቅርቦትን ለመጨመር ባሰብ ጊዜ ከገበያው ሰነድ በመሸጥ መበደሩን ሲያቆም የገንዘብ አቅርቦት እንዲቀንስ ከገበያው በሰነድ በመበደር ገንዘቡን በዘዴ ይሰበስባል "ሰነድ በሰዎች እጅ ገንዘብ በማዕከላዊ ባንክ እጅ ይገባል ማለት ነው" ነው፡፡
መንግስታት የግምጃ ቤት ሰነድ በቀጥታ በራሳቸው ቻናል ለሽያጭ በጨረታም ሆነ ያለጨረታ ሊያቀርቡም ሆኑ በሁለተኛ ገበያ/በካፒታል ገበያ በኩል ለሽያጭ ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ መንግስት ለሸጠው ሰነድ መተማመኛ የሚሆን ሰርተፍኬት ለሰነድ ገዢ (ግለሰብ ወይም ድርጅት) ይሰጣል፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ ለአጭር ጊዚያት ማለትም (ከ28 ቀን እስከ 365 ቀናት የቆይታ ጊዜ ሊኖራቸው ሲችል እንደቆይታ ጊዚያቸው የወለድ መጠናቸው ሊለያይ ይችላል) የሰነዱ የክፍያ ወቅት (Maturity) ሲደርስ መንግስት ወለዱን በማሰብ ክፍያ የሚፈጽም ይሆናል፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ ወለድ አስተሳሰቡ ሁለት አይነት ዘዴ ሊኖረው ይችላል (ወለድ ማስቀመጥ (ለምሳሌ ለተገዛው ሰነድ መጠን 3 ከመቶ ወለድ ማሰብ እንደማለት) አልያም የመሸጫ እና የመክፈያ መጠን ማስቀመጥ (ለምሳሌ የ100 ብር ሰነድን በ95 ብር እንደመሸጥ አይነት (በ95 የገዛ ሰው 100 ብር ተደርጎ ይከፈለዋል እንደማለት ነው)፡፡
ሃሳቡን በቀላሉ እድትረዱት የኢትዮጲያ ልማት ባንክ የህዳሴ ግድቡን ለመገንባት ቦንድ ለህዝብ አቅርቦ ሰዎች በቻሉት መጠን በሙሉ ገዝተዋል ከአምስት ዓመታት (Maturity) በኋላ ወለድ በማሰብ ክፍያ ሲፈጽም የምትመለከቱት የእዳ ሰነድን ይወክላል (የህዳሴው ግድብ የግምጃ ቤት ሰነድ ሳይሆን እንደቆይታው በኖት እና በቦንድ ውስጥ ሊጠቃለል ይችላል (በኢትዮጲያ ሁኔታ አሁን ላይ የግምጃ ቤት ሰነድ ለልማት ድርጅቶች (የፋይናንስ ተቋማትም ይጋበዛሉ!) በሽያጭ የሚቀርብ ሲሆን ወደፊት የስቶክ ገበያው ሲከፈት ለጠቅላላ ገበያው ሊለቀቀቅ ይችላል፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ ከሌሎች የመንግስት የእዳ ሰነዶች አይነት የአጭር ጊዜ እዳ ነው፡፡ ሌሎቹ Treasury Note ከ1- 10 ዓመት ቆይታ ያለው ብድር ሲሆን Treasury Bond እስከ 30 ዓመት ሊቆይ የሚችል እዳ የሚይዙ ናቸው፡፡
የግምጃ ቤት ሰንድ ሻጩ መንግስት በመሆኑ ላይከፈል ይችላል/ Default የሚል ስጋት የሌለበት ነው፡፡ አንድ ሰነድ የገዛ ሰው የመክፈያው ወቅት እስኪደርስ ወለድም ሆነ የከፈለውን ገንዘብ ባያገኝም ለሌላ ሰው (በካፒታል ገበያ በኩል የመሸጥ እድል ግን ይኖረዋል)፡፡
የግምጃ ቤት ሰነድ በባህሪው ዝቅተኛ እና ቋሚ ወለድ የሚታሰብበት (አንዴ ለሽያጭ ከቀረበ በኋላ ዋጋ ንረትን ከግምት በመክተት የማይለዋወጥ) በመሆኑ ስጋት የሚፈጥር ሲሆን የመንግስት መተማመኛ ያለው እና በካፒታል ገበያ በኩል በቀላሉ ለሌላ ሰው መሸጥ የሚችል መሆኑ እንደ እድል ያስቆጥረዋል፡፡
የብርሃን ባንክ ባለአክሲዮኖች የትርፍ ድርሻ ዝቅተኛ በመሆኑ ቅሬታቸዉን ገለፁ
የብርሃን ባንክ ባለአክሲዮኖች በቅርቡ በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት የተገኘው የትርፍ ክፍፍል ዝቅተኛ በመሆኑ ቅሬታቸውን ገለጹ።
የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ለ2022/23 የሒሳብ ዓመት ከ7 በመቶ በታች የትርፍ ክፍፍል ሐሳብ በማቅረቡ ከፍተኛ ትችት ገጥሞታል። ባለአክሲዮኖች አሁን ያለው ሁኔታ ተቀባይነት እንደሌለው ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ከ16,000 በላይ ባለአክሲዮኖች በተገኙበት የባንኩ 14ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ 15.6 በመቶ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልፆ ከዚህ ዉስጥ ለአንድ ባለአክሲዮን የትርፍ ድርሻ 156.2 ብር መሆኑን ተነግሯል ነገር ግን በማዕከላዊ ባንክ ውስጥ ያሉ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣኖች ወደ 6.03 በመቶ ዝቅ ያደረጉት ብድሮች እና ሌሎች ተቀናሾች ምክንያት ነው።
