Afar Mass Media Agency (AFMMA)
1.09K subscribers
3.65K photos
161 videos
2 files
655 links
This channel is an official channel of Afar Mass Media Agency (AFMMA).
AFMMA is an autonomous government organization accountable to the regional Council of the Afar region.
Download Telegram
#የሚዲያና ኮሙኒኬሽን የቀውስ ጊዜ ዘገባና የመረጃ ስርአት በጥንቃቄ መመራት ይኖርበታል--የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ሰመራ-ነሃሴ 22/2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)

የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ተቋማት የቀውስ ጊዜ ዘገባና የመረጃ ተደራሽነት ብሄራዊ ጥቅምን ታሳቢ ያደረገና በጥንቃቄ የሚመራ ሊሆን እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አሳሰበ።

ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የፌዴራልና የክልል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ጉባኤ ተጠናቋል።

ጉባዔው የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፣ የፌዴራልና የክልል የኮሙኒኬሽን ዘርፎች የ2014 በጀት ዓመት የስራ አፈጸጻምና የ2015 ዕቅድ ላይ ተወያይቷል።

የመንግስት ኮሙኒኬሸን የቀጣይ 5 ዓመታት ረቂቅ ስትራቴጂ ሰነድ እንደሁም በመንግስት ኮሙኒኬሸንና የክልል የዘርፉ መዋቅሮች የስራ ግንኙንት ላይ በተዘጋጀ የመግባቢያ ሰነድ ላይም መክሯል።

የክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት በፌዴራል መንግስት የሚገለጹ መረጃዎችን የሚለቁበት አግባብ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋለት እንደሚገባም በጉባኤው ተመልክቷል።

የክልል የኮሙኒኬሸን መዋቅሮች ያልተናበቡ መረጃዎችን ከመስጠት እንዲቆጠቡና ፈቃድ ያልተሰጣቸው ሚዲያዎች በመንግስት ሁነቶች ላይ የሚሳተፉበት ዕድልም ሊስተካከል ይገባል ነው ያሉት።

በተለይ አገር ቀውስ ሲገጥማት የሚዲያና ኮሙኒኬሸን ዘርፉ ላይ ያለው የመረጃ ፍሰት ጥንቃቄ ይሻል ብለዋል።

የክልል ሚዲያዎች ከክልላቸው ባሻገር ወደ ሌሎችም ክልሎች ተደራሽነታቸውን በማስፋት በአገራዊ መግባባትና ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም ጠቅሰዋል።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ፤ ለአገርና ህዝብ ጥቅም ሲባል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ እንዲጠናከር ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።

የአዘጋገብና መረጃ አሰጣጥ ሂደት ፈጣንና በዘመነ መልኩ ከወቅቱ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች እንደየ ዐውዱ እየተቃኘ መራመድ ይኖርበታልም ነው ያሉት።

ጠንካራ ኮሙኒኬሽን ስርዓት ለመገንባት የሚያስችል የኮሙኒኬሽን ፖሊሲና ስትራቴጂ ዝግጅት እየተጠናቀቀ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

የክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት በተቀናጀ አገራዊ አጀንዳ እየተናበቡ መስራት እንዳለባቸው ጠቅሰው በተናጠል አጀንዳ ቀርጾ ማስተጋባት የለባቸውም ብለዋል።

በመሆኑም በፌዴራል መንግስት በኩል ሊሰራጩ የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ መረጃ ከመስጠት ሊቆጠቡ ይገባል ነው ያሉት።

በተለይም የቀውስ ጊዜ የኮሙኒኬሽን ስራ ልዩ ትኩረት ይሻል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ጉዳዩ ከሚመለከተው አገራዊ ተቋምና ኮሚቴ በስተቀር ከጦርነት ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ማሰራጨት አይችሉም ነው ያሉት።

በእንዲህ አይነት ወቅት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎች የአገርን ብሔራዊ ጥቅም ታሳቢ ባደረገ መልኩ መመራት አለባቸው ብለዋል።

