#የአፋር እና የአማራ ህዝቦችን ጠንካራ ግንኙነት ለማስቀጠልና በጋራ ለመልማት እንደሚሰሩ የሁለቱ ክልል መንግስታት አስታወቁ።
ሰመራ- ሰኔ 02/2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የአፋር እና የአማራ ህዝቦችን ጠንካራ ግንኙነት ለማስቀጠልና በጋራ ለመልማት እንደሚሰሩ የሁለቱ ክልል መንግስታት አስታወቁ።
በአፋር እና በአማራ ህዝቦች መካከል ያለውን የቆየ እና የዳበረ ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲሁም ሁለቱም ሕዝቦች በጋራ በልማት በሚያድጉበት ጉዳይ ላይ የአፋር እና የአማራ ክልል መንግስታት ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱም የሁለቱ ክልሎች ፕሬዝዳንቶችን አቶ አወል አርባ እና ዶክተር ይልቃል ከፋለን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች የተገኙ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ፣ በተለይም በጸጥታ፣ በኢኮኖሚ እና እርስ በርስ ግንኙነትን ማጠናከር ዙሪያ የተለየ ትኩረት ተሰጥቶ ውይይቱ ተካሂዷል፡፡
በመጨረሻም የተነሱ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮችም በተግባር መሬት እንዲወርዱ ሁሉም ባለድርሻ አካል በሃለፊነት ስሜት መስራት እንዳለበት ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
#Afargcao
ሰመራ- ሰኔ 02/2014 (አፋ.ብ.መ.ድ)
የአፋር እና የአማራ ህዝቦችን ጠንካራ ግንኙነት ለማስቀጠልና በጋራ ለመልማት እንደሚሰሩ የሁለቱ ክልል መንግስታት አስታወቁ።
በአፋር እና በአማራ ህዝቦች መካከል ያለውን የቆየ እና የዳበረ ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲሁም ሁለቱም ሕዝቦች በጋራ በልማት በሚያድጉበት ጉዳይ ላይ የአፋር እና የአማራ ክልል መንግስታት ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱም የሁለቱ ክልሎች ፕሬዝዳንቶችን አቶ አወል አርባ እና ዶክተር ይልቃል ከፋለን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች የተገኙ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ፣ በተለይም በጸጥታ፣ በኢኮኖሚ እና እርስ በርስ ግንኙነትን ማጠናከር ዙሪያ የተለየ ትኩረት ተሰጥቶ ውይይቱ ተካሂዷል፡፡
በመጨረሻም የተነሱ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮችም በተግባር መሬት እንዲወርዱ ሁሉም ባለድርሻ አካል በሃለፊነት ስሜት መስራት እንዳለበት ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
#Afargcao