#ከከሚሴ ወደ አዲስ አበባ ሊዘዋወር የነበሩ 53 ጩቤ እና ሌሎች ሕገወጥ ቁሳቁስ በቁጥጥር ስር ዋሉ::
ሰመራ-ነሃሴ 25, 2013 (አፋ.ብ.መ.ድ)
ከከሚሴ ወደ አዲስ አበባ ሊዘዋወር የነበሩ 53 ጩቤ እና ሌሎች ሕገወጥ ቁሳቁስ በቁጥጥር ስር ዋሉ::
ከከሚሴ ወደ አዲስ አበባ ሊዘዋወሩ የነበሩ ጩቤ፣ የጥይት መያዣ ካርታ እና ሌሎች ሕገወጥ ቁሳቁስ በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
ዛሬ ከጠዋቱ 3፡30 አካባቢው 53 ሕገወጥ ጩቤ፣ 30 የጥይት መያዣ ካርታ፣ 30 እንግብ፣ 30 የትጥቅ መያዣ ቀበቶ እንዲሁም 3 ኪሎ የሚመዝን አደገኛ እጽ መሰል ነገር ከከሚሴ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ ሊዘዋወር ሲል በፖሊስ እና በማህበረሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ጽ/ቤቱ ገልጿል፡፡
ሕገወጥ ቁሳቁሱን ሲያዘዋውር የነበረው ግለሰብም በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት መሆኑን ከሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
#EBC
ሰመራ-ነሃሴ 25, 2013 (አፋ.ብ.መ.ድ)
ከከሚሴ ወደ አዲስ አበባ ሊዘዋወር የነበሩ 53 ጩቤ እና ሌሎች ሕገወጥ ቁሳቁስ በቁጥጥር ስር ዋሉ::
ከከሚሴ ወደ አዲስ አበባ ሊዘዋወሩ የነበሩ ጩቤ፣ የጥይት መያዣ ካርታ እና ሌሎች ሕገወጥ ቁሳቁስ በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
ዛሬ ከጠዋቱ 3፡30 አካባቢው 53 ሕገወጥ ጩቤ፣ 30 የጥይት መያዣ ካርታ፣ 30 እንግብ፣ 30 የትጥቅ መያዣ ቀበቶ እንዲሁም 3 ኪሎ የሚመዝን አደገኛ እጽ መሰል ነገር ከከሚሴ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ ሊዘዋወር ሲል በፖሊስ እና በማህበረሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ጽ/ቤቱ ገልጿል፡፡
ሕገወጥ ቁሳቁሱን ሲያዘዋውር የነበረው ግለሰብም በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት መሆኑን ከሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
#EBC