እንደ ሚኒስትሩ ገለፃ የቀውስ ጊዜ አዘጋገብ መመሪያዎች የተዘጋጁ በመሆኑ በቀጣይ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል።

የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ደሲሳ፤ የህዝብ መረጃ የማግኘት መብት መገደብ ስለሌበት ተቋማት በየወቅቱ ለሚዲያዎች መረጃ መስጠት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

በተቋማት ላይ ጠንካራ የምርመራ ጋዜጠኝነት እንዲሰራ የመንግስት ጽኑ ፍላጎት መሆኑን ጠቅሰው ከወዲሁ ግልጽ መረጃ ለመስጠት መዘጋጀት አለባቸው ነው ያሉት።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎትም ከክልሎች ጋር ደረጃውን በጠበቀና ወጥነት ባለው አግባብ ተናቦ እንደሚሰራ ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
#መከላከያ ሠራዊት ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ መሆኑን አስታወቀ፣፣

ሰመራ፣ ነሐሴ 22፣ 2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠባቂ በመሆኑ ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን በከፍተኛ ጥንቃቄ እየፈፀመ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡

መከላከያ ሠራዊት በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ÷ አሸባሪው ህወሓት የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱ፣ “እኔ እየመራሁ የማልዘርፋት ሀገር ትፍረስ” ከሚል እኩይ ተግባሩና ፀረ-ሕዝብ ባህሪው አንፃር የሚጠበቅ ነው ብሏል።

በተቃራኒው እኛ ግን የመላው ከ120 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵውያንን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ተቀብለን የምንፈፅም ሕዝባዊና ፕሮፌሽናል ብሔራዊ ኃይል ስለሆንን፥ መላውን ሕዝባችንና የትግራይን ጨቅላ ሕፃናት ከከንቱ እልቂት የመታደግ ሞራላዊና ሕጋዊ ግዴታ አለብን ነው ያለው መከላከያ በመግለጫው፡፡

ህወሓት ያኔ ጥንት በአንደኛው የዓለም ጦርነት ስልጣኔና የዘመነ ጦር መሳሪያ ባልነበረበት ጊዜ ጦርነትን በሰው ማዕበል ገጥመህ ማሸነፍ ወረት በነረበት ወቅት እንደሚደረገው፥ ከግብረ-ገብ፣ ከሞራልና ሕጋዊነት በእጅጉ በተጣረሰ አኳኋን ገና በሰውነታቸው ያልጠነከሩ ጨቅላና ለጋ ሕፃናትን ከኋላ በኃይል እየገፋ፥ በሚገባ ሰልጥኖ እስከ አፍንጫው ከታጠቀ የመከላከያና ጥምር ኃይል ፊት እያሰለፈ የእሳት እራት አድርጎ በማስፈጀት የሞት ቀኑን ለማዘግየት ታሪክ ይቅር የማይለውን ጭካኔ በገዛ ወገኑ፣ ወገናችን የትግራይ ሕዝብ ላይ እየፈፀመ መሆኑንም ነው የገለጸው፡፡

መከላከያ ሠራዊት በሕግ የተቋቋመ፣ በሕግ የሚመራና በሕዝብ በተመረጠ መንግስት የሚታዘዝ፣ ሲያለማ እደሚሞገስና እንደሚሸለም ሁሉ የተሰጠውን ሕገ መንግስታዊ ተልዕኮ በሚገባ ሳይፈፅም ሲቀርና ሲያበላሽ በሀገሪቱና ዓለም አቀፍ ሕጎች የሚጠየቅና የሚዳኝ ሀገራዊ ኃይል እንደሆነም በመግለጫው አስረድቷል፡፡

ስለሆነም መከላከያ ሠራዊት ሕግን ተከትሎ ወገኑን ከሰቆቃና እልቂት ለመታደግ አስፈላጊውን ሁሉ መስዋዕትነት በጀግንነት በመክፈል፥ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም ያስከብራል ነው ያለው መከላከያ ሠራዊት፡፡