ለተከታታይ ዓመታት የገቢ መጠን እያሽቆለቆለ መምጣቱን እና ከ7 ወደ 6 በመቶ ዝቅ ማለቱ ለጉዳት የሚያጋልጥ መሆኑን በማንሳት አንዳንድ ባለአክሲዮኖች ብስጭታቸውን ገልፀዋል ።
አንድ ባለአክሲዮን የሙስና አዝማሚያዎች መኖራቸውን በመጥቀስ በባንኩ የሥራ አፈጻጸም ላይ ከዓመት ወደ ዓመት ለውጥ ባለመኖሩ ቅሬታ ማቅረባቸውን ካፒታል ሰምቷል።
ሌላው የባለ አክሲዮኖች ስጋት በአዲስ አበባ 5,400 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ሰንጋ ተራ እየተባለ የሚጠራው የዋና መሥሪያ ቤት ግንባታ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ ከተማ ሊገነባ የታቀደው ሌላ ሕንፃ ነው። ባለአክሲዮኖች የእነዚህ ፕሮጀክቶች የረዥም ጊዜ የግንባታ ደረጃ ካፒታልን በማያያዝ እና የባንኩን የፋይናንስ አቋም ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ በመሆኑን ተከራክረዋል።
capitalethiopia
የብርሃን ባንክ ባለአክሲዮኖች በቅርቡ በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት የተገኘው የትርፍ ክፍፍል ዝቅተኛ በመሆኑ ቅሬታቸውን ገለጹ።
የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ለ2022/23 የሒሳብ ዓመት ከ7 በመቶ በታች የትርፍ ክፍፍል ሐሳብ በማቅረቡ ከፍተኛ ትችት ገጥሞታል። ባለአክሲዮኖች አሁን ያለው ሁኔታ ተቀባይነት እንደሌለው ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ከ16,000 በላይ ባለአክሲዮኖች በተገኙበት የባንኩ 14ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ 15.6 በመቶ የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን ገልፆ ከዚህ ዉስጥ ለአንድ ባለአክሲዮን የትርፍ ድርሻ 156.2 ብር መሆኑን ተነግሯል ነገር ግን በማዕከላዊ ባንክ ውስጥ ያሉ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣኖች ወደ 6.03 በመቶ ዝቅ ያደረጉት ብድሮች እና ሌሎች ተቀናሾች ምክንያት ነው።
ለተከታታይ ዓመታት የገቢ መጠን እያሽቆለቆለ መምጣቱን እና ከ7 ወደ 6 በመቶ ዝቅ ማለቱ ለጉዳት የሚያጋልጥ መሆኑን በማንሳት አንዳንድ ባለአክሲዮኖች ብስጭታቸውን ገልፀዋል ።
አንድ ባለአክሲዮን የሙስና አዝማሚያዎች መኖራቸውን በመጥቀስ በባንኩ የሥራ አፈጻጸም ላይ ከዓመት ወደ ዓመት ለውጥ ባለመኖሩ ቅሬታ ማቅረባቸውን ካፒታል ሰምቷል።
ሌላው የባለ አክሲዮኖች ስጋት በአዲስ አበባ 5,400 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ሰንጋ ተራ እየተባለ የሚጠራው የዋና መሥሪያ ቤት ግንባታ እንዲሁም በወላይታ ሶዶ ከተማ ሊገነባ የታቀደው ሌላ ሕንፃ ነው። ባለአክሲዮኖች የእነዚህ ፕሮጀክቶች የረዥም ጊዜ የግንባታ ደረጃ ካፒታልን በማያያዝ እና የባንኩን የፋይናንስ አቋም ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ በመሆኑን ተከራክረዋል።
capitalethiopia
ET Securities pinned «#Treasury_Bill (የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነድ) መንግስታት በሁለት ምክንያት የግምጃ ቤት ሰነድ ለሽያጭ ያቀርባሉ… የመጀመሪያዊ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለመስራት የካፒታል ፍላጎቶቻቸውን ለማሟላት (መንግስት ገቢ ከመሰብሰቡ በፊት ፕሮጀክቶቹ በፋይናንስ እጥረት እንዳይቆሙ ከገበያው በወለድ በመበደር ለማከናወን በማሰብ) ሲሆን….. በሁለተኝነት በገበያው ያለውን የገንዘብ አቅርቦት እና ፍላጎት ለማመጣጠን…»