#አሸባሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን ትንኮሳ ያደረገባቸውን ስትራቴጂክ ቦታዎች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን አስለቀቀ
ሰመራ-ነሐሴ 11፣ 2013 (አፋ.ብ.መ.ድ)
አሸባሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን ትንኮሳ ያደረገባቸውን ስትራቴጂክ ቦታዎች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን አስለቀቀ
አሸባሪው የህወሓት ቡድን ቆቦ ከተማን በመቆጣጠር ወደ ሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች በቀላሉ ለማለፍ በተለምዶ የአርሴማ ተራሮች የተባሉ አራት ተራሮችን እስከ ሀምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ተቆጣጥሮ ለቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ከፍተኛ ስጋት ሆኖ ነበር።
ሆኖም የፌዴራል ፖሊስ ሰሜን ዳይሬክቶሬት ዲቪዥን አራት ፈጥኖ ደራሽ አባላት ከሀገር መከላከያ ሠራዊትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት አነስተኛ የሰው ሃይልና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ብቻ በመጠቀም በርካታ የጁንታውን ሃይል በመደምሰስ አራቱንም ተራሮች በአንድ ቀን በማስለቀቅ ለአካባቢው ሚሊሺያ ማስረከብ መቻላቸው ተገልጿል፡፡
የጠላትን ግብዓተ መሬት ሳንፈጽም አንመለስም ያሉት የሰሜን ዳይሬክቶሬት ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ሻለቃ ምክትል አዛዥ ኢ/ር ሀሰን አብዱ የፌዴራል ፖሊስ አባላቱ ከሀገር መከላከያ ሰራዊትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት አሸባሪውን የህወሓት ጁንታ ቡድን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት፣ የተማመነባቸውን ስትራቴጂክ ቦታዎች በማስለቀቅና ጀሌዎቹን በመደምሰስ ለአካባቢው ማህበረሰብ መረጋጋትን ፈጥረዋል ብለዋል፡፡
አባላቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ሌላ ግዳጅ ለመሰማራት ዝግጅታቸውን አጠናቀው ትእዛዝ እየተጠባበቁ መሆናቸውንም የሰሜን ዳይሬክቶሬት ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ሻለቃ ምክትል አዛዡ ኢ/ር ሀሰን አብዱ ተናግረዋል።
በቀጣይም አሸባሪውን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት ዝግጁ ነን ሲሉ አንዳንድ ያነጋገርናቸው የፈጥኖ ደራሽ አባላቱ ተናግረዋል።
ጦርነት የገጠምነው ጉድጓድ ውስጥ ተደብቆ እንደገና ወረራ ከፈፀመ ሃይል ጋር በመሆኑ ተራራ ሲይዝ ተስፋ ባለመቁረጥ፤ ተራራ ሲለቅ "ተሸነፈ" ብለን ሳንዘናጋና ሳንደናገጥ ተልዕኮአችንን በብቃት መወጣት ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በመጨረሻም ለሀገር ሉዓላዊነት ሲባል ህዝባችንን ከጎናችን በማሰለፍና ጁንታውን እስከመጨረሻው ለማጥፋት መስዋትነትም ጭምር ለመክፈል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዝግጁ መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል።
#Federal Police
ሰመራ-ነሐሴ 11፣ 2013 (አፋ.ብ.መ.ድ)
አሸባሪው የህወሓት ጁንታ ቡድን ትንኮሳ ያደረገባቸውን ስትራቴጂክ ቦታዎች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን አስለቀቀ
አሸባሪው የህወሓት ቡድን ቆቦ ከተማን በመቆጣጠር ወደ ሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች በቀላሉ ለማለፍ በተለምዶ የአርሴማ ተራሮች የተባሉ አራት ተራሮችን እስከ ሀምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ተቆጣጥሮ ለቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ከፍተኛ ስጋት ሆኖ ነበር።
ሆኖም የፌዴራል ፖሊስ ሰሜን ዳይሬክቶሬት ዲቪዥን አራት ፈጥኖ ደራሽ አባላት ከሀገር መከላከያ ሠራዊትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት አነስተኛ የሰው ሃይልና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ብቻ በመጠቀም በርካታ የጁንታውን ሃይል በመደምሰስ አራቱንም ተራሮች በአንድ ቀን በማስለቀቅ ለአካባቢው ሚሊሺያ ማስረከብ መቻላቸው ተገልጿል፡፡
የጠላትን ግብዓተ መሬት ሳንፈጽም አንመለስም ያሉት የሰሜን ዳይሬክቶሬት ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ሻለቃ ምክትል አዛዥ ኢ/ር ሀሰን አብዱ የፌዴራል ፖሊስ አባላቱ ከሀገር መከላከያ ሰራዊትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት አሸባሪውን የህወሓት ጁንታ ቡድን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት፣ የተማመነባቸውን ስትራቴጂክ ቦታዎች በማስለቀቅና ጀሌዎቹን በመደምሰስ ለአካባቢው ማህበረሰብ መረጋጋትን ፈጥረዋል ብለዋል፡፡
አባላቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ሌላ ግዳጅ ለመሰማራት ዝግጅታቸውን አጠናቀው ትእዛዝ እየተጠባበቁ መሆናቸውንም የሰሜን ዳይሬክቶሬት ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ሻለቃ ምክትል አዛዡ ኢ/ር ሀሰን አብዱ ተናግረዋል።
በቀጣይም አሸባሪውን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት ዝግጁ ነን ሲሉ አንዳንድ ያነጋገርናቸው የፈጥኖ ደራሽ አባላቱ ተናግረዋል።
ጦርነት የገጠምነው ጉድጓድ ውስጥ ተደብቆ እንደገና ወረራ ከፈፀመ ሃይል ጋር በመሆኑ ተራራ ሲይዝ ተስፋ ባለመቁረጥ፤ ተራራ ሲለቅ "ተሸነፈ" ብለን ሳንዘናጋና ሳንደናገጥ ተልዕኮአችንን በብቃት መወጣት ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በመጨረሻም ለሀገር ሉዓላዊነት ሲባል ህዝባችንን ከጎናችን በማሰለፍና ጁንታውን እስከመጨረሻው ለማጥፋት መስዋትነትም ጭምር ለመክፈል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዝግጁ መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል።
#Federal Police