የሽብር ቡድኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ተከፋይ፣ ጉዳይ አስፈፃሚና በወንጀል የሚፈለግ ሕገ-ወጥ ሽፍታ መሆኑን ያመላከተው መከላከያ÷ ቡድኑ የኃላፊነትና የተጠያቂነት መንፈስ የማይሰማው መሆኑን ገልጾ፥ በባህሪው ምክንያት ሊሰማውም እንደማይችል አስረድቷል፡፡

በዚህ ሳቢያም የሽብር ቡድኑ እንደፈለገው የሚዋሽ እና የግፎች ሁሉ ጥግ የሆነ ተግባር በገዛ ወገኑ ላይ የሚፈጽም መሆኑንም ነው ያብራራው፡፡

ስለሆነም መከላከያ ሠራዊት ሕዝባችንን ከዚህ አረመኔ ቡድን ቀንበር ለማላቀቅና ከከንቱ ጭፍጨፋ ለማዳን ለሕዝባችንና ለሀገራችን ይጠቅማል የተባለውን ሁሉ በመስዋዕትነታችን እውን ለማድረግ በከፍተኛ ብቃትና የላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡

ሕዝባችንን ከፍጅት ለመታደግ ሲባል፥ መሆን የሚገባውን ሁሉ አጠቃላይ ሁኔታን በማያበላሽ አግባብ ቀጣይም ሊኖር እንደሚችል መታወቅ ይኖርበታል ነው ያለው፡፡

እኛ ታላቅና ታሪካዊ ኃላፊነት ካለበት የመከላከያ ኃይል በሚጠበቅ አግባብ፣ ሁለንተናዊ በሆነና ነገን አሻግሮ በሚመለከት እሳቤ እንዲሁም በወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ የምናደርገው እና እናንተ በጋለ ጥልቅ የሀገር ፍቅር ስሜት ዛሬ፣ አሁን፣ እዚችው እዲሆን የምትፈልጉትን ሁሉ "አፍ በእጅ በሚያሲዝ" አስተማማኝና ዘላቂ በሆነ ድል ይታረቃል ሲልም አረጋግጧል፡፡

“ዛሬም ሆነ እስከ ወዲያኛው የኢትዮጵያን ክብርና ጥቅም ለመጉዳት የሚደረግ ከሰማይ በታች ባለ ፈተና ሁሉ እንደማንፈተን ታውቃላችሁ! ታምኑናላችሁም!” ሲል የገለጸው መከላከያ ሠራዊት፥ ለኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ደህንነት፣ የግዛት አንድነትና ለሀገረ መንግሥቱ ቀጣይነት በመቆም የምንከፍለው መስዋዕትነት ክብርና ኩራታችን ነው ብሏል በመግለጫው፡፡
ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ መግለጫ፣፣
#Congratulations
#Unkaq Ruffa Inteenim

Samarâ Jaamuqat sissin barittô qaynatitte kee barittô caddol barisak sugte barteenit asaaku dooqaysak geytinta.

Asaaku akkuk geytinta dooqaysol Inik hattô caddooy, nammey haytô caddoo kee Ekestenshinih baritak sugteh tan barteenitiiy, ken buxah mara kee awlaytit elle geytinte.

#QafárTV

Ximolik 28, 2014
#Samarâ Jaamiqat 13heele addah inki Alfiik Daga Yakke Barteynit Dooqayse.

Samara-Ximolik 28, 2014 (AFMMA)

#Samarâ Jaamiqat 13heele addah inki Alfiik Daga Yakke Barteynit Dooqayse.

Asaaku akkuk geytinta dooqaysol Baxaabaxsa Le Barittô qaynatittel Barisak Sugteh Tan Sayyok 169 Kee Labhak 1021, ittat 1190 Yakke Barteynit Dooqaysime.

Samarâ Jaamiqat Asaakih Ayro Dooqassam 4 Weelol Barisak Sugteh Tan barteeni (Qimbô Digriiy, 2hayto Digriiy, Karmâ Baritto Kee Ekestenshinil Barisak Sugteh Tan 1190 Yakkeh Yan Barteyni.

#Missossem: Qali Qabdulkaadir

#QafárTV