#የትርጉም #መናፍስት
እንደ ሰው ስጠይቅ በብሔር አታዳምጡኝ
የራስ አስቀምጣችሁ የዘር ጆሮ አትስጡኝ
የዘር መልስ አትስጡኝ
እንደ ሰው ሲያወራ በጎጥ ጆሮ ሰምተን
"#መገዳደፍ" ጀመርን "#መደጋገፍ" ትተን
* * *
#እንግዳ #ሲመጣ
ትልቅ ሀገር ሽጠን መንደር ስለገዛን
"#ማሳቁን" ትተነው "#ማሳቀቅ" አበዛን
ሰውነትን ጥሎ ዘረኝነት ሲያልፈው
"#ተቀባይ" "#ተበቃይ" ሆነውና አረፈው
ዜግነት ሞቶ ብሄር ጀገነ
"#መቀበል" ማለት "#መበቀል" ሆነ
* * *
#አዲስ #ሞያ #ሆኖ
አፍ በጆሮ ማረድ ንግግር መበለት
"#እንቆረጥ" ሆኗል "#እንቆጠር" ማለት
#አትራፊ #ተብሎ
ፍቺ ሊቸረቸር ከሱቅ የወጣ ‘ለት
"#እንዝጋ" ይልሀል "#እንግዛ" ለማለት
* * *
ተርጓሚ ሲበዛ በየጥጋጥጉ
"#መተራረድ" ሆነ "#መረዳዳት" ወጉ
"#የማብላት" ትርጉሙ "#መብላት" የሆነ ‘ለት
"#መገናነዝ" ሆኗል "#መዘጋገን" ማለት
"#ሊቁን" ጠፍንገን "#ቂሉን" ስንፈታ
"#ወንጀል" ገነነ "#በወንጌል" ፋንታ
ትርጉም አለቀ ፍቺ ተዛባ
"#ልጅ" ስንጣራ "#ጅል" ዘሎ ገባ
========||=======
እንደ ሰው ስጠይቅ በብሔር አታዳምጡኝ
የራስ አስቀምጣችሁ የዘር ጆሮ አትስጡኝ
የዘር መልስ አትስጡኝ
እንደ ሰው ሲያወራ በጎጥ ጆሮ ሰምተን
"#መገዳደፍ" ጀመርን "#መደጋገፍ" ትተን
* * *
#እንግዳ #ሲመጣ
ትልቅ ሀገር ሽጠን መንደር ስለገዛን
"#ማሳቁን" ትተነው "#ማሳቀቅ" አበዛን
ሰውነትን ጥሎ ዘረኝነት ሲያልፈው
"#ተቀባይ" "#ተበቃይ" ሆነውና አረፈው
ዜግነት ሞቶ ብሄር ጀገነ
"#መቀበል" ማለት "#መበቀል" ሆነ
* * *
#አዲስ #ሞያ #ሆኖ
አፍ በጆሮ ማረድ ንግግር መበለት
"#እንቆረጥ" ሆኗል "#እንቆጠር" ማለት
#አትራፊ #ተብሎ
ፍቺ ሊቸረቸር ከሱቅ የወጣ ‘ለት
"#እንዝጋ" ይልሀል "#እንግዛ" ለማለት
* * *
ተርጓሚ ሲበዛ በየጥጋጥጉ
"#መተራረድ" ሆነ "#መረዳዳት" ወጉ
"#የማብላት" ትርጉሙ "#መብላት" የሆነ ‘ለት
"#መገናነዝ" ሆኗል "#መዘጋገን" ማለት
"#ሊቁን" ጠፍንገን "#ቂሉን" ስንፈታ
"#ወንጀል" ገነነ "#በወንጌል" ፋንታ
ትርጉም አለቀ ፍቺ ተዛባ
"#ልጅ" ስንጣራ "#ጅል" ዘሎ ገባ
========||=======