#ምክር ቤቱ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ዛሬ ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል፣፣
ሰመራ-የካቲት 14, 2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
ምክር ቤቱ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ዛሬ ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል፣፣
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ በሚገኘው ልዩ ስብሰባው የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል።
እንደ ኤፍቢሲ ዘገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ህብረተሰቡ አስተያየት እንዲሰጥባቸው ከዚህ በፊት ዝርዝራቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
የተገኘውን ግብዓት ምክር ቤቱ ከተመለከተ በኋላም መስፈርቱን በከፍተኛ ደረጃ አሟልተዋል ያላቸውን እጩ ኮሚሽነሮች በመምረጥ እንዲሾሙ ለምክር ቤቱ አቅርቧል።
በዚህ መሰረትም፦
1. ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
2. ወይዘሮ ሂሩት ገብረስላሴ
3. ዶክተር ተገኘወርቅ ጌቱ
4. አምባሳደር ዶክተር አይሮሪት መሃመድ
5. ወይዘሮ ብሌን ገብረመድህን
6. ዶክተር ዮናስ አዳዬ
7. አቶ ዘገየ አስፋው
8. አቶ መላኩ ወልደማሪያም
9. አምባሳደር መሃሙድ ድሪር
10. አቶ ሙሉጌታ አጎ እና
11. ዶክተር አምባዬ ኦጋቶ እጩ ኮሚሽነር ሆነው ቀርበዋል።
ምክር ቤቱ ዛሬ እያካሄደው በሚገኘው ልዩ ስብሰባ በእነዚህ እጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከተወያየ በኋላ ይሾማቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
#EBC
ሰመራ-የካቲት 14, 2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
ምክር ቤቱ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ዛሬ ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል፣፣
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ እያካሄደ በሚገኘው ልዩ ስብሰባው የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል።
እንደ ኤፍቢሲ ዘገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ህብረተሰቡ አስተያየት እንዲሰጥባቸው ከዚህ በፊት ዝርዝራቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።
የተገኘውን ግብዓት ምክር ቤቱ ከተመለከተ በኋላም መስፈርቱን በከፍተኛ ደረጃ አሟልተዋል ያላቸውን እጩ ኮሚሽነሮች በመምረጥ እንዲሾሙ ለምክር ቤቱ አቅርቧል።
በዚህ መሰረትም፦
1. ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
2. ወይዘሮ ሂሩት ገብረስላሴ
3. ዶክተር ተገኘወርቅ ጌቱ
4. አምባሳደር ዶክተር አይሮሪት መሃመድ
5. ወይዘሮ ብሌን ገብረመድህን
6. ዶክተር ዮናስ አዳዬ
7. አቶ ዘገየ አስፋው
8. አቶ መላኩ ወልደማሪያም
9. አምባሳደር መሃሙድ ድሪር
10. አቶ ሙሉጌታ አጎ እና
11. ዶክተር አምባዬ ኦጋቶ እጩ ኮሚሽነር ሆነው ቀርበዋል።
ምክር ቤቱ ዛሬ እያካሄደው በሚገኘው ልዩ ስብሰባ በእነዚህ እጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከተወያየ በኋላ ይሾማቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
#EBC