#ኤርትራ እና ሱዳን በኢትዮጵያ ጉዳይ መወያየታቸው ተገለጸ
አፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት-ህዳር 02, 2013
ኤርትራ እና ሱዳን በኢትዮጵያ ጉዳይ መወያየታቸው ተገለጸ::
የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ እና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አማካሪ የማነ ገብረ አብ የተካተቱበት የኤርትራ ልዑክ ዛሬ ካርቱም አቅንቶ ከሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ም/ቤት ፕሬዝዳንት አል-ቡርሃን እና ከጠ/ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ጋር መወያየቱን የሱዳን ዜና ወኪል ዘግቧል፡፡
የኤርትራ ልዑክ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ የተላከ መልዕክት ለሱዳን መሪዎች ያደረሰ ሲሆን በቆይታቸው ከሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ካደረጉት ውይይት በተጨማሪ የሁለቱም ጎረቤት በሆነችው ኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ችግር መምከራቸውንም የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል በትዊተራቸው ገልጸዋል፡፡
ይሁን እንጂ ስለውይይታቸው የተባለ ዝርዝር ጉዳይ የለም፡፡
#Sudan_Eritrea #Ethiopia
#al-Ain News
አፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት-ህዳር 02, 2013
ኤርትራ እና ሱዳን በኢትዮጵያ ጉዳይ መወያየታቸው ተገለጸ::
የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ እና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አማካሪ የማነ ገብረ አብ የተካተቱበት የኤርትራ ልዑክ ዛሬ ካርቱም አቅንቶ ከሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ም/ቤት ፕሬዝዳንት አል-ቡርሃን እና ከጠ/ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ጋር መወያየቱን የሱዳን ዜና ወኪል ዘግቧል፡፡
የኤርትራ ልዑክ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ የተላከ መልዕክት ለሱዳን መሪዎች ያደረሰ ሲሆን በቆይታቸው ከሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ካደረጉት ውይይት በተጨማሪ የሁለቱም ጎረቤት በሆነችው ኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ችግር መምከራቸውንም የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገ/መስቀል በትዊተራቸው ገልጸዋል፡፡
ይሁን እንጂ ስለውይይታቸው የተባለ ዝርዝር ጉዳይ የለም፡፡
#Sudan_Eritrea #Ethiopia
#al-Ain News
#ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር) ን ጨምሮ የ39ኝ የህወሓት ተወካዮች ያለመከሰስ መብት ተነስቷል::
አፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት-ህዳር 03, 2013
6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት መሰብሰቢያ አደራሽ በማካሄድ ላይ ያለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በወንጀል የተጠረጠሩ ከፍተኛ የህወሓት ባለስልጣናትን ያለመከሰስ መብት አነሳ፡፡
ግለሰቦቹ የተጠረጠሩት ጦር መሳሪያ ይዞ በማመፅ፣ የሀገር መከላከያን በመውጋት እና በሌሎችም ተያያዥ ወንጀሎች ዋና አድራጊነት ነው።
ምክር ቤቱ የተጠርጣሪዎቹን ያለመከሰስ መብት ያነሳው ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች ጠርጥሬያቸዋለሁ በሚል ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ መነሻ በማድረግ ነው፡፡
በዚህም መሰረት
ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ
አቶ አባይ ፀሃዬ
አምባሳደር አዲስ ዓለም ቤሌማ- (ዶ/ር)
አቶ ጌታቸው ረዳ
አቶ አፅበሃ አረጋዊ
አቶ ገብረ እግዚአብሄር አርአያን ጨምሮ የ39ኝ የህወሓት ተወካዮች ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን ፋና ብሮድካስቲንግ ዘግቧል፡፡
#al-Ain News
አፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት-ህዳር 03, 2013
6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባውን በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት መሰብሰቢያ አደራሽ በማካሄድ ላይ ያለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በወንጀል የተጠረጠሩ ከፍተኛ የህወሓት ባለስልጣናትን ያለመከሰስ መብት አነሳ፡፡
ግለሰቦቹ የተጠረጠሩት ጦር መሳሪያ ይዞ በማመፅ፣ የሀገር መከላከያን በመውጋት እና በሌሎችም ተያያዥ ወንጀሎች ዋና አድራጊነት ነው።
ምክር ቤቱ የተጠርጣሪዎቹን ያለመከሰስ መብት ያነሳው ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች ጠርጥሬያቸዋለሁ በሚል ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ መነሻ በማድረግ ነው፡፡
በዚህም መሰረት
ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ዶ/ር)
አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ
አቶ አባይ ፀሃዬ
አምባሳደር አዲስ ዓለም ቤሌማ- (ዶ/ር)
አቶ ጌታቸው ረዳ
አቶ አፅበሃ አረጋዊ
አቶ ገብረ እግዚአብሄር አርአያን ጨምሮ የ39ኝ የህወሓት ተወካዮች ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ መወሰኑን ፋና ብሮድካስቲንግ ዘግቧል፡፡
#al-Ain News